Tuesday, May 22, 2018

ማክሰኞ አመሻሽ ላይ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና ሌሎች መረጃዎች



አንቶን ግሪዝማን ከአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች ባደረገለት አቀባበል ምክንያት ክለቡን ለመልቀቅ ተቃርቧል፡፡ ግሪዝማን ለረጅም ጊዜ ስሙ ከባርሴሎና ጋር ሲያያዝ ነበር፡፡ ይሁንና ባለፈው ሳምንት ደግሞ በአትሌቲኮ መቆየት እፈልጋለው ብሏል የሚሉ ዘገባዎችም ወጥተው ነበር፡፡ ቢሆንም በዋንዳሜትሮፖሊታኖ በተደረገለት አቀባበል ደጋፊዎቹ በመጮሃቸው እና በማፏጫተው አሁን ዳግመኛ ክለቡን እንዲለቅ ሊያስገድድው እንደሚችል ተዘግቧል፡፡   (Marca)



ቸልሲዎች የባየር ሙኒኩን ሮበርት ሌዋንዶውስኪ በዚህ ክረምት ለማስፈረም ከሚፈልጓቸው ተጫዋቾች ውስጥ የመጀመሪያ ተፈላጊ አድርገውታል፡፡ በአንቶኒዮ ኮንቴ የመጀመሪያ የአሰልጣኝነት ዘመን የፕሪሚየር ሊጉ ቻምፒየን የሆኑት ቸልሲዎች በዚህኛው የውድድር አመት ግን አምስተኛ ሆነው ለመጨረስ ተገደዋል፡፡ እንዲሁም በቀጣዩ የውድድር አመት በቻምፒየንስ ሊግ የመሳተፍ እድልም አጥተዋል፡፡ የአንቶኒዮ ኮንቴ የወደፊት እጣ ፈንታ እስካሁን ያልተወሰነ ቢሆንም፤ አልቫሮ ሞራታ ክለቡን ይለቃል ተብሎ ስለሚጠበቀው በሱ ምትክ ሮበርት ሌዋንዶዊስኪን የመጀመሪያ ምርጫ አድርገዋል፡፡  (Telegraph)



ማንችስተር ሲቲ የሌዚስተሩን ሪያድ ማህሬዝ ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡ ማህሬዝ በ2015/16 ቻምፒየን የሆነው የሌዘስተር አስገራሚ ቡድን አባል ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ ተላያዩ ክለቦች ለመዘዋወር በራሱም ጭምር ጥያቄ አቅርቦ አልተሳካለትም፡፡ አሁን ግን ሲቲዎች በ60 ሚ. ፓውንድ ልጁን ወደ ኢቲሃድ ለማዘዋወር ተቃርበዋል፡፡ (Manchester Evening News)



ቡፎን የወደፊት እጣ ፈንታውን ለመወሰን ቢያንስ ሳምንት እንደሚፈልግ አስቃወቀ፡፡ ከጁቬንቱስ ጋር የተለያየው ቡፎን ስሜቴን ለማረጋገት ሳምንት እፈልጋለው ብሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ፒኤስጂም ሆነ ሌላ ክለቡ ዝነኛውን ግብ ጠባቂ ለማስፈረም የተወሰኑ ቀናቶችን ለመጠበቅ ይገደዳሉ፡፡ (Goal)



ለሳሪ ምንም አይነት የቀረበ ክፍያ የለም፡፡ የናፖሊው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ክለቡን ሁለተኛ ሆኖ እንዲያጠናቅቅ ከረዱት በኋላ በተለያዩ ክለቦች በመፈለግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ቸልሲ፣ ዜኒት እና ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ የሚለቅ ከሆነ ቶተንሃሞች አሰልጣኙን ይፈልጋሉ፡፡ ነገር ግን የአሰልጣኙ ወኪል አሌሳንድሮ ፔሌግሪኒ እስካሁን ምንም አይነት ክለብ ጥያቄ እንዳላቀረበ እና እሳቸውን መቅጠር የሚፈልግ ክለብ የውል ማፍረሻ የሆነውን 8 ሚ. ዩሮ ለናፖሊ መክፈል ይኖርበታል፡፡  (Goal)

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════

አርሰናሎች ኡናይ ኤምሪ አሰልጣኛቸው እንዲሆን መርጠዋል፡፡ አርሰን ቬንገር አርሰናልን መልቀቃቸው ተቀትሎ በርካታ ስሞች ከአርሰናል ጋር ሲያዝ ነበር፡፡ እስከ ትላንት ድረስም ሚኬል አርቴታ የአርሰናል አሰልጣኝ የመሆን እድል አለው ሲባል ነበር፡፡ ይሁንና አሁን አርሰናሎች ኡናይ ኤምሬን ለመቅጠር እንደወሰኑ ዘገባዎች አመላክተዋል፡፡ በቫሌንሺያ እና ሲቪያ በውስን በጀት ቡድኖቹን ከሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎና ጋር እንዲፎካከር ያደረገው ኤምሬ ለአርሰናል ተስማሚ መሆኑ በቦርዱ ታምኖበታል፡፡ በዚህም ምክንያት ቀጣዩ የአርሰናል አሰልጣኝ የዚህ አመቱ የፈረንሳይ ምርጥ አሰልጣኝነት ሽልማትን ያገኘው ኡናይ ኤምሬ ይሆናል፡፡  (Goal)


ኔይማር ወደ ሪያል ማድሪድ ለማምራት ይፈልጋል፡፡ ብራዚላዊው ኮከብ ለክለቡ ፒኤስጂ መልቀቅ እንደሚፈልግ ተናግሯል፡፡ ወኪሉም ቢሆን ከሪያል ማድሪዱ ፕሬዚዳንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ ጋር ተነጋግሯል፡፡ ይሁንና ክለቡ ፒኤስጂ እንዲሁ በቀላሉ ተጫዋቹን የሚለቀው አይሆንም፡፡ ዝውውሩም ከአለም ዋንጫው በኋላ እንጂ ከዛ ወዲ የመጠናቀቅ እድልም አይኖረውም፡፡  (Goal)


ሳንቲ ካዞርላ ከአርሰናል ጋር ተለያየ፡፡ ስድስት አመታትን ከአርሰናል ጋር ያሳለፈው ካዞርላ በጉዳት ምክንያት ከ2016 ወዲህ ለክለቡ ተሰልፎ አልተጫወተም፡፡ ኮንትራቱም በመጠናቀቁ ምክንያት አርሰናሎች ሊለቁት ወስነዋል፡፡ ካዞርላም ወደ ቪያሪያል ሊያመራ ይችላል፡፡ ካዞርላ ለቪያሪያል ከ2007-2011 ተጫውቶ ነበር፡፡ አሁን ለቅድመ ልምምድ ወደክለቡ ይመለሳል፡፡ ይሁንና ስለቀረበለት ኮንትራት ምንም የተባለ ነገር የለም፡፡ (Goal)


ፔሌግሪኒ የዌስትሃም አሰልጣኝ ለመሆን ተስማሙ፡፡ ቺሊያዊው የቀድሞ የማንችስተር ሲቲ አሰልጣኝ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የቻይናውን ሄቤ ፎርቹን በማሰልጠን ላይ ነበሩ፡፡ አሁን ከክለቡ ጋር የተለያዩ ሲሆን ወደ አሰልጣኝነት የመመለስ ፍላጎትም አላቸው፡፡ ወደ ለንደን አቅንተው ከዌስትሃም ባለቤት ዴቪድ ሱሊቫን ጋር ተነጋግረዋል፡፡ (Telegraph)


ባርሴሎናዎች የቶተንሃሙን ወጣት ቲዮ ግሪፊት ለማስፈረም ተስፋ ሰንቀዋል፡፡ በሌላ ቶተንሃሞችም የባርሴሎናውን ሪካርድ ፒዩጅ ለማስፈረም ተስፋ አድርገዋል፡፡ ባርሴሎናዎችም በድር በምድር ያሉ ይመስላል የ18 አመቱን የቶተንሃም ወጣት ለመውስድ ተዘጋጅተዋል፡፡  (Daily Star)



ሊቨርፑሎች ሁለት ተከላካዮች ላይ አነጣጥረዋል፡፡ በ75 ሚ. ፓውንድ ቨርጂል ቫንዳይክን ከሳውዛምፕተን ያስፈረሙት ሊቨርፑሎች አሁንም የተከላካይ መስመራቸውን ማጠናከር ይፈልጋሉ፡፡ የኒውካስትሉ ጀማል ላሰል እና የበርንሌው ጀምስ ትራኮወስኪ የሚለጉ ተጫዋቾች ናቸው፡፡ (Independent)


ጆሴ በተሰናባቹ ምክትል አሰልጣኝ ሩዪ ፋሪያ ቦታ ኬረን ማክኬናን ሹሟል፡፡ ማክኬና የዩናይትድ ከ18 አመት በታች አሰልጣኝ ሲሆን፣ ባለፈው አመት ነበር ከቶተንሃም ወደ ማንችስተር የተቀላቀለው፡፡ ያሰልጥነው የነበረው የ18 አመት በታች ቡድንም የሰሜን ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አሸንፏል፡፡
(ምንጭ፡ Sky Sports News)

ዌስትሃም ዩናይትድ ማኑዌል ፔሌግሪኒን አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ። ፔሌግሪኒ የ3 አመት ኮንትራትም ከለንደኑ ክለብ ጋር ተፈራርመዋል:: ማኑዌል ፔሌግሪኒ ከዚህ በፊት ከማንችስተር ሲቲ ጋር ቻምፒየን ሆነው ነበር፡፡


አርሰናል በቀጣይ የውድድር አመት ለብሶ የሚጫወትበትን ማለያ ይፋ አድርጓል፡፡ ቁጥራቸው የተቀየረላቸው ተጫዋቾችም አሉ፡፡

ፒተር ቼክ 1 ቁጥር፣
ቤሌሪን 2፣
ሙሀመድ ኤልኔኒ 4፤
ግራኒት ዣካ ደግሞ 34 ቁጥር ይለብሳሉ፡፡


═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════

Monday, May 21, 2018

ሰኞ ከሰአት በኃላ ላይ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና ሌሎች መረጃዎች



ፔፕ ጓርዲዮላ ኤዲን ሃዛርድን በክረምት ማስፈረም ይፈልጋል፡፡ የማንችስተር ሲቲው አሰልጣኝ በክረምት ማስፈረም ከሚፈለጋቸው ተጫዋቾች ውስጥ ሃዛርድን ተቀዳሚ ምርጫው አድርጓል፡፡ ሲቲዎች በከፍተኛ ሁኔታ ሪከርዶችን እየሰባበሩ ሻምፒየን ቢሆኑም አሁንም ቡድናቸውን ማጠናከር ይፈልጋሉ፡፡ ይሁንና ሃዛርድን በርካሽ ዋጋ አያገኝቱም፡፡ በትንሹ 100 ሚ. ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ እና 300 ሺህ ፓውንድ ሳምንታዊ ደሞዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ (Daily Star)



የቶተንሃም ሆትስፐሩ ተከላካይ ቶቢ አልደርዊረልድ በማንችስተር ዩናይትድ ከሚፈልጉ ተጫዋቾች ውስጥ የመጀመሪያው ሆኗል፡፡ ጆሴ ሞሪንሆ በኦልትራፎርድ ያደረጉት የ2ኛው አመት ቆይታ ያለዋንጫ ተጠናቋል፡፡ ማንችስተር ዩናይትድም ለሞሪኒሆ 250 ሚ. ፓውንድ ለዝውውር ለመስጠት ወስኗል፡፡ በዚህም ሞሪንሆ የናፖሊውን ጆርጊንሆ፣ የሻክታሩን ፍሬድ እንዲሁም የኒሱን ጄን ማይክል ሴሪ ለማስፈረም እንደሚንቀሳቀሱ ይጠበቃል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ አንቶኒ ማርሲያል፣ ሉክ ሾው፣ ዴሊ ብሊንድ እና ማቲዮ ዳርሚያን ኦልትራፎርድን በመልቀቅ ወደ ሌላ ክለብ ሊያቀኑ ይችላሉ፡፡ (Mirror)



ተሰናባቹ የፒኤስጂ አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሪ የአርቴታ ተፎካካሪ ሆኖ ብቅ ብሏል፡፡ የቀድሞው የአርሰናል አማካይ ሚኬል አርቴታ የአርሰናል አሰልጣኝ የመሆን እድሉ ሰፊ መሆኑን ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ሲዘገብ ነበር፡፡ ይሁንና እስካሁን ምንም የተፈረመ ስምምነት የለም፡፡ በሲቪያ እና ፒኤስጂ በርካታ ዋንጫዎችን ማሳካት የቻለው ኡናይ ኤምሪ ዋንጫ ለተጠማው አርሰናል መፍትሄ ሊሆን ይችላል የሚሉ የአርሰናል የቦርድ አባላት መኖራቸው ለአርቴታ እንቅፋት ሊሆን ይችላል፡፡ (Daily Mail)



ሮማዎች የአያክሱን ጀስቲን ክላይቨርት ለማስፈረም የሚደረገውን ፉክክር በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ክላይቨርት ከአያክስ የቀረበለትን አዲስ ኮንትራት አልፈርምም በማለቱ ክለቡ ሊሸጠው እንደሚገደድ ታውቋል፡፡ በርካታ ክለቦች ልጁን ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ የልጁ ማረፊያ ሊሆን ይችላል ቢባልም ሮማዎች ገፍተው በመሄድ ልጁን በእጃቸው ለማስገባት ጥረት ባመድረግ ላይ ናቸው፡፡ (France Football)

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════

ፖግባ ወደፊት ለፒኤስጂ መጫወት እንደሚችል አስታወቀ፡፡ በዚህ የወድድር አመት ከአጋማሽ በኋላ በአብዛኛው ጨዋዎች ወደ ተቀያሪ ወንበር የወረደው ፖግባ ማንችስተርን ሊለቅ ይችላል የሚሉ ዘገባዎች እንዲወጡ አድርጎ ነበር፡፡ ይሁንና እሱ በማንችስተር መቆየት እንደሚፈልግ አስታውቋል፡፡ በቅርቡ ደግሞ ፓሪስ ውስጥ በተደረገ የፎቶ ስነስርዓት ላይም ተገኝቶ ነበር፡፡ ከካናል ፕላስ ለቀረበለት ጥያቄም ለፎቶ ፕሮግራም ፓሪስ መገኘቱ ከዝውውር ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው ከገለፀ በኋላ አንድ ቀን በParc des france ለምን አልጫወትም; ውብ ስታዲየም ነው ሲሉ ወደፊት ሊዘዋወር እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል፡፡ (Goal)



ኤቨርተኖች የቀድሞውን የዋትፎርድ አሰልጣኝ ማርኮ ሲልቫ እንደሚቀጥረት ተስፋ አድርጓል፡፡ ኤቨርተኖች በጥር ወር ሲልቫን ለማዘዋወር በመንቀሳቀሳቸው ዋትፎርዶች ጉዳዩን ለፕሪሚየር ሊጉ ከሰው ነበር፡፡ ዋትፎርዶች በኋላ ሲልቫን ከአሰልጣኝነት አባረውትም ነበር፡፡ የኤቨርተኑ ባለቤት ፋርሃድ ሞሺሪ ሲልቫን ከማስፈረማቸው በፊት የክሱ ጉዳይ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ይፈልጋሉ፡፡ (Daily Mail)



ባየርሙኒኮች የቫሌንሺያውን አጥቂ ሮድሪጎ ሞሬኖ ለማስፈረም የሚደረገውን ፉክክር በመምራት ላይ ይገኛል፡፡ በ2017/18 ለቫሌንሺያ 19 ጎሎችን ያስቆጠረው የ27 አመቱ ሮድሪጎ በብርካታ አውሮፓ ክለቦች በመፈለግ ላይ ይገኛል፡፡ ባየር ሙኒክም እንዚህን ክለቦች በመምራት ላይ ይገኛል፡፡ ሙኒኮች አጥቂውን ላመስፈረም ከቫሌንሺያ ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል፡፡ ሮድሪጎም በ60 ሚ. ዩሮ ወደ ጀርመን ሊዘዋወር ይችላል፡፡ (Marca)



የቀድሞው የማንችስተር ሲቲ አሰልጣኝ ማኑዌል ፔሌግሪኒ አዲሱ የዌስትሃም አሰልጣኝ ለመሆን ተቃርበዋል፡፡ ዌስትሃሞች የኒውካስትሉን ራፋ ቤኒቴዝ ለመቅጠር ፈልገው ነበር፡፡ ይሁንና የኒውካስትሉ ባለቤት ማይክ አሽሊ ለዝውውር ብዙ ገንዘብ እንደሚመድብ ቃል ከገባ በኋላ ቤኒቴዝ እዛው ለመቆት ወስነዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ዌስትሃሞች የአሁኑን የሄቤ ቻይና ፎርቹን አሰልጣኝ ለመቅጠር ተቃርቧል፡፡ (Mirror)



የናፖሊው ሊቀመንበር ኦውሪሊዮ ዴ ላውሬንቲስ አሰልጣኛቸው ማውሪዚዮ ሳሪ ክለባቸውን ሊለቁ እንደሚችሉ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ላውረንቲስ እንደተናገሩት ከሆነ ሳሪን አዲስ ኮንትራት ለማስፈረም ያደረጉት ጥረት እንዳለተሳካ እና ጊዜ እያለቀባቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ሳሪ ቸልሲዎች ኮንቴን የሚያባሩ ከሆነ የሳቸውን ቦታ እንደሚተኩ ይጠበቃል፡፡ (Goal)



የአርሰናሉ አማካይ ጃክ ዊልሸር የቀረበለትን የ3 አመት ኮንትራት በመፈራረም በክለቡ እንደሚቆይ አስታውቋል፡፡ ዊልሸር ኮንትራቱ በዚህ አመት የሚናቀቅ ሲሆን ኤቨርተን እና ዌልቭስ ልጁን ማስፈረም ይፈልጉ ነበር፡፡ (Mirror)

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════

Saturday, May 19, 2018

ቅዳሜ ከሰአት በኃላ ላይ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና ሌሎችም መረጃዎች



ባየር ሙኒክ የባየርሊቨርኩሰኑን ሊዮን ቤይሊ ለማስፈረም እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ ሙኒኮች ጃማካዊውን የክንፍ ተጫዋች በ60 ሚ. ዩሮ ነው ማስፈረም የሚፈልጉት፡፡ ባየር ሊቨርኩሰኖች ደግሞ እስከ 100 ሚ ዩሮ ለተጫዋቹ ይፈልጋሉ፡፡ ሙኒክ ያን ያህል ገንዘብ የማይከፍል ከሆነ ለነሱ ከመሸጥ ይልቅ ለሪያል ማድሪድ መሸጥ ይፈልጋሉ፡፡ (ESPN)



ተሰናባቹ የዌስትሃም አሰልጣኝ ዴቪድ ሞየስ የስቶክ ሲቲ አሰልጣኝ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከፕሪሚየር ሊጉ የተናበቱት እና ፖል ላምበርትን ያሰናበቱት ስቶኮች አሁን ፊታቸውን ወደ ሞየስ አዙረዋል፡፡ ሞየስ በአሁኑ ሰዓት ምንም ስራ የሌላቸው ሲሆን ስቶክን በፍጥነት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ እንዲመልሱ ይፈለጋሉ፡፡ (Mirror)



የጆኒ ኢቫንስ ወኪል ለጆኒ ኢቫንስ ዝውውር ከሚለፈለው ገንዘብ በላይ ይፈልጋል፡፡ የቀድሞው የማነችስተር ዩናይትድ ተከላካይ ኢቫንስ ክለቡ ዌስት ብሮም ወደ ታች መውረዱን ተከትሎ ወደ ሌላ ክለብ የመሄድ መብት አለው፡፡ እሱን መግዛት የሚፈልግ ክለብም 3 ሚ. ፓውንድ የውል ማፍረሻ መክፈል ይኖርበታል፡፡ ሌዚስተር ሲቲዎች ይህን 3 ሚ. ፓውንድ በመክፈል ልጁን ለመውሰድ ዝግጁ ናቸው፡፡ ይሁንና ወኪሉ ደግሞ 4 ሚ. ፓውንድ ካልተከፈለኝ ማለቱ ዝውውሩን እንዲስቶጓገል አድርጓል፡፡ (Daily Mail)


═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════


ጆይ ሃርት በፕሪሚየር ሊጉ የሚያቆየውን እድል ሊያገኝ ነው፡፡ የማንችስተር ሲቲው ግብ ጠባቂ በወሰት  ወደ ጣሊያኑ ቶሪኖ ከዚያም ወደ ዌስትሃም አቅንቶ ነበር፡፡ ወደ ማንችስተር ሲቲ ተመልሶ የመሰለፍ እድል ማግኘቱ አጠራጣሪ ነው፡፡ ዌስትሃሞችም ቢሆኑ ልጁን በቋሚነት ማስፈረም አይፈልጉም፡፡ በዚህም ምክንያት ሁለት የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ለጆይ ሃርት እድል ሊሰጡት አቅደዋል፡፡ ክለቦቹም ሳውዛምፕተን እና አዲስ አዳጊው ወልቨርሃምፕተን ናቸው፡፡ (Mirror)



ሳውዛምፕተኖች የተከላካይ ክፈላቸውን ለማጠናከር ሁለት ተጫዋቾች ላይ አነጣጥረዋል፡፡ ባለፈው ጥር ቨርጂል ቫን ዳይክን ለሊቨርፑል የሸጡት ሳውዛምፕተኖች የሚድልስብሮውን ሜል ጊብሰን እና የስዋንዚ ሲቲውን አልፊ መውሰን ለማዘዋወር እቅድ አላቸው፡፡   (The Sun)



አንድሬስ ኢኒየስታ የሚኬል አርቴታ ተተኪ እንዲሆን ይፈለጋል፡፡ ሚኬል አርቴታ የአርሰናል አሰልጣኝ ለመሆን በድርድር ላይ የሚገኝ ሲሆን በሱ ቦታ ደግሞ ሲቲዎች ለኢኒየስታ የተጨዋች እና አሰልጣኝነት እድል ሊሰጡት አስበዋል፡፡  (Yahoo Sport)



ማንችስተር ሲቲዎች ኤዲን ሃዛርድ ቸልሲን ለመልቀቅ የሚወሰን ከሆነ ወደ ክለባቸው ሊያዘዋውሩት አቅደዋል፡፡ ቸልሲዎች ለቻምፒየንስ ሊግ አለመድረሳቸው እና ክለቡ ተጨዋቾችን ለማስፈረም አለመንቀሳቀሱ የሀዛርድን ልብ ሊያሸፍተው እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የፔፕ ጓርዲዮላው ሲቲ ሀዛርድ ቸልሲን ለመልቀቅ ከወሰነ እስከ 100 ሚ. ፓውንድ ክፍያን ለማቅረብ እና ሳምንታዊ 300 ሺ ፓወንድ ደሞዝ ሊከፍሉትም ዝግጁ መሆናቸው ተዘግቧል፡፡   (The Sun)



ፒኤስጂዎች ከጁቬንቱስ የሚለቀውን ጁዋንሉጂ ቡፎን በነፃ ማዘዋወር ይፈልጋሉ፡፡ ፒኤስጂዎች ለ40 አመቱ ግብ ጠባቂ አመታዊ 8 ሚ ዩሮ ደሞዝ ለመክፈል ዝግጁ ናቸው፡፡ ይህም ጁቬንቱስ ሲያገኝ ከነበረው እጥፍ ይሆናል ማለት ነው፡፡    (Goal)

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════
☞ የኤፌ ካፕ የፍፃሜ ጫዋታ.. ..

ቼልሲ 🆚 ማን. ዩናይትድ

#ምሽት ☞ 1:15
#ቦታው ☞ ዊምብሊይ

☞ ሁለቱ ክለቦች 179 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን ቼልሲ 53 ጊዜ ሲያሸንፍ ዩናይትድ በበኩሉ 77 ጊዜ አሸንፏል ቀሪውን 49 ጊዜ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል::

☞ ማንችስተር ዩናይትድ የዛሬ የኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጫዋታ 20ኛው ሲሆን 12 ጊዜ ዋንጫውን የማንሳት እድል አጋጥሞታል::

☞ ዛሬ ዩናይትድ ዋንጫውን የሚያነሳ ከሆነ በአርሰናል የተያዘውን የኤፌ ካፕ ዋንጫን 13 ጊዜ በማንሳት የአንደኝነት ማዕረግ ይጋራል::

☞ ሮሜሉ ሉካኩና አንቶኒ ማርሺያል ከጉዳታቸው አገግመው ለፍፃሜው ጫዋታ ለመሰለፍ ብቁ ሆነው ተገኝተዋል።

☞ ኤመርሰን በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ከ FA Cup Final ጨዋታ ውጪ ሆኗል።

☞ ኢዲን ሃዛርድ ዛሬ በሰማያዊው የቼልሲ ማልያ 300ኛ ጨዋታውን ያደርጋል።

ያነሳቸው ክብሮች.. .
- Premier League 🏆🏆
- League Cup 🏆
- PFA POTY
- Chelsea's POTY x3


☞ እንደ አንቶኒዮ ኮንቴ እምነት ከሆነ ቼልሲ ዛሬ የኤፍ.ካፕ ዋንጫውን ሊያነሳ እንደሚችል ተናግረው ባነሳው እንኳን ከመሰናበት አልተርፍም የሚል አስተያየትም አክለዋል።

☞ከጆዜ ሞሪንዎ ጋር በስጋሚ ስለመገናኘታቸው ሲጠየቁ ደግሞ ...

"ስለ እርሱ ጋር ስላለኝ ሁኔታ አሁን ማውራቱ ተገቢ አይደለም ወሳኙ ነገር በኔ እና በሱ መሃከል ያለው ግንኙነት ኖርማልና ጤናማ ነው። እጁን እጨብጠዋለው ከዛ በኃላ ማተኩረው ስለ ጨዋታው ብቻ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰትተዋል።

Friday, May 18, 2018

አርብ ምሽት ላይ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና ሌሎችም መረጃዎች



ማንቸስተር ዩናይትዶች ለላዚዮው አማካይ ሰርጂ ሚሊንኮቪች ሳቪች ዝውውር የ€91 ሚሊዮን ዩሮ እና እንደሚያሳየው ብቃት እየታየ የሚጨመር ሂሳብ ለክለቡ ላዚዮ አቀረቡ።  (DRusso deCerame)



አርሰናሎች ሚካኤል አርቴታን አዲሱ የክለባቸው አለቃ አድርገው ለመቅጠር ተቃርበዋል። ማንቸስተር ሲቲዎች የቀድሞው መድፈኛ ኢትሃድን በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚለቅ እና ወደ ቀድሞ ክለቡ እንደሚያመራ እርግጠኞች ሆነዋል።
(Daily Telegraph)


ማንችስተር ሲቲ እና ሊቨርፑል ጂያንሉጂ ቡፎንን ለማስፈረም እየተሽቀዳደሙ ነው፡፡ የ40 አመቱ ቡፎን በውድድር አመቱ መጨረሻ ጁቬንቱስን እንደሚለቅ አስታውቋል፡፡ ነገር ግን ከእግር ኳስ አለሙ አልርቅም ብሏል፡፡ ይህን ተከትሎ ሲቲ እና ሊቨርፑል ዝነኛውን ግብ ጠባቂ የግላቸው ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡ (The Sun)



ማርሲያል ቸልሲዎች ለማስፈረም ከሚፈልጓቸው ተጫዋቾች ውስጥ ቀዳሚው ነው፡፡ የማንችስተር ዩናይትዱ የክንፍ ተጫዋች ማርሲያል በዚህ የውድድር አመት የመሰለፍ እድል በብዛት አላገኘም፡፡ በዚህም ምክንያት ክለቡን ሊለቅ ይችላል የሚሉ በርካታ ዘገባዎች ሲወጡ ከርመዋል፡፡ በዘንድሮ የውድድር አመት ደግሞ ቸልሲዎች በአጥቂው መስመር ላይ ደከም ብለው ነበር፡፡ እሱን ለማጠናከር ፊታቸውን ወደ ማርሲያል አዙረዋል፡፡ የኒሱ አማካይ ጄን ማይክል ሴሪም በቸልሲ ከሚፈለጉ ተጫዋቾች ውስጥ ይገኛል፡፡ (Daily Mail)



 ጓርዲዮላ ምክትሉ ሚኬል አርቴታ ከአርሰናል ጋር እንዲነጋገር ፍቃድ ሰጥቶታል፡፡ የአርሰናሉ ሊቀመንበር አይቫን ጋዚዲስ የቀድሞ አማካያቸው ሚኬል አርቴታን አሰልጣኝ አድርጎ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ አርቴታም ከጓርዲዮላ ጋር ተገናኝቶ ስለጉዳዩ ያወራ ሲሆን፡፡ ጓርዲዮላ እና የማንችስተር ሲቲው ፉትቦል ዳይሬክተር ቤጂርስቴየን ፍላጎቱን እንሚቀበሉ ነግረውታል፡፡  (Sport)



ሮማዎች ሪያል ማድሪድ ለግብ ጠባቂያቸው ያቀረበውን ክፍያ ውድቅ አደረጉ፡፡ ማድሪዶች ግብ ጠባቂ ለማስፈረም እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ የሮማው አሊሰን ደግሞ ተቀዳሚ ምርጫቸው ሆኗል፡፡ ሮማዎች ግብ ጠባቂያቸውን መልቀቅ አይፈልጉም፡፡ ይሁንና ገፍቶ የሚመጣ ክለብ ካለ ደግሞ ከ100 ሚ. ዩሮ በላይ ይዞ መምጣት ይኖርበታል፡፡ ለአሁኑ ማድሪድ ከዛ ያነሰ ሂሳብ እንዳቀረበ ተዘግቧል፡፡ (Corrierre dello Sport)



አርሰናሎች ራምሴን ለመሸጥ ተዘጋጅተዋል፡፡ የአርሰናሉ አማካይ አሮን ሳምሴይ አዲስ ኮንትራት ከክለቡ ጋር የማይፈራረም ከሆነ ክለቡ ሊሸጠው ይገደዳል፡፡ የ27 አመቱ አማካይ ከንትራት በቀጣዩ ክረምት ነው የሚጠናቀቀው፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ቸልሲ እና ጁቬንቱስ ደግሞ ልጁን ይፈልጉታል፡፡ አርሰናሎችም ልጁን ማስፈረም እና በክለባቸው ማቆት ይፈልጋሉ፡፡ ይሁንና አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ካልተሰማማ ሊሸጡት ይችላሉ፡፡ (The Sun)



ሲሚዮኔ አጥቂው ግሪዝማንን ለመተካት የጁቬንቱሱን ፓብሎ ዲባላ ይፈልጋል፡፡ ግሪዝማን ወደ ባርሴሎና ይሄዳል የሚሉ ዘገባዎች እና እንደውም ተስማምቷል የሚሉ ዘገባዎች ባለፈው ሳምንት ሲወጡ ከርመዋል፡፡ ይህን ለመተካት ደግሞ አትሌቲኮዎች የጁቬንቱሱን ዲባላ ማምጣት ይፈልጋሉ፡፡ (Don Balon)



አርሰናሎች ቲየሪ ሄንሪን ማነጋገር ይፈልጋሉ፡፡ አርሰናሎች አርሰን ቬንገር ክለቡን ከለቀቁ በኋላ አሰልጣኝ በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ ሄንሪን ማነጋገር ይፈልጋሉ፡፡ ይሁንና አርቴታ የአርሰናል አሰልጣኝ የመሆን እድሉ ሰፊ ነው፡፡  (Sky Sports News)

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════

ሪያል ቤቲሶች የኒውካስትሉን ተጫዋች አዮዜ ፔሬዝ ማስፈረም ይፈልጋሉ፡፡ ቤቲሶች በቀጣዩ አመት በዩሮፓ ሊግ ለመሳተፍ በመዘጋጀት ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህ ውድድር ላይ ጠናካራ ሆነው ለመቅረብ ደግሞ ቡድናቸውን ለማጠናከር እንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡፡ ቡድናችንን ያጠናክርልናል ያሉት አንዱ ደግሞ የኒውካስትሉ አዮዜ ፔሬዝ ነው፡፡ (Mundo Deportivo)



ጀስቲን ክላይቨርት ከአያክስ የቀረበለትን ኮንትራት ውድቅ አደረገ፡፡ የ19 አመቱ ወጣት አጥቂ ስሙ በከፍተኛ ሁኔታ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ሲያያዝ ከርሟል፡፡ ኮንትራቱ በቀጣዩ አመት የሚጠናቀቅ ሲሆን አያክሶች ሊያስፈርሙት ይፈልጋሉ፡፡ ይሁንና ኮንትራቱን የማያራዝም ከሆነ ሊሸጡት ይገደዳሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ዩናይትድ የማቅናት እድሉ ሰፊ ይሆናል፡፡ (Goal)



 ፔፕ ጓርዲዮላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር አዲስ ኮንትራት ተፈራረመ፡፡ በዘንድሮው የውድድር አመት የእንግሊዝ ቻምፒን የሆነው አሰልጣኝ ከማንችስተር ሲቲ ጋር እስከ 2021 የሚቆየውን ኮንትራት ተፈራርሟል፡፡ (Goal)



ሴልቲኮች ተከላካያቸውን ኬረን ቲርኔይ ለመሸጥ 30 ሚ. ፓውንድ ይፈልጋሉ፡፡ የ20 አመቱ ስኮትላንዳዊ የግራ ተመላላሽ ምርጥ ብቃት ካላቸው ተጫዋቾች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ቶተንሃም እና አትሌቲኮ ልጁን ይፈልጉታል፡፡ ሴልቲኮችም ልጁን በክለባቸው ለማቆየት የረጅም ጊዜ ኮንትራት አስፈርመውታል፡፡ ነገር ግን እንዚህ ክለቦች ገፍተው የሚመጡ ከሆነ በትንሹ ለልጁ 30 ሚ. ፓውንድ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ፡፡  (Daily Mail)

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════

Thursday, May 17, 2018

ሃሙስ ምሽት ላይ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና መረጃዎች


1. የሲቪያው ተከላካይ ክሌመንት ሌንገልት ወደ ባርሴሎና ለመዘዋወር ተስማማ ሲል Mundo Deportivo  ዘግቧል፡፡ አሁን የሚቀረው ሁለቱ ክለቦች የሚያደርጉት ስምምነት ነው፡፡ ከዚያም የ22 አመቱ ፈረንሳዊው ተከላካይ የ5 አመት ኮንትራት ከካታላኑ ክለብ ጋር ይፈራረማል፡፡



2. ማንችስተር ዩናይትድ እና ባየር ሙኒክ የኤሲ ሚላኑን ተከላካይ ሊዖናርዶ ቦኑቺ ይፈልጋሉ፡፡ ቦኑቺ ባለፈው አመት ነበር ከጁቬንቱስ ወደ ኤሲ ሚላን የተዘዋወረው፡፡ ይሁንና ኤሲ ሚላን በዚህ የውድድር አመት ለቻምፒየንስ ሊግ አለማለፉ እሱን ጨምሮ በርካታ ተጨዋቾች ለመሸጥ ይገደዳል፡፡ ዩናይትድ እና ሙኒክም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ተከላካዩን ወደ ክለባቸው ለማምጣት ይንቀሳቀሳሉ ሲል Sun ዘግቧል፡፡



3. አርሰናል ሶዩንኮ ስለተወደደበት ፊቱን ወደ ሶቅራጢስ አዙሯል ሲል  Daily Mail ዘግቧል፡፡ አርሰናሎች በዚህ የዝውውር መስኮት ማስፈረም ከሚፈልጉት ተጫዋቾች ውስጥ የተከላካይ መስመር ተጫዋቹ ካግላር ሶዩንኩ አንዱ ነው፡፡ ይሁንና ወጣቱ ቱርካዊውን ለመሸጥ ፍራይበርግ 35 ሚ.ፓውንድ ጠይቋል፡፡ አርሰናሎች ደግሞ ይህ ዋጋ ውድ ነው በማለት ከሶዩንኩ በ8 አመት የሚበልጠውን የቦሩሺያ ዶርትመንድ ተከላካይ ሶቅራጢስ ፓፓስታቶፖሎስ ለማስፈረም አቅደዋል፡፡ ሶቅራጢስ እስከ 17.5 ሚ. ፓውንድ ተገምቷል፡፡



4. ማንችስተር ዩናይትድ ከቸልሲው የክንፍ ተጫዋች ዊሊያን ወኪል ጋር ንግግር ጀምሯል፡፡ የቀድሞ የሻክታር ዶኔትስ ተጫዋች የሆነው ዊሊያን በ2013 ነበር ለቸልሲ የፈረመው፡፡ በወቅቱም ሞሪንሆ የቸልሲ አሰልጣኝ ነበሩ፡፡ ጆሴ ዳግመኛ ከተጫዋቹ ጋር መገናኘት ይፈልጋሉ፡፡ በቀጣዩ ታህሳስ 30 አመት የሚሞላውን ለማምጣት ዩናይትድም ከወኪሉ ጋር ንግግር ላይ ናቸው ሲል Manchester Evening News ዘግቧል፡፡



5. ቶተንሃም ሆትስፐር ለቦሩሺያ ዶርትመንዱን ክርስቲያን ፑሊሲች የሚጠየቀውን ክፍያ ለመክፈል ዝግጁ መሆን Calcio Insider  ዘግቧል፡፡ የ19 አመቱ አሜሪካዊ በዘንድሮ የውድድር አመት ባሳየው ብቃት የበርካታ ክለቦች እይታ መሳብ ችሏል፡፡ እስካሁን ዶርትመንድ የልጁን ሂሳብ ባያስቀምጥም የእንግሊዙ ጋዜጣ Mirror ወጣቱ እስከ 40 ሚ. ፓውንድ ሊሆን ይችላል ሲል ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ዘግቦ ነበር፡፡


═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════


6. ቦሩሺያ ዶርትመንድ የቸልሲውን አጥቂ አልቫሮ ሞራታ ማስፈረም ይፈልጋል ሲል Bild ዘግቧል፡፡ ሞራታ ከሪያል ማድሪድ ወደ ቸልሲ መዘዋወሩ ቢቺ ባትሹዋዪን ወደ ተቀያሪ ወንበር አውርዶታል፡፡ የመሰለፍ እድል ያላገነውን ባትሹዋዪን ደግሞ ዶርትመንዶች ወስደው ሲጠቀሙበት ነበር፡፡ አሁንም ዳግመኛ ወደ ለንደኑ ክለብ በመመለስ አጠቂያቸውን ለመውሰድ ማቀዳቸውን ዘገባው አስነብቧል፡፡



7. ጁቬንቱሶች የባርሳውን ወጣት ለማስፈረም ከጫፍ ደርሷል፡፡ የ16 አመቱ ፓብሎ ሞሬኖ ከባርሴሎና የኮንትራት ማራዘሚያ ቢያቀርቡለትም ውድቅ አድርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ጁቬንቱስ ለመሄድ ተቃርቧል፡፡ ታዳጊውን ማስፈረም የሚፈልጉት ጁቬንቱሶችም የውል ማፍረሻ የሆነውን 3 ሚ. ፓውንድ ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን Sport ዘግቧል፡፡



8. ማንችስተር ዩናይትዶች ከአትሌቲኮ ማድሪዱን የቀኝ ተመላላሽ ሺሜ ቨርሳልኮን ለማስፈረም አቅዷል፡፡ ቨርሳልኮ 30 ሚ. ፓውንድ የተገመተ ሲሆን፣ አትሌቲኮዎችም ቡድናቸውን ለማጠናከር ስለሚፈልጉ ልጁን ለመሸጥ ይፈልጋሉ፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ የቀኝ እና የግራ ተመላላሽ ለማስፈረም ተጫዋች እያፈላለገ ነው፡፡ ቭርሳልኮም ከሚፈልጉ ተጫዋቾች ውስጥ አንዱ ሆኗል፡፡ (Daily Mail)



9. ዌስትሃሞች ራፋ ቤኒቴዝን አሰልጣኝ አድርጎ ለመቀጥር እያሰቡ ይገኛሉ፡፡ ቤኒቴዝ በአነስተኛ በጀት የገነቡት ቡድን 10ኛ ደረጃን ይዞ እዲጨርስ ረድተዋል፡፡ በዚህ ብቃታቸው የተደነቁት ዌስትሃሞችም እሳቸውን ወደ ለንደን እስታዲየም ለማምጣት ይፈልጋሉ፡፡ (Sky Sports News)



10. ሌዚስተር ሲቲ የፖርቶውን የቀኝ ተመላላሽ ሪካርዶ ፔሬራ ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡ የ24 አመቱ ፖርቹጋላዊ በማንችስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃም ሆትስፐር ሲፈለግ ነበር፡፡ ሌዚስተሮች ግን ገፍተው በመሄድ ለጁን በ25 ሚ ፓውንድ ለማስፈረም ተቃርበዋል፡፡ ከሱ በተጨማሪ ሌዚስተሮች የማንችስተር ሲቲውን የክንፍ ተጫዋች እና ባለፉት ሁለት አመታት በሴልቲክ በውሰት ያሳለፈውን ፓትሪክ ሮበርተስ ለማስፈረምም ከጫፍ ደርሰዋል፡፡ (Daily Mail)



11. ዶርትምንድ የጁቬንቱሱን ተከላካይ ማስፈረም አይፈልግም፡፡ የ34 አመቱ ስቴፋን ሌቸንስታይነር 7 አመት የቆየበትን ጁቬንቱስ በመልቀቅ በነፃ ከጁቬንቱስ ይለቃል፡፡ ከዚያም ዶርትመንድን ይቀላቀላል የሚሉ ዘገባዎች ሶወጡ ነበር፡፡ ዶርትመንዶች የኒሱን አሰልጣኝ ሉሲየን ፋቭሬ አሰልጣኝ አድርጎ ቀጥሯል፡፡ አሰልጣኙ ደግሞ ሌቸንስታይነርን የማስፈረም ፍላጎት የለውም፡፡ (Kicker)



12. ኒሶች የቀድሞውን የአርሰናል አማካይ ፓትሪክ ቪየራ ለመቅጠር አቅዷል፡፡ የአሁኑ የኒስ አሰልጣኝ ሊሲየን ፋቭረ በቀጣይ አመት የዶርትመንድ አሰልጣኝ ለመሆን ተስማምቷል፡፡ በዚህም ምክንያት ቪየራን አሰልጣኝ አድርገው ለመቅጠር አስበዋል፡፡ ቪየራ በአሁኑ ሰዓት የኒውየርክ ሲቲ አሰልጣኝ ነው፡፡ Nice-Matin

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════

Wednesday, May 16, 2018

ዕረቡ ከሰአት በኃላ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update



1. ቸልሲዎች የኒሱን አማካይ ጄን ማይክል ሴሪ ለማስፈረም የሚደረገውን ፉክክር እየመሩ ይገኛሉ ሲል Mirror ዘግቧል፡፡ አርሰናል ልጁን ለማስፈረም ከተጫዋቹ ጋር ተነጋግሮ ነበር፡፡ ይሁንና 40 ሚ. ፓውንድ የተገመተውን ኮትዲቯራዊ ተጫዋች የመውሰድ እድል ያለው ቸልሲ ነው ሲል ዘገባው ደምድሟል፡፡



2. የቶተንሃሙ አሰልጣኝ ሞውሪሲዮ ፖቼቲኖ ከቸልሲ የሚደረገውን ማንኛውም እንቅስቃሴ በማቆም እዛው ቶተንሃም ለመቆየት መወሰኑን Daily Star ዘግቧል፡፡ ከኤፍኤ ዋንጫው መጠናቀቅ በኋላ አሰልጣኝ አንቶኒዮ ኮንቴ ቸልሲን እንደሚለቅ ይጠበቃል፡፡ ቸልሲዎች ደግሞ በሱ ቦታ ፖቼቲኖን ለማምጣ አቅደው ነበር፡፡ ይሁንና በቶተንሃም ደስተኛ የሆነው ፖቼቲኖ እዛው ለመቆየት ወስኗል፡፡



3. ኒውካስትል ዩናይትድ ሁለት የቸልሲ ተጫዋቾችን በውሰት መውሰድ ይፈልጋል፡፡ ተጫዋቾቹም ኬኔዲ እና ታሚ አብራሃም ናቸው፡፡ ኬኔዲ በ2017/18 የውድድር አመት በውሰት ከኒውካስትል ጋር የቆየ ሲሆን ለራፋ ቤኒቴዙ ቡድን ምርጥ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል፡፡ በዚህ ደስተኛ የሆኑት ራፋ ልጁን ዳግመኛ ወደ ኒውካስትል ማምጣት ይፈልጋሉ፡፡ ሌላኛው ተጫዋች ደግሞ ለስዋንዚ ሲቲ በውሰት ሲጫወት የነበረው ታሚ አብረሃም ነው፡፡ አብረሃም 8 ጎሎችን ለስዋንዚ ያስቆጠረ ሲሆን፣ ኒውካስትሎች እሱንም በውሰት መውሰድ ይፈልጋሉ፡፡ ዘገባው የteamTalk ነው፡፡



4. ሶዩንኩ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መዘዋወር ይፈልጋል፡፡ ለፍራይበርግ የሚጫወተው የ21 አመቱ ተከላካይ ካግላር ሶዩንኮ በበርካታ የአውሮፓ ክለቦች እየተፈለገ ይገኛል፡፡ አርሰናል፣ ማንችስተር ዩናይትድ እና ማንችስተር ሲቲ ልጁን የሚፈልጉ ክለቦች ናቸው፡፡ አርሰናሎች ቱርካዊውን ተከላካይ ለማስፈረም ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው ሲሆን ወኪሉ ግን ከተለያዩ ክለቦች ጋር እየተነጋገረ መሆኑን Football London ዘግቧል፡፡

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════


5. ኤዲን ሃዛርድ ኮንትራቱን ከማራዘሙ በፊት ክለቡ በዝውውር መስኮቱ የሚደርገውን እንቅስቃሴ ማየት ይፈልጋል ሲል Goal ዘግቧል፡፡ ኤዲን ሀዛርድ ኮንትራቱ በ2020 ነው የሚጠናቀቀው፡፡ ቸልሲዎች ደግሞ ኮንትራቱን ለማራዘም እና በሳምንት እስከ 300 ሺ ፓውንድ ሊከፍሉት አቅደዋል፡፡ ነገር ግን ሀዛርድ ኮንትራቱን ከማራዘሙ በፊት ወደ ክለቡ የሚመጡ ተጫዋቾቸን ማየት እንደሚፈልግ አስታውቋል፡፡ ሀዛርድ  ስለ ወደፊት ሁኔታው ሲጠየቅ ‹‹ምርጥ ተጫዋቾች ወደ ክለቡ እንዲመጡ እፈልጋለው፡፡ ምክንያቱም በቀጣይ አመት ፕሪሚየር ሊጉን ማሸነፍ እፈልጋለሁ›› በሏል፡፡



6. አርሰናል እና ቶተንሃም ሆትስፐር ማሪዮ ሌሚናን ለማስፈረም ተፋጠዋል፡፡ አማካዩ ማሪዮ ሌሚና ባለፈው ክረምት ነበር ከጁቬንቱስ ወደ ሳውዛምፕተን የተዘዋወረው፡፡ ለሳውዛምፕተንም 29 ጨዋታዎችን ማድረግ ችሏል፡፡ የመሃል ሜዳ ክፍላቸውን ማጠናከር የሚፈልጉት ሁለቱ ክለቦች ደግሞ ልጁን ወደ ክለባቸው ለማዘዋወር አቅደዋል፡፡ ኤቨርተን እና ዌስተሃምም ልጁን ይፈልጉታል፡፡ ዘጋበው Footmercato ነው፡፡



7. የሌዚስተር ሲቲው ሃሪ ማጓየር የወደፊት እቅዱን ከአለም ዋንጫው በኋላ እንደሚያስታውቅ ተናግሯል፡፡ የ25 አመቱ ማጓየር ባለፈው ክረምት ወደ ሌዚስተር የተዘዋወረ ሲሆን በመጀመሪያው አመት ምርጥ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል፡፡ ይህም የበርካታ ክለቦች እይታ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ በተለይ ማንችስተር ሲቲ ልጁን ይፈልጋል፡፡ ማጓር ግን ሁሉንም ነገር ከአለም ዋንጫው መጠናቀቅ በኋላ አስታውቃለው ማለቱን Mirror ዘግቧል፡፡



8. ‹‹በየአመቱ 300 ሚ. ፓውንድ ወጪ አናደርግም›› ሲል ፔፕ ጓርዲዮላ ተናገረ፡፡ ሲቲ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ በተለያዩ ተጫዋቾች ላይ ወጪ በማድረግ የፐሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ብዙ ሪከርዶችን በመሰበር አንስቷል፡፡ በተጨማሪም የካራባኦ ካፕ ዋጫንም መውሰድ ችሏል፡፡ ስለወዲፊቱ የተጠየቀው ጓርዲዮላ ‹‹አሁን ቡድናችን ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለው፡፡ ከአንድ ወይም ሁለት ተጫዋች በላይ አናስፈረምም፡፡ በየአመቱ 300 ሚ. ፓውንድ የማውጣት አቅምም የለንም›› ማለቱን Goal ዘግቧል፡፡



9. ሌዚስተር ሲቲ እና ዌስትሃም ዩናይትድ የ21 አመቱን የማንችስተር ሲቲ የክንፍ ተጫዋች ማስፈረም ይፈልጋሉ፡፡ ፓትሪክ ሮበርትስ ባለፉት ሁለት አመታት ለሴልቲክ በውሰት ሲጫወት ከርሟል፡፡ በዚህም ወርም ወደ ሲቲ እንደሚመለስ ይጠበቃል፡፡ ይሁንና የመሰለፍ እድሉ አናሳ በመሆኑ በክለቡ የመቆየቱ ነገር አጠራጣሪ ነው፡፡ ይህን አጋጣሚ በመጠቀምም 15 ሚ. ፓውንድ የተገመተውን ተጫዋች ለመውሰድ ሌዚስተር እና ዌስትሃም ተዘጋጅተዋል ሲል Express ዘግቧል፡፡



10. አትሌቲኮ ማድሪድ የሴልቲኩን ቲርኔይ ለማስፈረም የሚደረገው ፉክክር ተቀላቅሏል፡፡ የ20 አመቱ ወጣት የግራ ተመላላሽ ኬረን ቴርኔይ በዘንድሮው የውድድር አመት ባሳየው ምርጥ ብቃት ምክንያት የበርካታ ክለቦች እይታ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ቶተንሃም እና ቦርንሞዝ ልጁን በመከታተል ላይ ይገኛሉ፡፡ አትሌቲኮ ማድሪድም አሁን ስኮትላንዳዊውን ከሚፈልጉ ክለቦች ውስጥ ሆኗል፡፡ እሁድ እለት ሴልቲክ ከማዘርዌል ጋር የሚደርጉትን የስኮትሽ ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ እንዲመለከቱም መለማዮች ለመላቅ ማቀዳቸውን The Sun ዘግቧል፡፡



11. ማንችስተር ዩናይትድ የኖቲንግሃም ፎረስቱን ታዳጊ ማቲው ቦንድስዌል ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡ የ16 አመቱ ተመላላሽ በኖቲንግሃም ፎረስት እንዲቆይ ኮንትራት ቢቀርብለትም አልተቀበለውም፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ሊሄድ ይችላል ሲል Daily Mail ዘግቧል፡፡



12. አልፊ መውሰን እና ፋቢያንስኪ ስዋንዚ ሲቲን ሊለቁ ይችላሉ፡፡ ስዋንዚ ወደ ቻምፒየን ሺፑ መውረዱን ተከትሎ በርካታ ተጫዋቾች ክልቡን ሊለቁ ይችላሉ፡፡ ከነዛ ውስጥ ተከላካዩ አልፊ መውሰን እና ግብ ጠባቂው ፋቢያንስኪ ይገኙበታል፡፡ 20 ሚ. ፓውንድ የተገመተውን መውሰን በዌስትሃም እና ሳውዛምፕተን የሚፈለግ ሲሆን፤ ዋትፎርድ፣ ኒውካስትል፣ ክሪታል ፓላስ እና ዌስተሃም የፋቢያንስኪን ሁኔታ በመከታተል ላይ ይገኛሉ፡፡ ዘገባው የThe Guardian ነው፡፡

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════

Tuesday, May 15, 2018

ማክሰኞ ከሰአት በኃላ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና መረጃዎችን ያንብቡ



1. ፔግ ጓርዲዮላ ከቶኒ ክሩስ ጋር ዳግመኛ መገናኘት ይፈልጋል ሲል Don Balon አስነብቧል፡፡ ማንችስተር ዩናይትዶች ለረጅም ጊዜ ክሩስን ወደ ኦልትራፎርድ ለማዘዋወር ሲፈልጉ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ማንችስተር ሲቲዎች እጃቸውን ለማስገባት እየሞከሩ ነው፡፡ ጓርዲዮላ እና ክሩስ በባየር ሙኒክ አብረው ሰርተው ነበር፡፡



2. ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ አምስተ ተጫዋቾችን መሸጥ ይፈልጋል፡፡ የቶተንሃሙ አሰልጣኝ የቡድኑ መሪ ዳኒ ሌቪ የደሞዝ መዋቅሩን በማስቀተካከል ኮከብ ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ እንዲያመጣለት ይፈልጋል፡፡ በከፍተኛ ገንዘብ ተጫዋቾችን ለማስፈረም ደግሞ ቡድኑ ውስጥ ያሉትን አምስት ተጫዋቾች ለመሸኘት ወስኗል፡፡ ቶቢ አልደርዌልድ፣ ዳኒ ሮዝ፣ ሙሳ ዴምቤሌ፣ ፈርናንዶ ሎሬንቴ እና ሙሳ ሲሶኮ እንደሸጡ የተወሰነባቸው አምስት ተጫዋቾች መሆናቸውን Mirror ዘግቧል፡፡



3. ቸልሲዎች አንቶኒዮ ኮንቴን የሚያባርሩት ከሆን እሱን ጨምሮ ለዘጠኝ ስታፎች የውል ማፍረሻ ካሳ ለመክፈል ይገደዳሉ፡፡ ቸልሲ ከአንቶኒዮ ኮንቴ ጋር ለመለያየት ካሰቡ የኮንቴን የአንድ አመት ደሞዝ ለመክፈል ይገደዳሉ፡፡ ነገረ ግን ክፍያው እዛ ጋ አያበቃም፡፡ አንቶኒዮ ኮንቴ ከጣሊያን ያመጧቸው ሌላ 8 ረዳቶቹም ይከፈላቸዋል፡፡ ይህ ደግሞ በቻምፒየንስ ሊጉ መሳተፍ ያልቻለው እና እስከ 50 ሚ. ፓውንድ ገቢ ላጣው ቸልሲ ትልቅ ራስ ምታት መሆኑን Daily Mail ዘግቧል፡፡



4. ፔፕ ጓርዲዮላ የቡዱኑ አካላት የዊልፍድ ዛሃን ሁኔታ እንዲከታተሉ ጠየቀ፡፡ ዛሃ ባለፈው እሁድ ለጋዜጠኞች በሰጠው መልስ ‹‹እኔ ቤቴ ነው ያለሁት ከቤቴ ደግሚ የትም መሄደ አልፈልግ›› ብሏል፡፡ ይሁንና ዛሃ ሀሳቡን የሚቀይር ከሆነ ጓርዲዮላ 50 ሚ. ፓውንድ በመክፈል ልጁን ወደ ኢቲሃድ ማዘዋወር ይፈልጋል ሲል Daily Star ዘግቧል፡፡



5. ቸልሲዎች የቶተንሃሙን አሰልየጣኝ ፖቸቲኖ ይፈልጋሉ ሲል Sun ዘግቧል፡፡ የቶተንሃሙ አሰልጣኝ ሞሪሲዮ ፖቼቲኖ እና የቡደኑ መሪ ዳኒ ሌቪ በዝውውር ጉዳይ ላይ ቅሬታ ውስጥ ገብተዋል፡፡ ፖቼቲኖ ተጫዋቾች እዲገዙለት ይፈልጋል፡፡ ሌቪ ግን እስካሁን ምላሽ አልሰጠውም፡፡ ይህ የማይሳካ ከሆነ ደግሞ ክለቡ ለመልቀቅ ይገደዳል፡፡ ቸልሲል ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ፖቸቲኖን ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ ለማምጣት አቅዷል፡፡

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/hair_regrowth
═════════════════════════

6. የፕሪሚየር ሊጉ የዝውውር መስኮት ከተለመደው ቀን ቀደም ብሎ ሊከፈት ነው፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ የዝውውር መስኮት ከዚህ በፊት ጁን 1  ነበር የሚከፈተው፡፡ ይህ የዝውውር መስኮት ደግሞ የሚዘጋው ኦገስት 31 ነው፡፡ ይህም ማለት ፕሪሚየር ሊጉ ከተጀመረ በኋላ ነው የሚሆን፡፡ ይሁንና በዚህ የዝውውር አመት የዝውውር መስኮቱን ፕሪሚየር ሊጉ ከመጀመሩ በፊት ኦገስት 9 ለይ ለመዝጋት ወስነዋል፡፡ ስለዚህ አስቀድሞው ለመከፍት በመሰናቸው ከቀጣዩ ሀሙስ ሜይ 17 ጀምሮ የዝውውር መስኮቱ በእንግሊዝ ክፍት ይሆናል፡፡ (Sky Sports News)



7. ቦካ ጁኒየርሶች ዴቪድ ኦስፒናን የፍልጉታል፡፡ አርሰናሎች በዚህ የዝውውር መስኮት ግብ ጠባቂ ለማስፈረም እንደሚንቀሳቀሱ ይጠበቃል፡፡ የባየር ሊቨርኩሰኑ ቤርንድ ሌኖን ጨምሮ በርካታ ግብ ጠባቂዎች ስማቸው ከአርሰናል ጋር በመያያዝ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም ምክንያት የኦስፒና በአርሰናል የመቆየት ጉዳይ አጠራጣሪ እየሆነ ነው፡፡ ቦካዎችም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ኮሎምቢያዊውን ግብ ጠባቂ ወደ አርጀንቲና ማምጣት ይፈልጋሉ፡፡ ዘገባው የSun ነው፡፡



8. ዌስትሃም ዩናይትዶች ከሻክታር ዶኔትስኩ አሰልጣኝ ፓውሎ ፌንሴካ ጋር ተነጋግረዋል ሲል Daily Mail አስነብቧል፡፡ የፎንሴካ ወኪል የሆነው ሆርጌ ሜንዴዝ ሰኞ እለት ከዌስትሃሙ ሊቀምነበር ዴቪድ ሱሊቫን ጋር Essex በሚገኘው ቤቱ በመገናኘት ተነጋግሯል፡፡ ዌስትሃሞች ከፎንሴካ በተጨማሪ የቀድሞውን የማንችስተር ሲቲ አሰልጣኝ ማኑዌል ፔሌግሪኒንም ይፈልጋሉ፡፡ ይሁንና ፎንሴካ ወጣት በመሆኑ ወደሱ ማድላታቸውን ዘገባው አክሎ አስፍሯል፡፡



9. የኤቨርተኑ አሰልጣኝ ሳም አላርዳይስ በ48 ሰዓታት ውስጥ ከአሰልጣኝነት ሊባረሩ ይችላሉ፡፡ በኤቨርተን ከፍተኛ ሼር ያለው ባለሀብቱ ፈርሃድ ሞሺሪ ከአላርዳይስ ጋር በመገናኘት ከስራ መባረሩን ይነግረዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በቦታው ደግሞ ከዋትፎርድ የተባረረው ሲልቫ እንደሚመጣ ይጠበቃል፡፡ የኤቨርተን ደጋፊዎች በአላርዳይስ የጨዋታ ዘይቤ ደስተኛ አለመሆናቸው እና ተቃውሞ ማሰማታቸው ለመባረራቸው ምክንያት እንደሆነ The Guardian አስነብቧል፡፡



10. ማንችስተር ዩናይትዶች ለናፖሊው የቀኝ ተመላላሽ ኤልሰዒድ ሀይሳጅ የውል ማፍረሻ የሆነውን 44 ሚ. ፓውንድ ለመክፈል መዘጋጀታቸውን Sun ዘግቧል፡፡ ዩናይትዶች በዚህ የዝውውር መስኮት የቀኝ እና የግራ ተመላላሽ የማስፈረም ፍላጎት አላቸው፡፡ አልባኒያዊው የ24 አመት ተጨዋችም ይሆን ቦታ እንዲሸፍን ወደ ኦልትፎረድ ይመጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ተጫዋቹ የሚፈርም ከሆነ 7ኛው ወዱ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ይሆናል፡፡

═════════════════════════
📂  ADVERTISEMENTS

የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ:
➧ https://t.me/ethio_bodybuilders
═════════════════════════

Sunday, May 13, 2018

እሁድ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update



 ጁቬንትሶች ሞራታን በድጋሜ ማስፈረም ይፈልጋሉ፡፡ ሞራታ ከዚህ በፊት ለጁቬንቱስ ለሁለት አመት ተጫውቶ ነበር፡፡ ከዚያም በውሉ መሰረት ለሪያል ማድሪድ ተሽጧል፡፡ ከአንድ አመት በኋላ ደግሞ ማድሪድ ሞራታን ለቸልሲ ሸጠው፡፡ አሁን በቸልሲ ቤት የተሳካ ጊዜን እያሳላፈ የማይገኘውን ሞራታ መልሰው ወደ ቱሪን ማምጣት ይፈልጋሉ ሲል Sky Sports ሰግቧል፡፡



ማንችስተር ዩናይትዶች ኔይማርን ይፈልጉታል ሲል Mirror ዘግቧል፡፡ ብራዚላዊው ኔይማር በከፍተኛ ገንዘብ ወደ ፒኤስጂ ከተዘዋወር በኋላ ምርጥ ጊዜ አሳልፎ ነበር፡፡ ይሁንና እግሩ ላይ የደረሰው ጉዳት ለ2 ወር ያህል ከሜዳ አርቆታል፡፡ ኔይማር ወደ ሪያል ማድሪድ ሊያቀና ይችላል የሚሉ በርካታ ዜናዎች ሲወጡም ከርመዋል፡፡ አሁን ደግሞ ዩናይትዶች ማድሪድን በመርታት ልጁን ማስፈረም ይፈልጋሉ፡፡ ዩናይትዶች 200 ሚ. ፓውንድ ለመክፈልም ዝግጁ ናቸው፡፡



ኡናይ ኤምሬ የአርሰናል አሰልጣኝ የመሆን እድል አለው ሲሉ Daily እና Sunday Express ዘገቡ፡፡ ተሰናባቹ የፒኤስጂ አሰልጣኝ ተሰናባቹን የአርሰናል አሰልጣኝ የመተካት እድል አላቸው ሲሉም አስነብበዋል፡፡ የአርሰናል አሰልጣኝ የመሆን እድል አላቸው የተባሉት ማሲሚሊያኖ አሌግሪ እና ሊዊስ ኤንሪኬ ቡድኑ ውስጥ ያለውን አስተዳደራዊ መዋቀር አለመፈለጋቸው እንዲሁም ኤንሪኬ ከፍተኛ ደሞዝ መጠየቁ ከእጩነት ሊያርቃቸው እንደሚችልም በተጨማሪ አስፈረዋል፡፡ ሁለት አመት በፒኤስጂ የቆዩት ኤምሬ በዌስትሃም ዩናይትድም የሚፈለጉ አሰልጣኝ ናቸው፡፡





ፉልሃም የሴሰይኖንን ዋጋ ከፍ አደረገ፡፡ Sun ይዞት በወጣው ዘገባ መሰረት የተፈላጊው ወጣት ረያን ሴሴይኖን ዋጋ ወደ 100 ሚ. ፓውንድ ከፍ ብሏል፡፡ ፉልሃሞች ሴሰይኖንን የእንግሊዝ ወዱ ተጫዋች የማድረግ ፍላጎት አላቸው፡፡ ይህ ክፍያ ደግሞ ቶተንሃምን ከፉክክሩ ሲያወጣ፣ ምናልባት ማንችስተር ዩናይትድ ገንዘቡን ከፍሎ ሊያስፈርመው ይችላል ሲል ዘገባው አስነብቧል፡፡



ቸልሲዎች አንቶኒዮ ኮንቴን ላማባረር የወሰኑት ኤዲን ሀዛርድን በክለባቸው ለማቆየት ነው ሲል Telegraph ዘግቧል፡፡ ሀዛርድ የአንቶኒዮ ኮንቴ ጋር ያለው ግንኙነት መልካም ባለመሆኑ ከአሰልጣኙ ጋር ግጭት ውስጥ እንደገባው ዘገባው አስረድቷል፡፡ በዚሁ መሰረት ቸልሲዎች አጥቅቶ መጫወት የሚፈልግ አሰልጣኝ ወደ ቡድኑ በማምጣት ስሙ ከሪያል ማድሪድ ጋር የተያያዘውን ሀዛርድ በክለባቸው ለማቆየት ወስነዋል፡፡ ሊዊስ ኤንሪኬ እና የናፖሊው አሰልጣኝ ማውሪዚዮ ሳሪ ወደ ቸልሲ የሚመጡ ከሆነ ሀዛርድ በክለቡ ሊቆይ ይችላል የሚል ተስፋም አላቸው፡፡



ማሲሚሊያኖ አሌግሪ 200 ሚ. ፓውንድ ይፈልጋ ሲል Sun ዘግቧል፡፡ አርሰናሎች አሌግሪን አሰልጣኝ አድርገው መቅጠር ከፈለጉ 200 ሚ. ፓውንድ ለተጫዋቾች ዝውውር ማዘጋጀት ይኖርባቸዋል፡፡ ክለቡን መልሶ በፕሪሚየር ሊጉ እና በአውሮፓ መድረክ ተፎካካሪ ለማድረግ ተጫዋቾች መገዛት አለባቸው፡፡ ይህ ከሆነ እና አርሰናል ገንዘቡን የሚያዘጋጅ ከሆነ ቱሪንን ለቀው ወደ ኤሚሬትስ መሄድ እንደሚፈልጉ ዘግቧል፡፡



ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያደጉት ዎልቮች የማንችስተር ዩናይትዱን ቮክተር ሊንደሎፍ በውሰት መውሰድ ይፈልጋሉ፡፡ ባለፈው ክረምት በ31 ሚ. ፓውንድ ከቤነፊካ የፈረመው ሊንደሎፍ ብዙም የመሰለፍ እድል እያገኘ አይደለም፡፡ ይህን በመጠቀም ዎልቮች የመሰለፍ እድል ሊሰጡት እና በፕሪሚየር ሊጉ ልምድ እንዲቀስም ለማድረግ በውሰት ሊያስፈርት እንደፈለጉ Mirror ዘግቧል፡፡





አርሰናሎች ኩሊባሊን ይፈልጋሉ፡፡ አርሰናሎች ውጤታማ ያልሆነውን የተከላካይ መስመር ለማጠናከር ሲሉ የናፖሊውን ካሊዱ ኩሊባ ማስፈረም ይፈልጋ ሲሉ Daily እና Sunday Express ዘግበዋል፡፡ ናፖሊዎች ለሴኔጋላዊው ተከላካይ 53 ሚ. ፓውንድ ይፈልጋሉ፡፡ ይህን ደግሞ አርሰናሎች የቻምፒየንስ ሊግ እድል ባለማግኘታቸው መክፈል መቻላቸው አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ ናፖሊዎች ከአማካዩ ጆርጊንሆ እና ኩሊባሊ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ ለማትረፍ አቅደዋል፡፡



ኔይማር 2000 ፐርሰን በፒኤስጂ ይቆያል ሲሉ የፒኤስጂው ፕሬዝዳንት ናስር አል ክላፊ ተናገሩ፡፡ ኔይማር ባለፈው አመት በ201 ሚ. ፓውንድ ነበር ወደ ፒኤስጂ የተዘዋወረው፡፡ (Goal)



አርሰናሎች የባየር ሊቨርኩሰኑን ግብ ጠባቂ ሌኖ እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡ አርሰናል ፒተር ቼክን ሊተካላቸው የሚችል ግብ ጠባቂ በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአለም ዋንጫው የጀርመን ቁጥር አንድ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው በርንድ ሌኖ ደግሞ በአርሰናሎች የሚፈለግ ተጫዋች ነው፡፡ ተጫዋቹ ለማስፈረም የውል ማፍረሻ 22 ሚ. ፓውንድ ብቻ መሆኑ ደግሞ ለአርሰናል ሁኔታውን እንደሚያቃልል Mirror ዘግቧል፡፡



ኤቨርተኖች አሰልጣኛቸውን ለማባረር ማቀዳቸውን Sun ዘግቧል፡፡ አሰልጣኝ ሳም አላርዳይስ በውድድሩ ግማሽ አመት ላይ ነበር የኤቨርተን አሰልጣኝ ተደርገው የተሾሙት፡፡ ይሁንና የኤቨርተን ባለቤት የሆነው ፋርሃድ ሞሺሪ በአላርዳይስ ሁኔታ ደስተኛ ባለመሆናቸው ሊያባሩት አቅደዋል፡፡ በቦታውም ከዋትፎርድ የተባረረውን ማርኮ ሲልቫ ለማምጣት አቅደዋል፡፡


"ቤንች ላይ በመቀመጥ መማር አትችልም''
 ቴዲ ሼሪንግሃም ማርቆስ ራሽፎርድን ቡድኑን ለቆ እንዲወጣ መክሯል። በሆዜ ተመራጭ መሆን ያቃተውና ከማርሻል ጋር ለተደጋጋሚ ወቀሳ የበቃው ራሽፎርድ በሆዜ ስር የነበረው ፈጣን እድገት እንደተገታና ከሱ ይልቅ ፌላይኒን ማመናቸው በብዙዎች የዩናይትድ ደጋፊዎች ኩርፊያን ፈጥሯል።

Saturday, May 12, 2018

ቅዳሜ የወጡ የዝውውር ዜናዎችና መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update


═════════════════════════
📂  ሞሪንዎ ክላይቨርትን ይፈልጉታል
═════════════════════════


እንደ the guardian ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ጆዜ ሞሪንዎ የአያክሱን ታዳጊ ጀስቲን ክላይቨርትን ማዛወር ይፈልጋሉ።

የ19 አመቱ ተጭዋች በመጀመሪያው የኤርዲቪዜ የውድድር አመቱ ላይ ድንቅ ብቃቱን ማሳየቱን ተከትሎ በበርካታ የአውሮፓ ትላልቅ ክለቦች አይን ውስጥ መግባት ችሏል።

ጆዜ ሞሪንዎ እንደሚያምኑት ከሆነ ዩናይትዶች ተጨዋቹን ከሆላንዱ ክለብ ለመንጠቅ ጥሩ ስቴፕ እንደሄዱ እና ክረምት ላይ ሂሳብ አቅርበው እንደሚወስዱት ያምናሉ።


═════════════════════════
📂  ዲሲ ዩናይትዶች ሮኒን የማዛወር ፍላጎት እንዳላቸው አረጋገጡ
═════════════════════════


የዲሲ ዩናይትዱ አለቃ ቤን ሆልሰን እንደተናገሩት ከሆነ ዋይኒ ሩኒን የማዛወር ፍላጎት አላቸው።

እንግሊዛዊው ኢንተርናሽናል ወደ አደገበት ክለብ ኤቨርተን ከተመለሰ በኃላ ከዲሲ ክለብ ሰዎች ጋር ድርድር ላይ ቢሆንም እንደ ኦልሰን ገለፃ ከሆነ ግን ድርድሩ እስካሁን አልተጠናቀቀም።

"ድርድሩ አሁን ላይ አልተጠናቀቀም"  ሲሉ ኦልሰን ለTMZ ተናግረዋል።


═════════════════════════
📂  ቼልሲዎች ካንቴን በአሴንሶ ሊቀይሩት ነው
═════════════════════════


እንደ ስፔኑ ተነባቢ Don Ballon ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ቼልሲዎች የሪያል ማድሪዱን ማርኮ አሴንሶን ለማስፈረም ሲሉ ንጎሎ ካንቴንም ሳይቀር ለመስጠት ዝግጁ ናቸው።

ስፔናዊው ተጭዋች የሮማን አቭራሞቪች የክረምቱ ዝውውር ዋነኛ ኢላማቸው ሲሆን እርሱን ለማዛወር ሲሉ ኮከብ ተጭዋቻቸውን ለመስጠትም ፍቃደኛ ናቸው።

ሪያል ማድሪዶች ሙሉ ትኩረታቸውን ከኤዲን ሃዛርድ ዝውውር ወደ ኔይማር ማዞራቸውን ተከትሎ ቼልሲዎች በበኩላቸው ካንቴን መስዋት ለማድረግ ተሰናድተዋል።


═════════════════════════
📂  ጋሬዝማን ከአትሌቲኮዎች ጋር ወሳኝ ንግግር አድርጓል
═════════════════════════


እንደ Mundo Deportivo ዘገባ ከሆነ አንቶኔ ጋሬዝንማ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ባለስልጣናት ጋር በወደፊት የክለቡ ቆይታው ዙሪያ ንግግር አድርጓል።

ምንም እንኳን በቅርቡ ተጨዋቹ ወደ ባርሴሎና መዛወር እንደሚፈልግ ፍንፅ ቢሰጥም አሁን ግን በክለቡ ሊቆይ እንደሚችል አመላካች ነገር ማሳየት ጀምሮአል።

ባለፈው አርብ ለት የሱ የህግ ሰዎች ከማድሪዶች ጋር ተገናኝተው ዝውውሩ ቢጠናቀቅ ምን አይነት ህጋዊ ተፅህኖዎችን ሊያመጣ እንደሚችል ተነጋግረዋል።

═════════════════════════
📂  ማን.ዩናይትዶች ጀርጊንዎ ላይ የነበራቸውን ፍላጎት አንስተዋል
═════════════════════════


እንደ ማንቸስተር ኢቭኒንግ ዘገባ ከሆነ ማን.ዩናይትዶች በናፖሊው አማካይ ጀርጊንዎ ላይ ያላቸውን ፍላጎት ትተውታል።

የዩናይትዶች ከጣሊያናዊው የ26 አመት አማካይ  ዝውውር ፉክክር ራሳቸውን ማግለላቸው ለጎረቤቶቻቸው የቅርብ ተቀናቃኞች ማን.ሲቲዎች ልጁን እንዲያስፈርሙት የተሻለ እድል የሚፈጥር ይሆናል።

የዩናይትድ ሰዎች በእርሱ ፋንታ ሚሊንኮቪች ሳቪች፣ አርቱሮ ቪዳል፣ ጂያን ሚኬል ሴሪ፣ ፍሬድ እና ማርኮ ቬራቲን ጉዳይ እየተከታተሉ ይገኛሉ።


═════════════════════════
📂  ጆዜ ሞሪንዎ የዩናይትድ ደሞዝ ጣሪያን ቢልን ሊቀንሱ ነው
═════════════════════════


እንደ ሚረር ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ የዩናይትዱ አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ የቡድኑን ከፍተኛ የደሞዝ ጣሪያ ድምር መጠን በመቀነስ ለዝውውር የሚሆናቸውን የ150ሚ.ፓ ወይም የ203ሚ.ዶ ሂሳብ ለማትረፍ አስበዋል።

ይሄ ማለት እንደ ማቲዩ ዳርሜይን፣ ዴይሊ ብላይንድ እና ሉክ ሾው የመሳሰሉ ተጭዋቾች ክለቡን የመልቀቅ እድላቸው ሰፊ ነው።
═════════════════════════
ADVERTISEMENT


═════════════════════════
ሌሎች አጫጭር ወሬዎች ...
═════════════════════════


📂  የማንችስተር ዩናይትዱ የፊት አጥቂ ሮሜሉ ሉካኩ በሚቀጥለው ሳምንት ከቼልሲ ለሚደረገው የኤፍ, ኤ ካፕ ፍፃሜ ወደ ጨዋታ እንደሚመለስ ተማምኖዋል።   (ሜይል)


📂  አዲሱ የሊቨርፑል ወዱ ፈራሚ ቨርጂል ቫንዳይክ በውሉ ላይ አንድ ይፋ ያልወጣ አንቀፅ እንዳለበት በመረጃ አፈትላኪው (ፉትቦል ሊክስ) በኩል ተጠቅሷል፣ አንቀፁም እንደሚለው ተከላካዩ ለ22 ጨዋታዎች ያክል ጎሉን ካላስደፈረ £750,000 ሺህ ጉርሻ እንደሚያገኝ የሰፈረ ሲሆን፣ ጎል ባገባ ቁጥር ደግሞ ተጨማሪ £20,000 እንደሚሰጠው በውሉ ላይ ሰፍሯል።   (ሜይል)


📂  በኦልትራፎርድ ስታዲዮም ውስጥ በህክምና ላይ ያሉትን ሰር አሌክስ ፈርጉሰንን ለማሰብ አዲስ ባነር ተዘጋጅቷል፣ «እያንዳንዳችን አሌክስ ፈርጉሰንን እንወዳለን» የሚል ነው።   (ሜይል)


📂  የአርሰናሉ አጥቂ ኦቦሚያንግ ከዶርትመንድ ሲመጣ በነበረው ሂደትና፣ በውሉ ዙሪያ ያልተሰሙ አዳዲስ መረጃዎች እየወጡ ሲሆን፣ ለዚህም ደግሞ አፈትላኪ መረጃዎችን በማውጣት ቀዳሚ የሆነው ፉትቦል ሊክስ ነው፣ አሁን በለቀቀው መረጃም አርሰናል ለዝውውሩ ለተጫዋቹ £18.2 ሚሊዮን  የከፈሉ ሲሆን፣ አስከ 2021 የሚያቆየውን ውል በታማኝነት ከጨረሰ ደግሞ £15.15 ሚልዮን ሎያሊቲ ይከፈለዋል፣ ሌላው የኦቦሚያንግ ጉርሻ ደግሞ፣ የመጀመሪያ ተሰላፊ በሆነበት ጨዋታ አርሰናል ካሸነፈ በየጨዋታው £50 ሺህ እንደሚሰጠው የታወቀ ሲሆን በእስካሂኑ ሂደትም £250 ሺህ ያክል እንዳገኘም ተዘግቧል።  (ሜይል፣ጋርዲያን)


📂  ቼልሲ የ2018/19 አዲሱን የመጀመሪያውን ማሊያ ያስተዋወቀ ሲሆን ሆኖም በደጋፊዎቹ ዘንድ የተጠበቀውን ተቀባይነትን እንዳላገኘ እየተነገረ ነው።  (ደይሊ ስታር)


📂  የቀድሞው የባርሴሎናና ጁቬንቱስ ፉልባክ ዳኒ አልቬዝ በሳምንቱ አጋማሽ በተደረገው የፈረንሳይ ዋንጫ ላይ ከፍተኛ ጉዳትን ያሰተናገደ ሲሆን፣ እንደተፈራውም የጉዳቱ መጠን ከአለም ዋንጫው እንዳገለለው የታወቀው ትላንት ምሽት ነበር።(ማሪካ


📂  አንቶኒዮ ኮንቴ የሱ ቼልሲ ከሞውሪንሆው ቼልሲ የተሻለ እንደሆነ አስረግጦ ተናግሯል ። (ጋርዲያን)


📂  ማንችስተር ዩናይትድ ጀርጊንሆ ላይ የነበረው ፍላጎት በመቀዛቀዙ ፣ ማንችስተር ሲቲ የናፖሊውን አማካኝ ለማግኘት የተሻለ ወቅት ላይ እንደሚገኝ ታውቋል። (ማንችስተር ኢቭኒንግ)


📂  የአርሰናሉ የመሰመር ተጫዋች ሄክቶር ቤለሪን፣ በሚቀጥለው የውድድር ዘመንም በአርሰናል መቆየት እንደሚፈልግ ተናግሯል ። (ስካይ ስፖርት)


📂  የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን ፣ወደ ማድሪድ የመሄድ ፍላጎት አለው እየተባለ የሚታማው ብራዚላዊው ኔይማር እና ሮናልዶ በአንድ ቡድን ውስጥ መጫወት እንደሚችሉ ተናግሯል።  (ማርካ)


📂  ሊቨርፑልና አርሰናል €65 ሚሊዮን ያወጣል የተባለውን የናፖሊ አማካኝ ፔግሮ ዜሌንስኪ  ለማግኘት በፉክክር ላይ ናቸው። (ኮሬሮ ዴሎ ስፖርት)


📂  የአርሰናል አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር በመጨረሻው የጨዋታ በፊት ቃለ ምልልሳቸው ፣ አርሰናል ወደ ኤምሬትስ ከተዘዋወረ ቡሃላ በሃይበሪ የነበረውን የተለየ መንፈስ እንዳጡት አምነዋል። (ሚረር)

═════════════════════════
ADVERTISEMENT

Thursday, May 10, 2018

ዕለተ ሃሙስ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሰፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች ፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ባርሴሎና 8 ተጫዋቾችነ ለመሸጥ አቅዷል


➧ ባርሴሎና በክረምት የአትሌቲኮ ማድሪዱን አንቶን ግሪዝማን ለማስፈረም ይፈልጋል፡፡ እሱን ለማሳካት ደግሞ ከፍተኛ ገንዘብ ያስፈልገዋል፡፡ ገንዘቡን ደግሞ ስምንት ተጫዋቾችን በመሸጥ ለማዘጋጀት ወስኗል፡፡ የስምንቱ ተጫዋቾች ሽያጭ እስከ 100 ሚ. ዩሮ ሊያስገኝለት እንደሚችልም ተገምቷል፡፡

ተጫዋቾቹ ሉካ ዲኘ፣ አንድሬ ጎሜዝ፣ አልክስ ቪዳል፣ ፓኮ አልካሴር፣ ዴኒስ ሱዓሬዝ፣ ጄራርደ ዴሎፉ፣ ሙኒር ኤል ሀዳዲ እና ራፊናህ ናቸው፡፡

ባርሴሎና አንቶን ግሪዝማንን ከማስፈረሙም በተጨማሪም ሌሎች ተጫዋቾችንም እንሚያመጣ ይጠበቃል፡፡   (ምንጭ፡ Sky Sports News)



ሪያል ማድሪዶች ግብ ጠባቂ አሰሳ ላይ ናቸው


 ➧ ሪያል ማድሪዶች የሮማውን ግብ ጠባቂ አሊሰን ለማስፈረም መዘጋጀታቸውን RMC Sport ዘገቧል፡፡ አሊሰን በዚህ የውድድር አመት በሮማ ባሳየው ምርጥ ብቃት መሰረት ስሙ ከሊቨርፑል እና ማንችስተር ዩናይትድ ጋር ሲያያዝ ከርሟል፡፡ ሪያል ማድሪድ ከዚህ በፊት ስሙ ከቲቦ ኮርቱዋ እና ዴቪድ ዴ ሂያ ጋር ሲያያዝ ቢከርምም አሁን ግን ፉቱን ወደ አሊሰን በማዞር ለልጁ ክፍያ ለማቅረብ መዘጋጀቱም ተዘግቧል፡፡


 ዴ ሊግት በክረምቱ አያክስን መልቀቅ ይፈልጋል


 ➧ የአያክስ አምስተርዳሙ ተከላካይ ማቲያስ ዴ ሊግት በአውሮፓ ከሚገኙ ምርጥ ተጫዋቾች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የዝውውር መስኮቱ ሲከፈት ወደ ሌላ ክለብ ለመዘዋወር እንዳቀደ ተዘግቧል፡፡ ወኪሉ ሚኖ ራዮላም ይህን እንደሚያሳካለት እምነት ጥሏል፡፡ ባየር ሙኒክ፣ ባርሴሎና፣ ማንችስተር ሲቲ እና ቶተንሃም ሆትስፐር የልጁ ፈላጊ መሆናቸውን De Telegraaf ዘግቧል፡፡



 ማንችስተር ሲቲዎች የሌዚስተር ሲቲውን ሪያድ ማህሬዝ ማስፈረም ይፈልጋሉ


➧ ሲቲዎች ባለፈው የጥር መስኮት ልጁን ለማስፈረም ጥያቄ አቅርበው ነበር፡፡ ይሁንና ሌዚስተር 95 ሚ. ፓውንድ ካልከፈላችሁ በማለቱ ዝውውሩ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ በሰዓቱ ሲቲ ያቀረበው የ65 ሚ. ፓውንድ ክፍያ ነበር፡፡ ማህሬዝም ቢሆን ወደ ሲቲ ለመሄድ ጥረት አድርጎ ነበር፡፡ ይሁንና አልተሳካም፡፡ አሁን ግን ሲቲዎች ዳግመኛ ወደ ሌዚስተር በመመለስ ልጁን ለማስፈረም ጥረት ያደርጋሉ ሲል The Times ዘግቧል፡፡


ፒኤስጂ የፉልሃሙን ወጣት ርያን ሴሴይኖን ለማስፈረም የሚደረገውን ጥረት ግፍተውበታል


➧ ፒኤስጂ የፉልሃሙን ወጣት ርያን ሴሴይኖን ለማስፈረም የሚደረገውን ጥረት ግፈቶበታል ሲል Daily Mirror ዘግቧል፡፡ የ17 አመቱ ተጫዋች በቶተንሃምና ማንችስተር ዩናይትድ ይፈለጋል፡፡ ነገር ግን የሊግ 1 ሻምፒዮኑ ፒኤስጂ 50 ሚ. ፓውንድ በመክፈል ልጁን ለመውሰድ ተዘጋጅቷል፡፡ የሴሴይኖን እጣ ፈንታ በክለቡ ውጤት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡ ፉልሃም በአሁኑ ሰዓት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ለማለፍ በጥሎ ማለፉ ተደልድሏል፡፡ ምናልባት አሸንፎ የሚያልፈ ከሆነ ወጣቱ በፉልሃም ሊቆይ ይችላል፡፡


‹‹ፖግባ በማንችስተር ዩናይትድ የሚቆይ ይመስለኛል›› 


 ➧ ‹‹ፖግባ በማንችስተር ዩናይትድ የሚቆይ ይመስለኛል›› ሲሉ ጆሴ ሞሪንሆ ለጋዜጠኞች ገልፀዋል፡፡ ፖግባ ከሞሪንሆ ጋር ግጭት ውስጥ ገብቷል ተብሎ ሲዘገብ ነበር፡፡ ይሁንና ክለቡም ሆነ እሳቸው ልጁን መሸጥ እንደማይፈልጉ አስታውቀዋል፡፡ ፖግባ ወደ ፈረንሳይ በማምራት ለፒኤስጂ ሊፈርም ይችላል የሚሉ በርካታ መረጃዎች ሲወጡ ነበር፡፡ ዘገባው የGoal ነው፡፡


የዌንገር ተተኪ እጩዎች ወደ 5 ዝቅ አሉ


 ➧ በአርሰናል የሚፈለጉ አሰልጣኞች ስም ዝርዝር ወደ አምስት ዝቅ ብሏል ሲል Daily Mail ዘግቧል፡፡ እንደ ደይሊ ሜል ዘገባ ከሆነ ሚኬል አርቴታ፣ ፓትሪክ ቪየራ፣ ማሲሚሊያኖ አሌግሪ፣ ዮዓኪም ሎው እና ሊዊስ ኤንሪኬ በዝርዝሩ ውስጥ ያሉ ናቸው፡፡ የክለቡ ባለስልጣናት ወጣት አሰልጣኝ ለመቅጠር መፈለጋቸው ደግሞ ለአርቴታ እና ቪየራ እድሉን ያሰፋል ሲል ዘገባው አክሏል፡፡


ሌሮይ ሳኔ - "ስለኮንትራት ለማውራት አልቸኩልም"


 ➧ የማንችስተር ሲቲው ሌሮይ ሳኔ ስለኮንትራት ለማውራት አልቸኩልም ማለቱን The Sun ዘገቧል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ የአመቱ ወጣት ተጫዋችን ኮንትራት ለማራዘም ሲቲዎች ከፍተኛ የሆነ ፍጎት አላቸው፡፡ በ2021 የሚጠናቀቀውን ኮንትራቱንም ከፍተኛ ደሞዝ በማቅረብ ለማራዘም አቅደዋል፡፡ ይሁንና ሳኔ ስለ ኮንትራት ማራዘም መነጋገር የሚፈልገው ከአለም ዋንጫው መጠናቀቅ በኋላ መሆኑ ተዘግቧል፡፡


 ሊቨርፑል ሌይቴን ለማስፈረም የሚደረገውን ጥረት እየመራ ይገኛል


 ➧ የፖርቶው ወጣት ተከላካይ በአርሰናል እና ማንችስተር ሲቲም ይፈለጋል፡፡ አርሰናል ክለቡ ፖርቶ የሚፈልገውን 15 ሚ. ዩሮ የውል ማፍረሻ ለመክፈልም ተዘጋጅቶ ነበር፡፡ ይሁንና ሊቨርፑሎች በቅርቡ ጥረታቸውን በማጠናከር ልጁን ከአርሰናል ለመንጠቅ እየሞከሩ ይገኛል፡፡ ዘገባው የThe Guardian ነው፡፡


 ባርሴሎና ዴ ጆንግን በ2019 ማስፈረም ይፈልጋል


 ➧ አንደ Mundo Deportivo ዘገባ ከሆነ ባርሳዎች በ2018 ለማስፈረም ያቀዱት የአትሌቲኮውን አንቶን ግሪዝማን ነው፡፡ በተጨማሪም የግሬሚዮውን አማካይ አርተር ሜሎ ለማስፈረም ተስማምተዋል፡፡ ይሁንና በእድሜ እየገፋ ያለውን የመሃል ሜዳቸውን ሀይል ለመስጠም ወጣቱን የአያክስ አምስተርዳም አማካይ ፍሬንኪ ዴ ጆንግን ለማስፈረም አቅደዋል፡፡ ነገር ግን ልጁን በ2019 ነው ማስፈረም የሚፈልጉት


  ካርል ሄንዝ ሩሚኒግ ሮበርት ሌዋንዶውስኪ በክለባቸው እንደሚቆይ አስታወቁ


 ➧ የባየር ሙኒኩ ሀላፊ ካርል ሄንዝ ሩሚኒግ አጥቂያቸው ሮበርት ሌዋንዶውስኪ በቀጣዩ አመት በክለባቸው እንደሚቆይ አስታወቁ፡፡ ካሪም ቤነዜማ በዚህ የውድድር አመት አስቸጋሪ ጊዜን በማሳለፉ ምክንያት ማድሪድ ሌዋንዶውስኪን ሊያስፈረም ይችላል የሚሉ በርካታ ዘገባዎች ሲወጡ ነበር፡፡ ይሁንና ሩሚኒግ አጥቂውን መልቀቅ እንደማይፈልጉ እና በቀጣዩ አመትም የባየር ሙኒክን ማለያ እንደሚለብስ ተናግረዋል ሲል የዘገበው Goal ነው፡፡


ኔይማር ከማድሪዶች ጋር በድብቅ ተነጋግሯል


➧ የፒኤስጂው ኮከብ ብራዚላዊው ኔይማር በማርች ወር ውስጥ ከሪያል ማድሪድ ጋር በድብቅ ድርድር ማድረጉ እየተዘገበ ይገኛል፡፡ ኔይማር ፈረንሳይን በመልቀቅ ወደ እስፔን መመለስ ይፈልጋል ሲልም Express- ASን በመጥቀስ አስንብቧል፡፡



➧ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያደጉት ዎልቮች ወይኒ ሩኒን ማስፈረም ይፈልጋ፡፡ የ32 አመቱ ወይኒ ሩኒ ከአሰልጣኙ ጋር ባለመስማማቱ ክለቡን ሊለቅ ይችላል ሲል የዘገበው Birmingham Mail ነው፡፤


➧ አርሰናሎች ለጃክ ዊልሸር የ3 አመት ኮንትራት ማቅረባቸውን Star ዘገቧል፡፡ የዊልሸር ኮንትራት በዚህ ክረምት ይጠናቀቃል፡፡


➧ አርሰናሎች የባየር ሊቨርኩሰኑን ግብ ጠበቂ በርንድ ሌኖ ለማስፈረም ድርድር መጀመራቸውን Express - Bildን በመጥቀስ ዘግቧል፡፡

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ADVERTISEMENT

Wednesday, May 9, 2018

ዕረቡ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሰፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች ፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የርገን ክሎፕ የ70ሚ.ዩ የዝውውር ግምት የተሰጠውን ፌከር አግኝተውታል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ Canal Plus ዘገባ ከሆነ የሊቨርፑሉ አለቃ የርገን ክሎፕ በ70ሚ.ዩ ወይም በ80ሚ.ዶ የዝውውር ሂሳብ ግምት የተሰጠውን የሊዮን ኮከብ ናቢ ፊከር አግኝተው በዝውውሩ ዙሪያ አነጋግረውታል።

እንደ ዘገባው ከሆነ የፈረንሳዊው ኢንተርናሽናል የ24 አመት ኮከብ አንፊልድ ዝውውር ከመጠናቀቅ ምንም እንሰማያደናቅፈው የተነገረ ሲሆን በ2018-19 የውድድር አመት ላይ ይዛወራል።

ቼልሲዎችም ተጨዋቹን የማዛወር ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም እርሱ ግን ከሰማያዊዎቹ ይልቅ ቀዮቹን መርጧል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማን.ዩናይትዶች ለፑሊሲች ዝውውር ማርሻል እና ገንዘብ ሊያቀርቡ ነው
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ማንቸስተር ዩናይትዶች አሜሪካዊውን አማካይ ክርስቲያን ፑሊሲች ለማዛወር ሲሉ አንቶኒዮ ማርሻል እና ተጨማሪ ጥሬ ገንዘብ ለክለቡ ቦሩሲያ ዶርትመንዶች ሊሰጡአቸው አቅደዋል።

እንደ mirror ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ የ22 አመቱ ፈረንሳዊ ኢንተርናሽናል አጥቂ በኦልትራፎርድ ተመራጭ መሆን እያቃተው ሲሆን በጆዜ ሞሪንዎ በክረምቱ ሊለቀቅ ተወስኖበታል።

በዚህ ሳቢያ ፈረንሳዊው ተጭዋች በጀርመኑ ቡንደስሊጋ ላይ ምርጥ ብቃቱን እያሳየ ባለው እና ከእርሱ በ3ት አመታት እድሜ በሚያንሰው የክንፍ ተጭዋች ዝውውር አካል ሊደረግ ይችላል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
አትሌቲኮ ማድሪዶች ከካቫኒ ጋር ከሞላ ጎደል ተስማምተዋል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ Mundo Deportivo ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ አትሌቲኮ ማድሪዶች የPSGውን አጥቂ ኤድሰን ካቫኒን ለማዛወር ቅድመ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የቡድኑ አለቃ ዲያጎ ሲሞኔ በመጨረሻም አንቶኔ ጋሬዝማን ከሲዝኑ መጠናቀቅ በኃላ ክለቡን እንደሚለቅ ያመነ ሲሆን ከወዲሁ ትልቅ ስም ባለው ተጫዋች ሊተካው አቅዷል።

ኡራጉዋዊው ኢንተርናሽናል ከኔይማር ጋር ስምምነት ስላሌለው የፓሪሱን ክለብ መልቀቅ የሚፈልግ ሲሆን ዲያጎ ጎዲን እና ጆዜ ጊሚኔዝ ደግሞ ወደ አትሌቲኮ እንዲመጣ አሳምነውታል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ኤቨርተኖች ሳም አላርዳይስን አርሰን ዌንገር እንዲተኳቸው ይፈልጋሉ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ dailystar ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ኤቨርተኞች የክለባቸውን አለቃ ሳም አላርዳይስን በማሰናበት አርሰን ዌንገር ቦታቸውን እንዲተኩላቸው ይፈልጋሉ።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ብራይተር፦ ኔይማር በቀጣዩ አመት ለሪያል ማድሪድ ወሳኝ ተጭዋች ይሆናል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ እውቁ ጀርመናዊ ፓል ብራይተር እምነት ከሆነ የኔይማር የሪያል ማድሪድ የክረምቱ ዝውውር የማይቀር ሲሆን የPSGው ብራዚላዊ ኮከብ በቀጣይ አመት የማድሪዶች ቁልፉ ሰው ይሆናል የሚል ግምታቸውን ተናግረዋል።

በሪያል ማድሪድ ቆይታቸው ወቅት የላ ሊ ጋውን ዋንጫ ከክለቡ ጋር ማንሳት የቻሉት ብራይተር ለጀርመን Sport 1 ቴሌቭዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ መጠይቅ መሰረት "እመኑኝ ኔይማር በበርናባው ወሳኝ ይሆናል" ብለዋል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
● ሄክተር ቤለሪን ወደ ባርሴሎና
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ሄክቶር ቤለሪን ስሙ በተደጋጋሚ ግዜ ከጁቬንቱስ እና ባርሴሎና ዝውውር ጋር ተያይዞ መነሳቱን ተከትሎ ሲጠየቅ በክለቡ አርሰናል ፍፁም ደስተኛ መሆኑን እና ስለነዚህ ወሬዎች ቦታ እንደሌለው በመግለፅ አስተባብሎአቸዋል።

ከ2015 ጀምሮ ከመድፈኞቹ አካዳሚ በቅሎ ድንቅ ብቃቱን ያሳየው ስፔናዊ ተመላላሽ ተከላካይ ለረጅም ጊዜያት ያህል ወደ አሳዳጊው የካታሎን ክለብ ሊመለስ ይችላል ሲባል ከቆየ በኃላ በቅርብ ግዜ ደግሞ ስሙ ከጁቬንቱሶች ዝውውር ጋር ተያይዞ መወራቱ የሚታወስ ነው።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
አንቸሎቲ የአርሰናሎች ቁ2 ተመራጭ ናቸው
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


አርሰናሎች አዲስ አሰልጣኝ ለመቅጠር እያደረጉ ባሉት ጥረት ላይ ማሲሞ አሌግሪን የማያዛውሩ ከሆነ በምትካቸው ካርሎ አንቸሎቲን ለማምጣት እንደሚሰሩ dailystar ዘግቧል።

መድፈኞቹ የጁቮንቱሱን አለቃ እንደ ሁነኛ ቁ1 የአርሰን ዌንገር ምትክ አድርገው የሚያዩአቸው ቢሆንም ካልተሳካ ግን አንቸሎቲን እንደ አጭር ግዜ መፍትሄ ተቆጥረው ያዛውሩአቸዋል።

ተሳክቶላቸው አንቸሎቲን ወደ ኤምሬትስ የሚያዛውሩ ከሆነ ከፓትሪክ ቪየራ፣ ሚካኤል አርቴታ እና ዜሊኮ ቡቫች አንዳቸውን ምክትል አሰልጣኝ በማድረግ በሂደት ቡድኑን ሙሉ ለሙሉ እንዲረከቡ የማድረግ እቅድ አላቸው።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሃዛርድ ለቼልሲዎች ተስፋ ሰጥቷቸዋል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ኤዲን ሃዛርድ በለንደን ህይወቱ ፍፁም ደስተኛ መሆኑን በመግለፅ እና የቻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ማግኘት ማጣት በወደፊት ቆይታው ላይ ተፅህኖ እንደማይፈጥርበት በመናገር ለቼልሲ ሰዎች ተስፋ ሰጥቷል።

ቤልጂየማዊው የ27 አመት ኮከብ ተጫዋች ስሙ በተደጋጋሚ ግዜ ከስፔኑ ሃያል ክለብ ሪያል ማድሪድ እና ከሊግ ዋኑ ሻምፒየኖች ፒኤስጂ ጋር ተያይዞ ሲወራ መቆየቱ ክለቡን ስጋት ላይ ጥሎት ቆይቷል።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ADVERTISEMENT

Tuesday, May 8, 2018

ማክሰኞ ከሰአት በኃላ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሰፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች ፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማንቸስተር ዩናይትዶች ሚሊንኮቪች ሳቪችን ለማዛወር ተስማሙ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ TheSun ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ማን.ዩናይትዶች በ80ሚ.ፓ የዝውውር ሂሳብ ወይም በ108ሚ. ዶላር ሂሳብ የላዚዎውን አማካይ ሰርጂ ሚሊንኮቪች ሳቪች ዝውውር ከስምምነት ላይ ደረሱ። ተጨዋቹ የመጀመሪያው የክለቡ ፈራሚ ይሆናል።


እንደ ዘገባው ከሆነ ጆዜ ሞሪንዎ በአማካይ ክፍል ላይ በማርዋን ፌላይኒ መውጣት እና በማይክል ካሪክ መልቀቅ ሳቢያ የሳሳውን የአማካይ ክፍል ማጠናከር ይፈልጋሉ።


የዝውውሩ ዋጋ ሚሊንኮቪች ሳቪች በፕሪሚየር ሊጉ ታሪክ ከፖል ፖግባ በመቀጠል ሁለተኛው ከፍተኛ የዝውውር ሂሳብ የተከፈለበት ተጭዋች ይሆናል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ኢኔሽታ ወደ ጃፖን ለመዛወር ተስማማ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


አንድሬስ ኢኔሽታ ወደ ጃፓኑ ክለብ ቪሴል ኮቤ ለመዛወር ከስምምነት ላይ ደረሰ ሲል ESPN ዘገበ።


ስፔናዊው የ31 አመት ኮከብ ለJ-League ተወዳዳሪው ክለብ ለ3ት አመታት ለመጫወት የተስማማ ሲሆን አመታዊ የ30ሚ. ዶላር ወይም የ22ሚ.ዩ ሂሳብ ደሞዝ ይከፈለዋል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
PSGዎች ዶናሩማን ተቀዳሚ ኢላማቸው አድርገውታል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ ፈረንሳዊው ተነባቢ ጋዜጣ ዘገባ Lequipe እንዳስነበበው ከሆነ PSGዎች ዶናሩማን የክረምቱ የዝውውር መስኮት ተቀዳሚ ኢላማቸው አድርገውታል።


የሊግ ዋኑ ሻምፒየን ክለብ እንዳሉት ከሆነ ያሁኑን የክለባቸውን ግብ ጠባቂ አልፎንሴ አሪዎላ በዶናሩማ መተካት ይፈልጋሉ። ሆኖም ዝውውሩን እውን የሚያደርጉት የፊፋን Financial Fair Play Rule የማይትሱ ከሆነ ብቻ ነው።


የፓሪሱ ክለብ ሰዎች የክለቡን ቁ1 ግብ ጠባቂ በማሰስ ላይ ሲሆኑ ቲቢዎት ኩርቱዋንም ቀርበው አናግረውታል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
አርሰናሎች በዊልሸር ኮንትራት ዙሪያ ተስፋ ሰንቀዋል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ ቴሌግራፍ ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ አርሰናሎች ከጃክ ዊልሸር ጋር ሲያደርጉት የነበረውን የኮንትራት ድርድር ንግግር ተስፋ ሰጪ ሆኖላቸዋል። ተጨዋቹ በዚህ ሲዝን ወጥ በሆነ ጥሩ አቋም ብቃት ላይ ይገኛል።


መድፈኞቹ ባለፈው ክረምት ላይ ተጭዋቹን ለመሸጥ ብዙ ሞክረው የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በክለቡ እያገኘ ያለውን ሳምንታዊ የ110,000 ፖውንድ ደሞዝ ላይ ጥቅማ ጥቅሞችን በመጨመር አዲስ ኮንትራት ሊያስፈርሙት ይፈልጋሉ።


ተጨዋቹ በሰሜን ለንደኑ ክለብ የሚያቆየውን አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም እንደተቃረበ ለቃቂው አሰልጣኝ አርሰን ዌንገር ተናግረዋል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የጀርጊንዎ ወኪል ደንበኛው በበርካታ የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች እንደሚፈለግ ተናገረ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ ብራዚላዊው የናፖሊ አማካይ ጆርጊንዎ ወኪል ከሆነ ደንበኛው በ'አራት ወይም አምስት' የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ለዝውውር ይፈለጋል። ሆኖም የሴሪአው ክለብ የተጨዋቹ የወደፊት ቆይታ ላይ እስካሁን ምንም ውሳኔ አላሳለፈም።


ወኪል ጆአዎ ሳንቶስ እንዳለው ከሆነ ሁሉም ሰው የእንግሊዝ ክለቦች ሊያዛውሩት እንደሚፈልጉ ያውቃል። ሆኖም ግን የናፖሊዎችን ፍላጎት ስላልተረዳ ከየትኛውም ክለብ ጋር ንግግር እያደረገ አይደለም።


ጆርጊንዎ በክለቡ እስከ 2020 ድረስ የሚያቆየው ውል ያለው ሲሆን ጣሊያናዊው አማካይ አዲስ ኮንትራት ሊፈራረም እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሉዊስ ሄነሪኬ ራሱን አስወድዶ ከአርሰናል መንበር ለመረከብ እየራቀ ነው
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ the Mirror ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ አርሰን ዌንገርን ለመተካት በሚደረገው ፉክክር ላይ የቀድሞው የባርሴሎና አሰልጣኝ ሉዊስ ሄነሪኬ ውድ ኮንትራት በመጠየቅ ራሱን ከፉክክሩ እያገለለ ነው።


ሄነሪኬ ክለቡን ለመረከብ የጠየቀው አመታዊ ደሞዝ ከግብር በኃላ 15ሚ.ፓ ወይም 20ሚ. ዶላር ነው ተብሏል። ሆኖም አሁንም ድረስ ግን ከፉክክሩ ውጪ አይደለም።


አርሰናሎች መጪው የአለም ዋንጫ ውድድር ከመጀመሩ ቀደም ብለው ቀጣዩን የክለቡ አለቃ ለመቅጠርና ይፋ ለማድረግ እየሰሩ ይገኛሉ።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማስታወቂያ ...

Monday, May 7, 2018

Transfer News - ዕለተ ሰኞ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሰፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች ፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሊቨርፑሎች በ50ሚ.ፓ የዘሃ ዝውውር ላይ ቼልሲን ይፎካከራሉ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


The Dailystar ጋዜጣ እንደዘገበው ከሆነ ሊቨርፑሎች 50ሚ.ፓ የዝውውር ዋጋ የተተመነለትን ዊልፍሪድ ዘሃ ለማዛወር ከፕሪሚየር ሊጉ ተፎካካሪ ክለብ ቼልሲ ጋር ለመፎካከር ወስነዋል።


አይቬሪኮስታዊው ኢንተርናሽናል የክንፍ መስመር ተሰላፊ በዚህ የውድድር አመት ላይ ኤግልሶች ከሊጉ እንዳይወርዱ ያዳናቸው ሲሆን በማንቸስተር ዩናይትድ ያልተሳካ ጊዜ ካሳለፈ በኃላ በሌላ ትልቅ ክለብ ውስጥ የመዛወር ሌላ እድል ይቀርብለታል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ራሞስ ኢኔሽታን በመከተል ወደ ቻይና ሊጓዝ እንደሚችል ፍንጭ ሰጠ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ሰርጂዎ ራሞስ ቀልድ ባዘለው ምላሹ ላይ እሱም ወደ ቻይናው ሱፐር ሊግ ሊዛወር እንደሚችል ተናገረ።


ኢኔሽታ በዚህ የውድድር አመት መጨረሻ ላይ ባርሴሎናን በመልቀቅ ወደ ቻይናው ሱፐር ሊግ እንደሚዛወር የተረጋገጠ ሲሆን ራሞስ በበኩሉ በቅርብ ጊዜያቶች ውስጥ በቻይና ሊገናኙ እንደሚችሉ ጠቁሟል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማንቸስተር ዩናይትዶች ማርሻልን የሚለቁበትን መንገድ አስቀምጠዋል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ማንቸስተር ዪናይትዶች አንቶኔ ማርሻልን ለቼልሲ ለመሸጥ ፍቃደኛ ናቸው ሆኖም ግን ዝውውሩ እውን የሚሆነው 80ሚ.ፓ የዝውውር ሂሳብ እና ዊሊያንን ተጨምረው ሲሰጧቸው ብቻ ነው ሲል dailystar ዘገበ።


ፈረንሳዊው ኢንተርናሽናል የፊት መስመር ተሰላፊ በዚህ የውድድር አመት ላይ የሚፈልገው ጨዋታዎች ያህል ቊሚ ተሰላፊ መሆን ያልቻለ ሲሆን የቼልሲዎች የክረምቱ የዝውውር እቅድ ውስጥ መካተት ችሏል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ኩቲንዎ ካን በባርሴሎና እንዲቀላቀለው ይፈልጋል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ Don Ballon ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ፊሊፕ ኩቲንዎ የቀድሞው የቡድን አጋሩ ኤምሬ ካን በባርሴሎና እንዲሰላቀለው ይፈልጋል።


ስሙ ከጁቬንቱስ ጋር በተደጋጋሚ እየተነሳ ያለው ጀርመናዊ ኢንተርናሽናል በሲዝኑ መጨረሻ ላይ ክለቡን የመልቀቅ ሙሉ መብት ያለው ሲሆን ፍሪ ኤጀንት በመሆን ወደፈለገበት ክለብ መዛወር ይችላል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሰርጂ ሚሊንኮቪች ሳቪች አረንጓዴ መብራት አይቷል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ሰርጂ ሚሊንኮቪች-ሳቪች ከዚህ የውድድር ዘመን መጨረሻ በኃላ ክለቡን ላዚዮን የመልቀቅ ምንም አይነት ስምምነት የለውም። ይህን ያለው ወኪሉ ሲሆን ተጨዋቹ በ80ሚ.ፓ የዝውውር ሂሳብ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ይዛወራል በሚል ሲወራ ቆይቷል።


አንዳንድ ከሰርቢያ የሚወጡ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ሳቪች ክለቡን እንዲለቅ እና ወደ ኦልትራፎርዱ ክለብ እንዲያቀና ፍንጮችን እና  አረንጓዴ መብራት ያየ ሲሆን የጆዜ ሞሪንዎም ተቀዳሚ የዝውውር ኢላማ ሆኑአል።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማስታወቂያ ...

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

Saturday, May 5, 2018

Transfer News - ዕለተ ቅዳሜ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሰፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች ፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማንቸስተር ዩናይትዶች ሜርቴንስን ይፈልጉታል!
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ማንቸስተር ዩናይትዶች በ25ሚ.ፓ የዝውውር ሂሳብ የናፖሊውን ኮከብ ድሬስ ማርቲንስን ለማዛወር ይፈልጋሉ ሲል daily mirror አስነብቧል።

የ30 አመቱ ቤልጂየማዊ ኢንተርናሽናል በባለፉት ሁለት የሴሪአ ሲዝኖች ላይ በድምሩ 46 ጎሎችን በማስቆጠር ከሊጉ ምርጥ ተጭዋቾች ተርታ አንዱ መሆን ችሏል።

መርቴንስ በኮንትራት ውሉ ላይ ከጣሊያን ውጪ ያሉ ክለቦች ከፈለጉት በ25ሚ.ፓ ዋጋ ብቻ ሊያዛውሩት እንደሚችሉ አንቀፅ ተካቶለታል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሱዋሬዝ አንቶኔ ጋሬዝማን ባርሴሎናን እንደሚቀላቀል ፍንጭ ሰጠ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ሉዊስ ሱዋሬዝ እንደሰጠው ፍንጭ ከሆነ የአትሌቲኮ ማድሪዱ ኮከብ አንቶኔ ጋሬዝማን የሆነ ቀን ባርሴሎናን ሊቀላቀል ይችላል።

ሱዋሬዝ ለራዲዮ ሪንኮን በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ ባርሴሎናዎች እነ ኦስማን ዴምቤሌይ እና ፊሊፕ ኩቲንዎ የመሳሰሉ ከዋክብትን የሚያስፈርምበትን መንገድ አድንቋል።

እናም ስለ አንቶኒዮ ጋሬዝማን ዝውውር ሲጠየቅ ተጨዋቹ በባርሴሎና የሚያጫውተው የተሟላ ብቃት አለው ካለ በኃላ ቢመጣ "በደንብ አርገን እንቀበለዋለን" ሲል አክሏል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ባርሴሎናዎች 'አዲሱ ኔይማርን' ሊያዛውሩ ነው
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ባርሴሎናዎች የ17 አመቱን ብራዚላዊ ታዳጊ ኮከብ ሮድሪጎን ወደ ካምፕ ኑ ስለሚያዛውሩበት ሁኔታ ከወኪሎቹ  ጋር ንግግር አድርገዋል ሲል Sport ዘግቧል።

ታዳጊው ባለው እምቅ ተሰጥዎ ሳቢያ ብዙዎች ከኔይማር ጋር እያነፃፀሩት ሲሆን ወደፊትም ሮድሪጎ የኔይማርን ያህል አለማቀፋዊ ተፅህኖ የሚኖረው ተጭዋች ሊሆን እንደሚችል ተናግረውለታል።

ታድጊው ኮከብ በሳንቶስ ክለብ እስከ 2022 ድረስ የሚያቆየውን ኮንትራት ያለው ሲሆን የ50ሚ.ፓ ውል ማፍረሻ ሂሳብ ውሉ ላይ ተክምቷል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ጋሬዝማን የማድሪድ እቅድ 'B' ውስጥ ይገኛል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ Don Ballon ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ሪያል ማድሪዶች በክረምቱ ሞሃመድ ሳላህን ማዛወር የማይችሉ ከሆነ በምትኩ አንቶኔ ጋሬዝማንን ለማዛወር ይንቀሳቀሳሉ።

ሳላህ በቀጣይ የውድድር አመት ላይ በማድሪድ ማሊያ ሊያዩት የሚፈልጉት ቁጥር አንዱ ተጭዋች ቢሆንም ሊቨርፒሎች ግብፃዊውን ለመልቀቅ የሚጠይቁትን የ200ሚ.ዩ የዝውውር ሂሳብ ለመክፈል ግን ፍቃደኞች አይደሉም።

ምንም እንኳን የጋሬዝማ ስም ከባርሴሎና ዝውውር ጋር በተደጋጋሚ እየተነሳ ቢሆንም ማድሪዶችም የውል ማፍረሻ 100ሚ.ዩ ሂሳቡን ለመክፈል ፍቃደኞች ናቸው።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የዌንገር ምትክ የ200ሚ.ፓ ዝውውር ሂሳብ ይለቀቅላቸዋል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


እንደ Dailystar ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ የአርሰናል መጪው አዲስ አሰልጣኝ ቡድኑን እንዲያሻሽሉት የ200ሚ.ፓ የዝውውር በጀት ይመደብላቸዋል።

አርሰን ዌንገር በሲዝኑ መጠናቀቂያ ላይ ክለቡን ለቀው የሚሄዱ ሲሆን በተከታታይ ሁለት አመታት ቡድኑ ከቻምፒየንስ ሊጉ ውድድር የራቀበትን ውጤት አስመዝግቧል።

ዘገባው አክሎ እንደገለፀው ከሆነ የጁቬንቱሱ አለቃ ማሲሞ አሌግሪ ቀጣዩ መድፈኛ ለመሆን ቁጥር አንዱ ተመራጭ ሲሆኑ ጣሊያናዊው ወደ ለንደን መዛወር የሚፈልጉ ከሆነ ለዝውውር የሚሆናቸው ረብጣ ሚሊዮን ዶላር ይኖራቸዋል ተብሏል።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማስታወቂያ ...

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

Friday, May 4, 2018

Transfer News - ዕለተ አርብ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሰፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች ፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎችን ያንብቡ



▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማስታወቂያ ...


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
PSGዎች 100ሚ.ፓ የሚያወጣውን ኤሪክሰን ይፈልጋሉ


እንደ Daily express ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ፒ.ኤስ.ጂዎች የቶተንሃሙን አማካይ ክሪስቲያን ኤሪክሰን ለማዛወር የ100ሚ.ፓ የዝውውር ሂሳብ በክረምቱ ለማቅረብ አሰናድተዋል።

የፈረንሳዩ ክለብ በቻምፒየንስ ሊጉ ላይ ብርቱ ተፎካካሪ የመሆን እቅድ የያዙ ሲሆን ይህንን ለማድረግ ደግሞ ለማዛወር ካቀዷቸው አማካዮች ውስጥ ዴንማርካዊው ኢንተርናሽናል አማካይ ቀዳሚውን ስፍራ ይዟል።

ኤሪክሰን በ2013 ከአያክስ የፈረመው በ12.5 ሚ.ፓ ሂሳብ ሲሆን ባሁኑ የገበያ ዋጋ ግን ተጭዋቹ ቶተንሃምን ለተከታታ ቶፕ-4 ካበቃ በኃላ ስምንት እጥፍ ሂሳብ ያወጣል ተብሏል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማርሻል የዝውውር ሂሳቦችን እያጤነ ነው


አንቶኔ ማርሻል ወኪሉ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ የሚቀርቡለትን የዝውውር ጥያቄዎች በሙሉ እንዲያጤናቸው ነግሮታል ሲል goal ድህረ ገፅ ዘግቧል።

ጆዜ ሞሪንዎ በ2016 የማንቸስተር ዩናይትድን መንበር ከተረከቡ በኃላ ክለቡ ካደረጋቸው አጠቃላይ ጨዋታዎች በ46% ላይ ብቻ ቋሚ ተሰላፊ መሆን ችሏል። በዚህም ደስታኛ አይደለም።

ባየር ሙኒክ እና ጁቬንቱሶች የ22 አመቱን የኦልትራፎርድ ቆይታ ሁኔታ በቅርበት ሆነው በመከታተል ላይ ይገኛሉ።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሶዩንሱ አርሰናልን በክረምቱ ሊቀላቀል ነው


እንደ ቀድሞ ክለቡ አለቃ ፍንጭ ከሆነ ቱርካዊው ኢንተርናሽናል ካግላር ሶዩንቹ በክረምቱ ላይ አርሰናልን ይቀላቀላል።

የ22 አመቱ ተጭዋች በ2016 ከፌይኖርድ በ2.65 ሚ.ፓ የዝውውር ሂሳብ ከቀድሞ ክለቡ አልቲኖርዱ የተቀላቀለ ሲሆን በውሉ ላይ የሚለቅበትን አንቀፅ አካቷል። በዚህ ሳቢያ ወኪሎቹ ከመድፈኞቹ ሰዎች ጋር ኮንታክት ያደረጉ ሲሆን ስለ መሃል ተከላካዩ መረጃዎችን ወስደዋል።

እንደ ቀድሞ ክለቡ ፕሬዝዳንት ሰይት መህመት ኦስካን ከሆነ አርሰናሎች በተጨዋቹ ዝውውር ላይ ባየር ሙኒክን በመርታት ፉክክሩን እየመሩት ይገኛሉ።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ቤይሊ የኬይላን ምባፔ እና ሃዛርድ አማራጭ


ማንቸስተር ሲቲዎች ሊዮን ቤይሊን የኬይላን ምባፔ ወይም ኢዲን ሃዛርድ ዝውውር ሁነኛ አማራጭ ኢላማ አድርገውታል።

የባየር ሊቨርኩሰኑ አጥቂ ከፒኤስ.ጂው  እና ከቼልሲው አጥቂዎች በቀነሰ የዝውውር ሂሳብ እንደሚያገኙት ያሰቡ ሲሆን ፔፕ ጋርዲዮላ በክረምቱ የፊት መስመር አጥቂውን ማሻሻል ይፈልጋል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ማን.ዩናይትዶች ሳንድሮን ለሻው ምትክ አጭተውታል


ለማንቸስተር ቅርብ እንደሆነ የሚነገርለት Manchester Evening News ጋዜጣ እንደዘገበው ከሆነ ማን.ዩናይትዶች የጁቬንቱሱን ግራ ተመላላሽ ተከላካይ አሌክስ ሳንድሮን በማዛወር ሉክ ሾውን ሊተኩበት ይፈልጋሉ።

ሪፖርቱ አክሎ እንደዘገበው ከሆነ ጆዜ ሞሪንዎ ዳኒ ሮዝ እና ኬይላን ትራኒን ለማዛወር የያዙትን እቅድ ያቀዘቀዙት ሲሆን ከነርሱ ይልቅ ብራዚላዊውን ኢንተርናሽናል ለማዛወር ቀዳሚ ኢላማቸው አድርገውታል።

ማቲዩ ዳርሜይን በክረምቱ ጁቬንቱስን ለመቀላቀል መቃረቡን ተከትሎ ተከላካዩ ለሳንድሮ ዝውውር አካል ሊሆን ይችላል ተብሏል።


▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ኢስኮ፣ ቤል እና ኮቫሲች ማድሪድን ሊለቁ ነው


እንደ Don Ballon ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ኢስኮ፣ ጋሬዝ ቤል እና ማቲዮ ኮቫሲች ከሻምፒየንስ ሊጉ ፍፃሜ ጨዋታ በኃላ ሪያል ማድሪድን ይለቃሉ።

ኢስኮ ማንቸስተር ሲቲን የሚቀላቀል ሲሆን ፤ ጋሬዝ ቤል በበኩሉ የሃሪ ኬን የዝውውር አካል በመሆን ለቶተንሃም ይቀርባል። ሆኖም የአማካዩ ኮቫሲች ማረፊያ ግን እስካሁን አልታወቀም።

Featured Post/ቀጣይ ልጥፍ

የዝውውር ዜናዎች

  ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር...