Saturday, November 18, 2017

ቅዳሜ ከሰት በኃላ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



MAN UTD TO MAKE ANOTHER RUN
AT BALE


ማንቸስተር ዩናይትዶች ለሦስተኛ ግዜ የሪያል ማድሪዱን አጥቂ ጋሬዝ ቤልን ለማዛወር ጥረት ያደርጋሉ ያለን the Mirror ጋዜጣ ነው።

እንደ ሪፖርቱ ዘገባ ከሆነ ሪያል ማድሪዶች በጋሬዝ ቤል ተደጋጋሚ ጉዳት የተማረሩ ሲሆን ማን.ዩናይትዶች በበኩላቸው ደግሞ ጆዜ ሞሪንዎ ዌልሳዊውን አማካይ ወደ እንግሊዝ በመመለስ የቀድሞ አካል ብቃቱ ላይ እንደሚመልሱት እምነት አላቸው።

ያም ሆኖ ማን.ዩናይትዶች የላ ሊጋው ክለብ ለዝውውሩ እየጠየቀ ያለውን የ£85 million ሂሳብ የማስቀነስ ተልእኮ ያለባቸው ሲሆን የቤል ኮንትራት እስከ 2022 ድረስ የሚቆይ ይሆናል።


MAN UTD TO MAKE JANUARY MOVE FOR ROSE


ጆዜ ሞሪንዎ የቶተንሃሙን ግራ ተመላላሽ ተከላካይ ዳኒ ሮዝን በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ በማዘዋወር ወደ ኦልትራፎርድ ሊያመጡት ይፈልጋሉ ሲል The Sun አስነብቧል።

ሮስ ለረጅም ጊዜያቶች ያህል ወደ ኦልትራፎርድ ይዛወራል በሚል በተደጋጋሚ ሲወራበት የቆየ ሲሆን ሪፖርቱ አክሎ እንደዘገበው ከሆነ ሮስ ወደ ቀያይ ሰይጣኖቹ የመዛቀር ፍላጎት አለው።

ቶተንሃሞች ተጭዋቹን እንዲለቁት ማሳመን የዩናይትዶች ተቀዳሚ ተግባር የሚሆን ሲሆን ዩናይትዶች ስፐርሶችን ለማለስለስ ሉክ ሾውን የዝውውሩ አካል በማድረግ ሊያቀርቡት ይችላሉ።


OZIL IS BARCA'S COUTINHO BACK-UP


ባርሴሎናዎች የፊሊፕ ኩቲንዎ ዝውውር የማይሳካላቸው ከሆነ ፊታቸውን ወደ አርሰናሉ አማካይ ሜሱት ኦዚል ለማዞር በተጠባባቂነት መያዛቸውን Mundo Deportivo ዘገበ።

የሊቨርፑሉ ኮከብ ኩቲንዎን በክረምት ለማዛወር ያደረጉት ተደጋጋሚ ጥረት ከከሸፈባቸው በኃላ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ የካታላኑ ክለብ የዝውውር ኢላማ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ሆኖም ሊቨርፑሎች አሁንም ተጭዋቹን ላለመልቀቅ የያዙትን አቋም የቀጠሉበት ሲሆን ዝውውሩ የማይሳካ ከሆነ ባርሴሎናዎች በእርሱ ምትክ በክረምቱ ኮንትራቱ የሚጠናቀቀውን ሜሱት ኦዚልን በቅናሽ ዋጋ ከአርሰናል ለማዛወር ጥረት ያደርጋሉ።

BARCA TRACKING LYON MIDFIELDER


ባርሴሎናዎች የሊዮኑን አማካይ ሉካስ ቱሳልት በዚህ የውድድር አመት ላይ እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተሉት ይገኛሉ ሲል Mundo
Deportivo ዘገበ።

ቱሳርት በክረምቱ ክለቡን የለቀቀውን ኮሬንቲን ቶሊሶን በመተካት መታየት የጀመረ ሲሆን በዚህ አመት ያደረጋቸውን በርካታ ጨዋታዎች ብዙ የባርሴሎና ቁልፍ ሰዎች በአካል በመሄድ ተመልክተውታል።


ARSENAL SCOUT BORO WINGER


አርሰናሎች የሚድልስቦሮውን ታዳጊ የክንፍ መስመር ተጫዋች ማርከስ ታቬርኒየርን ለማዛወር የሙከራ ግዜ ሰጥተውታል ሲል Daily Mail ዘገበ።

ታቨርኒየር በቅርቡ ቡድኑ ከሰንደርላንድ ጋር ሲጫወት የማሸነፊያውን ጎል ያስቆጠረ ሲሆን የእንግሊዙ ከ19 አመት በታች ተጫዋች በኤቨርተን ፣ በርንማውዝ እና አስቶን ቪላም ጭምር እየተከታተሉት ይገኛል።


BARCA MAKE FEKIR CONTACT


ባርሴሎናዎች አርሰናሎች ለሊዮኑ አማካይ ናቢል ፌከር ዝውውር ጥያቄ አቀረቡ የሚል ወሬ መሰማቱን ተከትሎ ተጭዋቹን እንዳይቀሙ ከተጭዋቹ ወኪሎች ጋር ንግግር ማድረግ ጀምረዋል ሲል Sport ዘገበ።

ፌከር በዚህ አመት እያሳየ ያለውን ምርጥ እንቅስቃሴ ተከትሎ የአርሰናሎች ተቀዳሚ የዝውውር ኢላማ የሆነ ሲሆን ሪያል ማድሪዶችም መልማዮቻቸውን ልከው ተመልክተውታል።

ይሄም ሆኖ ባርሴሎናዎች ፌከርን በሌላ ክለብ ላለመነጠቅ በሚል ከወዲሁ በዝውውሩ ዙሪያ በጥልቀት በመንቀሳቀስ ጥያቄ ለማቅረብ የተሰናዱ ሲሆን በጃቸው ማስገባት ከፈለጉ ለዝውውሩ ከ €50 million በላይ መክፈል ይኖርባቸዋል ተብሏል።

ታላቅ ቅናሽ - በአዲስ አበባ (መገናኛ እና ሳሪስ) ፣ ሀዋሳ፣ አዳማ፣ ጂማ፣ ሽሬ፣ ደብረ ማርቆስ፣ መቀሌ፣ ሀረር፣ ጎንደር እና ደሴ ከተማ ነዋሪ ነዎት? እንግዲያውስ በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናቶች ቅዳሜ እና እሁድ ብቻ የአይቴል S11 እና S31 ስልኮችን በታላቅ ቅናሽ ይግዙ! እንዲሁም ሲገዙ ልዩ ስጦታዎች ከአይቴል ሞባይል እዚያው ይውሰዱ! ለበለጠ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይጎብኙ  ፦  www.facebook.com/itelMobileEthiopia/



MOURINHO PLOTS LUIZ SWOOP


የማንቸስተር ዩናይትዱ አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ የቼልሲውን መሃል ተከላካይ ዴቪድ ሉዊዝ በማዛወር በድጋሚ አብረውት መስራት ይፈልጋሉ ሲል  Express ዘገበ።

የቀድሞው የቼልሲ አለቃ የብራዚላዊው ተጭዋችን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉት ያሉ ሲሆን ተጭዋቹ ከዩናይትድ ጋር በነበረው ጨዋታ ላይ ከቡድኑ ውጪ ከተደረገ በኃላ ሁኔታውን እየተከታተሉት ይገኛል።

ሉዊዝ ከቼልሲው አለቃ አንቶኒዮ ኮንቴ ጋር ቡድኑ በቻምፒየንስ ሊጉ በሮማ ሰፊ በሆነ የ3ለ0 ውጤት ከተሸነፈ በኃላ ግጭት ውስጥ መግባታቸው የሚታወስ ነው።

Thursday, November 16, 2017

ሃሙስ አመሻሽ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች




MAN UTD IDENTIFY NO.1 JANUARY
TARGET


ማንቸስተር ዩናይትዶች የቫሌንሺያውን አማካይ ካርሎስ ሶለር የጥሩ የዝውውር መስኮት ቁ1 የዝውውር ኢላማቸው አድርገውታል ሲል The Independent ጋዜጣ ዘገበ።

ሶለር በባለፉት 12 ወራት ውስጥ በቫሌንሺያ ጥሩ ብቃቱን እያስመሰከረ ሲሆን ጆዜ ሞሪንዎ የ20 አመቱን አማካይ በማዛወር ደካማውን የቡድናቸው አማካይ ክፍል መጠገን ይፈልጋሉ።

ከስፔን 21 አመት በታች እየተጫወተ የሚገኘው ኮከብ በቫሌንሺያ የሚያቆየውን አዲስ ኮንትታት የተፈራረመው በባለፈው ሜይ ወር ላይ ሲሆን የውል ማፍረሻው ወደ €80 million, ሆኖ ቢቀመጥም ዩናይትዶች ይሄንን ዋጋ አውርደው በ £40m የዝውውር ሂሳብ ብቻ እንደሚያዛውሩት ተስፋ አድርገዋል። አስፈላጊ ከሆነም በውሰት እዛው የሚገኘውን ተጭዋቻቸው አንድሪያስ ፔሬራን የዝውውሩ አካል በማድረግ መስጠት ይፈልጋሉ።


ታላቅ ቅናሽ - በአዲስ አበባ (መገናኛ እና ሳሪስ) ፣ ሀዋሳ፣ አዳማ፣ ጂማ፣ ሽሬ፣ ደብረ ማርቆስ፣ መቀሌ፣ ሀረር፣ ጎንደር እና ደሴ ከተማ ነዋሪ ነዎት? እንግዲያውስ በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናቶች አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ብቻ  የአይቴል S11 እና S31 ስልኮችን በታላቅ ቅናሽ ይግዙ! እንዲሁም ሲገዙ ልዩ ስጦታዎች ከአይቴል ሞባይል እዚያው ይውሰዱ! ለበለጠ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይጎብኙ  ፦  www.facebook.com/itelMobileEthiopia/


MAN CITY BATTLE MAN UTD FOR GRIEZMANN


ማንቸስተር ሲቲዎች የአትሌቲኮ ማድሪዱን ኮከብ አንቶኔ ጋሬዝማንን ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ የከተማቸውን ተቀናቃኝ ማን.ዩናይትዶች ለመፎካከር ዝግጁ ናቸው ያለው Sport's print edition ነው።

ዩናይትዶች ፈረንሳዊውን ኢንተርናሽናል ባለፈው ክረምት ላይ እንደሚያዛውሩት የሚጠበቅ የነበረ ቢሆንም የአትሌቲኮዎች የዝውውር እገዳ መነሳት ባለመቻሉ ግን ዝውውሩ እውን ሳይሆን ቀርቷል።

ሆኖም በተጭዋቹ ዝውውር ላይ አሁን ከማን.ሲቲዎች ጋር መፎካከር ያለባቸው ሲሆን የኢትሃዱ ክለብ አሁን ባለው የተሟላ ቡድን ላይ የ26 አመቱን የፊት አጥቂ በመጨመር ቡድኑን ይበልጥ ተፈሪ ማድረግ ይፈልጋሉ።



NEYMAR WANTED TO CANCEL PSG TRANSFER


ብራዚላዊዉ ኔይማር ጁኔር ያለማችን ሪከርድ ዋጋ በመስበር ወደ PSG ከመዘዋወሩ በፊት ዝውውሩ እንዳይሳካ የባርሴሎናን ክለብ ፕሬዝዳንት የሆኑት ማርዮ ባርቶሚዮን ሁሉ ጠይቁዋቸው ነበር ሲል ማርካ ዘግቡዋል።

ነገር ግን የተጫዋቹ ወኪል እና አባቱ የሆኑት ኔይማር ጁኔር በመጨረሻም ዝውውሩን እንዲሳካ አድርገውታል ተብሎል።

ሁኖም ግን ኔይማር አሁንም በፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ የመቆየቱ ነገር አጠራጣሪ ነዉ፣ ምክንያቱም ከካቪኒ ጋር በገባዉ ሰጣ ገባ እንደ ታዉቆል።  (marca)

ይገምቱ ይሸለሙ - የሳምንቱን የፕሪሚየር ሊጉ ታላቅ ጨዋታ ከታች ባለው ሊንክ ገብተው ይገምቱ እና ከአይቴ ሞባይል ኢትዮጵያ ባለ 100ብር ካርዶችን ይሸለሙ ፦  goo.gl/fpMJxP

BAYERN WANT GIROUD


የጀርመኑ ክለብ ባየርሙኒክ አይኑን ወደ አርሰናሉ አጥቂ ኦሊቨር ዤሩድ አዙሮል።

ባባሪያኖቹ የሮበርት ሌቫንዶቪስኪ ተጠባባቂ እንዲሆንላቸው በማሰብ ፈረንሳዩን አጥቂ ለማስፈረም አስቦል ተብሎል::

ዤሩድ በክለቡ ያለዉ ቦታ በሀገሩ ልጅ አሌክስ ሳንደር ላካዚት መያዙ አላስደሰተዉ በዚህም ክለቡ ሊለቅ
ይችላል ተብሎል።    (daily mirror)



BETIS LOOK TO SIGN WILSHERE


የስፔን ላሊጋው ክለብ ሬያል ቤቲስ በአርሰናል ቤት ያልተረጋጋውን እንግሊዛዊዉ አማካይ ጃክ ዊልሻየርን
እንደሚያዘዋውሩት ተስፍ አድርገዋልተብሎል።

ዊልሸር በሳምንት £90,000  ሳምንታዊ ደሞዝ እየከፈሉት ሪያል ቤትስን ሊቀላቀል ይችላል ሲል፣ (marca) ዘግቧል።



ARSENAL WILL SWAP ALEXIS FOR STERLING


የፕሪሜር ሊጉ ክለቦች አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ ተጫዋቾችን ሊለዋወጡ ነዉ ተባለ።

በአርሰናል ቤት ያለዉን ኩንትራት ዉል እስካሁን አለማደሱ አሌክሲ ሳንቸዝ በክለቡ አርሰናል የመቆየት ፍላጎት እንደሌለዉ ያስታዉቃል ተብሎል። ሆኖም አርሰናል ሳንቸዝ የማቆየት አሳቡ የሚሳካ አይመስልም በዚህም አርሰናል ተጫዋቹን ዝም ብሎ ከሚሸጠዉ ይልቅ ለሚሸጠዉ ክለብ ዉስጥ በምትኩ እንግሊዛዊዉን ተጫዋች ራሄም ስተርሊንግ መግዛት ይፈልጋሉ።

ሆነም ቀረ አሌክሲሳንቸዝ በጥር ሲቲ የሚቀላቀል ከሆነ ስተርሊንግም አርሰናል የመቀላቀሉ ነገር እዉን ይሆናል ሲል ያስነበበዉ (marca) ነዉ።

Wednesday, November 15, 2017

ዕረቡ ምሽት ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



ARSENAL WANT FELLAINI


አርሰናሎች በክለቡ አዲስ ኮንትራቱን እስካሁን ያልፈረመው ቤልጂየማዊውን አማካይ ማርዋን ፌላይኒን ከማን.ዩናይትድ ማዛወር ይፈልጋሉ Calciomercato ዘገበ።

ቤልጂየማዊው ኢንተርናሽናል በክለቡ የመጨረሻ አመት ኮንትራቱ ላይ የሚገኝ ሲሆን የቱርኩ ክለብ ቤሺክታሾችም ሊያዛውሩት በጥብቅ ይፈልጋሉ።


MOYES WANTS DUNK AT WEST HAM


ማንቸስተር ዩናይትዶች ሉክ ሾውን በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ በ£20 million የዝውውር ሂሳብ ብቻ ሊሸጡት ይፈልጋሉ ያለን The Times ነው።

ሻው በተደጋጋሚ ግዜ ወደ ፌነርባቼ በውሰት ያመራል በሚል ሲወራ ቆይቷል። ሆኖም በጆዜ ሞሪንዎ የአሰልጣኝነት ዘመን ሙሉ ብቃቱን አውጥቶ የተጠቀመ ባለመሆኑ አሰልጣኙ ጋር ተቃቅሮአል። ተጭዋቹ ግን ወደ ቱርክ መዛወር አይፈልግም።


SELL WILLIAN, BUY LUCAS MOURA


ሰማያወቹ ቼልሲወች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ዊልያምን በመሸጥ የሀገሩን ልጅ ሉካስ ሞራን ከሊግ 1 ክለብ ፒኤስጂ ማስፈረም ይፈልጋሉ ሲል፣ የፈረንሳዩ ጋዜጣ (le10sport) አስነብቦል።

ቼልሲወች ወደ ቻይና ሱፐር ሊግ ያቀናል የተባለዉን ሉካስን ወደ እስኮዳቸዉ በመቀላቀል ወደ እስታንፎርድ ብሪጅ ሊያስኮበልሉት ይችላሉ ሲል፣ ሪፖርቱ le 10 sport ጨምሮ ዘግቧል።

ማስታወቂያ ፦ በታላቅ ቅናሽ ገዝተው! እዛው ስጦታዎችን ይውሰዱ
በአዲስ አበባ (መገናኛ እና ሳሪስ) ፣ ሀዋሳ፣ አዳማ፣ ጂማ፣ ሽሬ፣ ደብረ ማርቆስ፣ መቀሌ፣ ሀረር፣ ጎንደር እና ደሴ ከተማ ነዋሪ ነዎት? እንግዲያውስ በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናቶች አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ብቻ  የአይቴል S11 እና S31 ስልኮችን በታላቅ ቅናሽ ይግዙ! እንዲሁም ሲገዙ ልዩ ስጦታዎች ከአይቴል ሞባይል እዚያው ይውሰዱ! ለበለጠ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይጎብኙ  ፦  www.facebook.com/itelMobileEthiopia/


ARSENAL ABANDON LEMAR CHASE


የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የሞናኮውን የመስመር ተጫዋች ቶማስ ሌማርን የማስፈረም እቅዱን ሙሉ
ለሙሉ በመተው ወደ ሌሎች አማራጮችን እየተመለከተ ነው ተብሎል::


መድፈኞቹ ባለፈው በተዘጋው የክረምቱ የዝውውር
መስኮት ባለቀ ሰዓት ተጫዋቹን ለማዘዋወር £90
million ቢያያቀርቡም የሊግ 1 ሻምፕዮኖቹ ክለብ ሞናኮ ግን ውድቅ ማድረጋቸው አይዘነጋም ነበር።

ነገር ግን የስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና እና የኢንግሊዙ ሀያል ክለብ ሊቨርፑል አሁንም የ 22 አመቱ ፈረንሳያዊ አማካኝ ፈላጊ መሆናቸዉን፣ (mirror) ዘግቧል።


RB Leipzig 'lead Manchester United'


የጀርመን ቦንደስ ሊጋዉ ክለብ አርቢሊዝቢግ የቤኔፊካዉን ተጫዋች የሆነዉን ዩማሮ ኢምባሎን ለማስፈረም ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ፉክክር ገባ።

ፖርቹጋላዊዉ ወጣት ከዚህ ቀደም ብሎ ሪፖርቶቹ እንደአሉት ከሆነ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር በ€5 million ተስማምቶል ቢባልም።

ነገር ግን የቦንደስ ሊጋዉ ክለብ አርቢ ልዝቢግ የዝውውር ሂሳቡን ከፍ በማድረግ €11.6 million አቅርቧል።


በዚህም ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን ለማስፈረም ከ አርቢሊዝቢግ ከባድ ፉክክር ይገጥመዋል ተብሎል። (the star)


ማንችስተር ሲቲ ለረዥም ጊዜ በሚያቆይ የኩንትራት ዉል የሻልክ ዜሮ አራቱን የፊት አጥቂ ብሬል ኢምቦሎን ማስፈረም እንደሚፈልጉ ተነግሮል።  (Source: Daily Mail)


የባርሴሎና አጥቂ የሆነዉ ምህታተኛዉ አርጀንቲናዊዉ ተጫዋች ሊዩነል ሜሲ የቶተንሃሙን አጥቂ ዴሊ አሊን ከተቀናቃኛቸዉ ክለብ ከሆኑት ሪያል ማድሪድ ቀድመዉ ክለቡ ባርሴሎና ተጫዋቹን እንዲያስፈርሙት ተናግሮል።  (Source: Don Balon)


አንቶን ግሪዝማን ወደ ፒኤስጂ በማምራት ኔይማር ጁኔርን እና ከሀገሩ ልጅ ከሆነዉ ኬሊያን ሞፓፔ ጋር ተጣምሮ ሊጫወት ይችላል ተብሎል። (Source: Daily Mail)


የአትሌቲኮ ማድሪዱ አጥቂ ፈርናዶ ቶሬስ ወደ ፕሪሜር ሊጉ በመመለስ ሳዉዝሃምተንን ወይም ኒዉካስትልን ሊቀላቀል ይችላል ሲል፣ (Source: Daily Mirror) ዘግቧል።


ማንችስተር ዩናይትድ በ€77 million የዝውውር ሂሳብ የሪያል ማድሪዱን አማካኝ ስፔናዊዉን ተጫዋች የሆነዉ ማርኮ አሴንሶን ሊያስፈርሙ እንደሆነ ተነግሮል።   (Source: Don Balon)

በታላቅ ቅናሽ ገዝተው! እዛው ስጦታዎችን ይውሰዱ
በአዲስ አበባ (መገናኛ እና ሳሪስ) ፣ ሀዋሳ፣ አዳማ፣ ጂማ፣ ሽሬ፣ ደብረ ማርቆስ፣ መቀሌ፣ ሀረር፣ ጎንደር እና ደሴ ከተማ ነዋሪ ነዎት? እንግዲያውስ በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናቶች አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ብቻ  የአይቴል S11 እና S31 ስልኮችን በታላቅ ቅናሽ ይግዙ! እንዲሁም ሲገዙ ልዩ ስጦታዎች ከአይቴል ሞባይል እዚያው ይውሰዱ! ለበለጠ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይጎብኙ  ፦  www.facebook.com/itelMobileEthiopia/



የማንችስተር ዩናይትድ ተከላካይ ማቲዩ ዳሪሚያን በጣሊያን ሴሪያ ክለቦች ይፈለጋል ከክለቦቹ መካከል፦ ጁቬንትስ፣ ሮማ እና ናፖሊ ናቸዉ ተብሎል።  (Source: Gazzetta dello Sport)


ቦርሲያ ዶርትመንድ የሊቨርፑሉን ጀርመናዊዉ አማካኝ የሆነዉን ኤሜሪ ቻንን ማስፈረም ይፈልጋል ተብሎል።  (Source: Daily Mirror)


ሪያል ማድሪዶች በሚቀጥለዉ ክረምት የጋሬዝ ቤልን ተተኪ የሚሆን አዲስ ተጫዋች ከአሁኑ እያፈላለጉ ነዉ።   (Source: AS)


አንቶን ግሪዝማን በመጪዉ ክረምት የማንችስተር ዩናይትድን የዝውውር ጥያቄ የተቀበለ የይመስልም ምክንያቱም ወደ ፒኤስጂን ተቀላቅሎ መጫወት መፈለጉ ነዉ ተብሎል። (Source: Daily Star)


Tuesday, November 14, 2017

ማክሰኞ ምሽት ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች




RONALDO WANTS REAL EXIT


ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሪያል ማድሪድን መልቀቅ ይፈልጋል ሲል የስፔኑ ቴሌቭዥን ጣቢያ የሆነው Chiringuito TV ያልታሰበውን ዜና አፈንድቶታል።

ፖርቹጋላዊው ኢንተርናሽናል በቅርቡ ያለፈው አመት ምርጥ ብቃቱን መድገም የተሳነው ሲሆን የብቃት መውረድ ታይቶበታል። እስካሁን ድረስ ያስቆጠረውም አንድ የላ ሊጋ ጎል ብቻ ነው።

እናም ክርስቲያኖ ሮናልዶ ክለቡን ማድሪድ ጁን 30 ላይ መልቀቅ የሚፈልግ ሲሆን በሳንቲያጎ በርናባው የቀረበለትን አዲስ ኮንትራት አልቀበልም ብሎ ሳይፈርመው ቀርቷል።

ለአራተኛ ግዜ የባሎን ደኦርን ያሸነፈው ኮከብ ባለፈው ክረምት ላይ ክለቡን ለመልቀቅ ያቀረበው ጥያቄ በክለቡ ፕሬዝዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ ሳቢያ በሁለቱ ግለሰቦች መሃከል መቃቃር ተፈጥሮአል።



ATLETICO MAKE OZIL CONTACT


አትሌቲኮ ማድሪዶች የአርሰናሉን አማካይ አጥቂ ሜሱት ኦዚልን ለማስፈረም በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ሙከራ ለማድረግ ተሰናድተዋል ሲል የእንግሊዙ ጋዜጣ The Sun ዘገበ።

ጀርመናዊው ኢንተርናሽናል በክረምቱ መጨረሻ ላይ ከኮንትራቱ ሙሉ ለሙሉ ነፃ የሚሆን ሲሆን ተጭዋቹ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ከየትኛውም ክለብ ጋር ተደራድሮ ቅድመ ስምምነቶችን መፈራረም የንደሚችል ይታወቃል።

አትሌቲኮ ማድሪዶች ለኦዚል ሳምንታዊ የ£200,000 ደሞዝ ለመስጠት ፍቃደኞች የሆኑ ሲሆን ደሞዙ ምንም እንኳን ከፍተኛ ቢሆንም አርሰናሎች እንዲከፍሉት ከጠየቀው ሳምንታዊ የ£330,000 ደሞዝ ጥያቄ ያነሰ ሂሳብ ነው።

ኦዚል በግሉ ወደ ሪያል ማድሪድ ቢመለስ ደስተኛ የሚሆን ቢሆንም ከ2010 እስከ 2013 ድረስ የተጫወተበት ክለብ ግን ምንም አይነት የመመለስ ፍላጎት አላሳየም።



TOTTENHAM TURN TO RICHARLISON


ቶተንሃሞች የዋትፎርዱን የፊት መስመር ተጫዋች ሪቻርሊሰንን ለማስፈረም ጥያቄ ያቀርባሉ ሲል
Daily Mirror ዘግቦታል።

የ20 አመቱ አጥቂ ለሆርኔትሶች በዚህ የውድድር አመት ላይ በክረምቱ ቡድኑን ከተቀላቀለ በኃላ ድንቅ ብቃቱን እያሳያቸው ሲሆን ቶተንሃሞች የተጭዋቹን እድገትና ለውጥ በቅርበት ሆነው እየተከታተሉት ይገኛሉ።



ARSENAL CLOSE IN ON FEKIR


አርሰናሎች በ£60 million ፖውንድ የዝውውር ሂሳብ የሊዮኑን አማካይ አጥቂ ናቢ ፊከርን ለማዛወር ተቃርበዋል ሲል Daily Star ዘገበ።

መስፈኞቹ ከ24 አመቱ ፈረንሳዊ አማካይ ጋር ቀደም ብለው ንግግር ማድረግ የጀመሩ ሲሆን ተጭዋቹን ወደ ኤምሬትስ ለማዛወር የሚደረገው ድርድር በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ እንደሚጠናቀቅ ተስፋ አድርገዋል።

24-year-old fo እንደታሰበው ዝውውሩ የሚጠናቀቅ ክሆነም ከክለቡ ይለቃሉ የተባሉት አሌክሲስ ሳንቼዝ እና ሜሱት ኦዚል ከክረምቱ በፊት በጥር ወር ላይ ክለቡን መልቀቃቸው አይቀሬ መሆኑን ያረጋግጣል ተብሏል።



MAN UTD WANT ATLETICO STAR


ማንቸስተር ዩናይትዶች በበኩላቸው የአትሌቲኮ ማድሪዱን አማካይ ሳኡል ንጉዋዝን ማዛወር ይፈልጋሉ። ተጭዋቹ ግን በኮንትራቱ ላይ የ €150 million መልቀቂያ ሂሳብ ሰፍሮበታል ያለው The Sun ነው።

ጆዜ ሞሪንዎ በቡድናቸው ያለውን የጎል ፈጣሪነት ሚና ማሳደግ የሚፈልጉ ሲሆን በቀጣዩ ክረምት ላይ ስፔናዊውን ፈጣሪ አማካይ የቡድናቸው አካል ማድረግ ይፈልጋሉ።

ጆዜ ሞሪንዎ ከንጉዌዝ ዝውውር ጎን ለጎን ደግሞ አትሌቲኮ ማድሪዶች ከአማካያቸው አንደር ሄሬራ ላይ አይናቸውን እንዲያነሱና እንዳይነጥቋቸው የሚታገሉ ሲሆን በኮንትራቱ ላይ የሰፈረውን የአንድ አመት አማራጭ ውል ለማንቀሳቀስና ለተጨማሪ አመት እንዲቆይ ለማድረግ ይሞክራሉ።

Monday, November 13, 2017

ሰኞ ምሽት ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች




REAL OFFER BALE & KROOS FOR NEYMAR


የሪያል ማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ የፒ.ኤስ.ጂውን አጥቂ ኔይማር በክረምቱ ለማዛወር የቆረጡ ሲሆን በምትኩ ለፓሪሱ ክለብ ቶኒ ክሮስን እና ጋሬዝ ቤልን ለመስጠት አቅደዋል ያለው Don Balon ነው።


እንደ ሪፖርቱ ከሆነ ብራዚላዊውን ኮከብ አሁን ላይ ለማዛወር ባጠቃላይ የ€400 million, ሂሳብ የሚያስፈልግ ሲሆን ሪያሎች ግን ቤል እና ክሮስን በመስጠት ዋጋውን ለማውረድ አስበዋል።


ባሁኑ ሰአት PSGዎች ተጭዋቹን የመሸጥ ምንም አይነት ፍላጎት የላቸውም ሆኖም ማድሪዶች ተጭዋቹን በቀጣዮቹ ሁለት ሲዝኖች ውስጥ ለማዛወር ቆርጠዋል።



MADRID TARGET LYON STAR


የሊዮኑ አጥቂ ንምቢ ኪየታ በሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን ተቀዳሚ የዝውውር ኢላምን መሆን ችሏል ያለው ደግሞ SFR Sport ነው በAS በኩል።


ፌከር በዚህ የውድድር አመት ላይ በሊዮን ድንቅ ብቃቱን ያሳየ ሲሆን የ24 አመቱ ፈረንሳዊ ኢንተርናሽናል እንደ አጥቂም እንደ አማካይ አጥቂም ሆኖ መጫወት ይችላል። በባርሴሎናም መልማዮች ታይቷል።


አርሰናሎች፣ ጁቬንቱስ እና ማንቸስተር ዩናይትዶችም በፌከር ዝውውር ላይ ፍላጎት ያላቸው ሲሆን ሆኖም ግን ማድሪዶች በዚህ አመት እያሳየ ያለውን እንቅስቃሴ በአካል እየተከታተሉት ይገኛሉ።


BARCA TO RAISE UMTITI RELEASE CLAUSE TO €180M


ባርሴሎናዎች በማንቸስተር ዩናይትድ በጥብቅ እየተፈለገ ያለውን ተከላካይ ሳሙኤል ኡምቲትን በ2018 አመት መጀመሪያ ላይ አዲስ የተሻሻለ ኮንትራት ለማስፈረም አቅደዋል ሲል Sport ዘገበ።


የኡምቲት ባርሴሎና ኮንትራት የሚጠናቀቀው በ2021 ላይ ሲሆን በአመት የ€3 million ደሞዝ እየተከፈለው ይገኛል። በኮንትራቱ ላይ የ€60m ውል ማፍረሻም ተቀምጦአል።


በአዲሱ ኮንትራቱ ደሞዙን ለማሳደግ የታሰበ ሲሆን በዋነኛነት ከፈላጊ ክለቡ ማን.ዩናይትዶችን ለማሸሽ ሲባል አዲስ የ€180m ሂሳብ ውል ማፍረሻ ለማካተት ታቅዷል።



BARCA MIDFIELDER SET FOR NEW
DEAL


ባርሴሎናዎች አማካያቸውን ሰርጂ ሮቤርቶ አዲስ የአምስት አመት ኮንትራት ለማስፈረም እና ፈላጊ ክለቦቹን ሁለቱን የማንቸስተር ከተማ ክለቦች ሲቲ እና ዩናይትድ ለማሸሽ አቅደዋል ሲል Mundo Deportivo ዘገበ።


የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ሰርጂ ሮቤርቶን ማዛወር ይፈልጋሉ በሚል ስማቸው ከተጭዋቹ ዝውውር ጋር በተደጋጋሚ ግዜ ሲነሳ ቢቆይም የተጭዋቹ ውል የሚያበቃው በ2019 ላይ ነው።


ያም ሆኖ ግን የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦችን ለማሸሽ ባርሴሎናዎች ለተጭዋቹ አዲስ ኮንትራት ውል አቅርበው የውል ማፍረሻ ሂሳቡን ከ€40 million ሂሳብ ወደ €400m ሂሳብ ማሳደግ ይፈልጋሉ።



GORETZKA WANTS PREMIER LEAGUE
MOVE


የሻልካው አማካይ ሊዮን ጎረትስካ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች መዛወር የሚፈልግ ሲሆን በቀጣዩ አመት ከኮንትራቱ ሙሉ ለሙሉ ነፃ ይሆናል ብሏል Sport .


ጀርመናዊው ኢንተርናሽናል ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ኦሊቨር ቤይሮፍ እንዳሉት ከሆነ የእንግሊዝ ክለቦች እያቀረቡ ያሉት የዝውውር እና የደሞዝ ክፍያዎች የትኛውንም ተጭዋች ልብ የሚያሸፍቱ መሆናቸውን አምነው ተጭዋቹ የሪያል ማድሪድ ፤ ባርሴሎና እና ባየር ሙኒክ የዝውውር ኢላማ እንደሆነ ዘግበዋል።


ያም ሆኖ የ22 አመቱ ተጫዋች ከስፔን እና ከጀርመን ሃያል ክለቦች እየቀረቡለት ያለውን ጥያቄ ያልተቀበላቸው ሲሆን ፍላጎቱ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መዛወር ብቻ ነው ተብሏል። አርሰናል፤ ቶተንሃም፤ ሊቨርፑል እና ቼልሲ ከተጭዋቹ ዝውውር ጋር ስማቸው የተነሱ ክለቦች ናቸው።



MAN UTD TO SELL SHAW FOR £20M


ማንቸስተር ዩናይትዶች ሉክ ሾውን በ20ሚ.ፓ ሂሳብ ብቻ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ሊለቁት ፍቃደኞች ናቸው ብሏል የTimes ነው።


ሻው በቅርቡ ወደ ፌነርባቼ ቱርክ ሊያመራ ነው በሚል ሲወራበት የቆየ ሲሆን እርሱ ክን ወደ ኢስታምቡሉ ክለብ መዛወርን አይፈልግም። ዩናይትዶች ግን ግራ ተመላላሽ ተከላካዩን በቅናሽ የዝውውር ሂሳብ ለማዛወር ለመልቀቅ ፍቃደኞች ናቸው። ተከላካዩ እያሳየ ያለው ብቃት ጆዜ ሞሪንዎን አላሳመናቸውም ተብሏል።



CAN TO SNUB JUVE FOR CITY


ሊቨርፑሎች አማካያቸው ኤምሬ ካን የጣሊያኑን ክለብ ጁቬንቱስ ጥያቄ ችላ በማለት ወደ እንሊዙ ማንቸስተር ሲቲ ለመዛወር አስቧል ያለው Star ነው።


ጀርመናዊው ኢንተርናሽናል ካን በጁን ወር ላይ ከሊቨርፑል ኮንትራቱ ሙሉ ለሙሉ ነፃ ሲሆን ጁቬንቱሶች በነፃ የዝውውር ሂሳብ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ለማዛወር በጥር ወር ላይ  ከስምምነት እንደርሳለን የሚል ተስፋ ነበራቸው።


ሆኖም ጀርመናዊው ተጭዋች ካን ሊቨርፑል እና ጁቬንትስን ጥያቄ ችላ በማለት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መሪ ክለብ ማንቸስተር ሲቲ እንደሚያቀና ጠርጥረዋል።

Sunday, November 12, 2017

እሁድ ምሽት ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች




ARSENAL WANT ZAHA TO REPLACE
SANCHEZ


የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ለኮከባቸዉ ለአሌክሲስ ሳንቼዝ ተተኪ ይሆናል ያሉትን የክሪስታል ፓላሱን የአጥቂ መስመር ተሰላፊ አይቬሪኮስታዊዉን
ዊልፍሪድ ዛሃ እንደ አማራጭ ይዘውታል፡፡


የቺሊያዊው የአሌክስ ሳንቸዝ ኩንትራት በሚቀጥለው አመት የሚጠናቀቅ መሆኑን ተከትሎ አርሰን
ቬንገር ለአይቬሪኮስታዊው ኢንተርናሽናል £35
million አዘጋጅተዋል፡፡


ዛሃ በፓላስ ጥሩ ብቃቱን እያሳየ መሆኑ ተከትሎ አርሰኖሎች ሳንቸዝ ወደ ማን ሲቲ መሄዱ ካልቀረ ተጫዋቹን ማስፈረማቸዉ አይቀርም ተብሎል።
(The star)


BARCA TURNED DOWN AUBAMEYANG


ባርሴሎናዎች በክረምቱ የዝውውር መስኮት የቦርሺያ ዶርትመንዱን አጥቂ ጋቦናዊዉን ፔሬ ኤምሪክ ኦበምያንግ የማስፈረም እድል ቀርቦላቸው ነበር፡፡


ነገር ግን ኔይማር ፒኤስጂን መቀላቀሉን ተከትሎ የካታላኑ ክለብ ኦበምያንግን ለማስፈረም አማራጭ የቀረበለት ቢሆንም የ9 ቁጥር ቦታው በሉይስ ስዋሬዝ መያዙን ተከትሎ ሳያስፈርሙት ቀርተዋል፡፡


ሁኖም ባርሴሎና የሊዉስ ስዋሬዝ ብቃት መዉረድን ተከትሎ በጥር ተጫዋቹን በድጋሜ የእናስፈርም ጥያቄ ሊያቀርቡለት ይችላሉ ተብሎል።  (Mundo Deportivo).


CHELSEA EYEING UP €100M ICARDI


ቼልሲዎች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ
የኢንተር ሚላን ማውሮ ኢካርዲ የጠየቀውን የ€100 million የውል ማፍረሻ ለመክፈል ተዘጋጅተዋል ተብሎል፡፡


አርጀንቲናዊው አጥቂ በጣሊያን ክለብ ኢንተር ሚላን ጥሩ አቋም እያሳየ ሲሆን 11 ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፎአል፡፡


ቼልሲም የአጥቂ ክፍሉን ለማጠናከር ሲል ተጫዋቹን ሊያስፈርመዉ እንደሚችሉ የተለያዩ ሚዲያወች እየዘገቡ ነዉ።    (daily mirror)


JUVENTUS PLOTTING BELLERIN BID


የአምናዉ የጣሊያን ሴሪያዉ ሻንምፒዩኑ ክለብ ጁቬንትስ የአርሰናሉን ሁለገብ ተጫዋች የሆነዉን ስፔናዊዉን ወጣት ሄክቶር ቤለሪን ደጎስ ባለ የዝውውር ሂሳብ ለማዘዋወር አስበዋል።


ቤሌሪን በአርሰናል ጥሩ የሚባል ብቃት ላይ ይገኛል። በዚህም በተለያዩ ክለቦች አይን ዉስጥ መግባት ችሎል። ሁኖም ተጫዋቹ በክለቡ አርሰናል የመቆየቱ ነገር አሳሳቢ ነዉ ተብሎል ሲል tuttomercato ዘግቧል።


OTHER SHORT STORIES 


ሪያል ማድሪዶች በዌልሳዊዉ ጋሬዝ ቤል የጉዳት ችግሮች ምክንያት ተስፋ ቆርጠዋል ተብሎል፡፡
በዚህም ተጫዋቹን ለፈላጊ ክለቦቹ ለሆኑት፦
ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ቼልሲ ወይም ቶተንሃም
አሳልፈዉ ሊሰጡት ይችላሉ ተብሎል፡፡
(Mirror)


የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ተጫዋች የሆነዉ አማካኙ ኤምሪ ቻን ከጁቬንቱስ የሚቀርብለትን ጥያቄ በማስተባበል የሊጉን ተቀናቃኝ ማንቸስተር ሲቲ ሊቀላቀል ይችላል፡፡


ጀርመናዊው ኢንተርናሽናል ኩንትራቱ በሚቀጥለው
ክረምት የሚጠናቀቅ ሲሆን በነጻ የፔፕ ጋርዴወላዉን ክለብ ማን ሲቲ የመቀላቀል እድል ይኖረዋል ተብሎል፡፡ (mirror)


ቀያይ ሰይጣኖቹ ማንቸስተር ዩናይትዶች የ29 አመቱን ቤልጄማዊዉን አማካይ ማርዋን ፌላይኒ በጥሩ የዝውውር መስኮት ለቤኪሽታሽ በ£8m ለመሸጥ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል ተብሎል፡፡ ፌላይኒ በአሁኑ ሰአት በጉዳት ላይ ይገኛል።     (Mirror)


የካታሎኑ ክለብ ባርሴሎና በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በቀዳሚነት የአያክሳምስተርዳሙን ተከላካይ ማቲያስ ዲላይት ለማስፈረም ከአሁኑ ንግግር ሊያደርግ ነዉ፡፡የካታላኑ ክለብ ከጄራርድ ፒኬ ጋር ይመሳሰላል የሚባልለትን የ18 አመቱን ወጣት ለማስፈረም እየተመለከተ ቢሆንም ዳቪንሰን ሳንቼዝን ለቶተንሃም የለቀቀው አያክስ ተከላካዩን በቀላል ለባርሴሎና አሳልፎ ይሰጣል ተብሎ አይጠበቅም ተብሎል፡፡     (Mundo Deportivo)


ሪያል ማድሪዶች ብራዚላዊውን የፒኤስጂ አጥቂ ኔይማር በሚቀጥለው ክረምት የማስፈረም
እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡    (Marca)


በተያያዘ ዜና ኔይማር ሀገሩ ብራዚል ጃፓንን 3-1 ባሸነፈችበት የወዳጅነት ጨዋታ ላይ የምሳ ግብዣዉ ላይ ባልታወቀ ምክንያት አልታደመም ተብሎል። (indepedent)


የሌስተር ሲቲዉ ተጫዋች የሆነዉ ዴማራይ ግራይ የበፊቶቹን አሰልጣኞች የሆኑትን አሰልጣኝ ክላዉዲወ ራኔሪ እና ክሬድ ሼክስፔርን እንዲመለሱ እፈልጋለሁኝ ሲል ለፎክስ ገልፆል። (sky)

Saturday, November 11, 2017

ቅዳሜ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ግሬት ሳዉዚኬት ትናንት ጉዳት የደረሰበት ፊል ጆንስ ከሶስት እስከ አራት ሳምንት ከጨዋታ ያርቀዋል ብሎል።    (source፦ daily mail)



”የፒኤስጂዉ አጥቂ ኬሌያን ሞፓፔ ስለ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ስለ ሊዩነል ሜሲ የሚበልጠዉን ሲናገር እንዲህ አለ ሮናልዶ የእኔ አይዶል ነዉ። ሜሲ ግን የአለማችን ምርጥ ተጫዋች ነዉ ሲል ተናግሮል። (the star)



የሊቨርፑሉ ጨዋታ አቀጣጣይ ፊሊፕ ኮንቲኒሆ እኔ ለባርሴሎና እንጂ ለፒኤሲጂ አልፈርም ብሎል። (Sport via Daily Mail)





የቶተንሃሙ አሰልጣኝ ማዉሪሾ ፑቺቲኖ የዌስታሃም ዩናይትዱን አርጀንቲናዊዉን አጥቂ ማኑየል ላንዚኒ ማስፈረም ይፈልጋሉ።    (Mirror)



የአርሰናሉ ሁለገብ ተጫዋች የሆነ ሄክቶር ቤሌሪን በጣሊያኖ ክለብ ጁቬንትስ በጥብቅ ይፈለጋል። ያለዉ።    (Sun)



የፈረንሳዩ ክለብ ፓሪሴን ጄርሜን የባርሴሎናዉን ተከላካይ የ33 አመቱን ጃቪየር ማሻራኖን የማስፈረም ፍላጎት አሳይቶል። (Diario Gol via Talksport)



የቼልሲዉ አጥቂ ስፔናዊዉ አልቫሮ ሞራታ ወደ ቀድሞዉ ክለቡ ሪያል ማድሪድ እንደሚመለስ ተስፋ አደርጋለሁኝ ሲል ተናግሮል።   (Mirror)



የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቾች የሆኑት፦ ዩን ማታ፣አንድሬ ሄሬራ፣አሽሊ ያንግ እና ዳኒ ብሌንድ በክለቡ ያላቸዉ ኩንትራት በቀጣዩ ክረምት ይጠናቀቃል።   (Telegraph)



የማንችስተር ሲቲዉ አጥቂ ጋብሬል ጀሰስ ጠንክሬ በመስራት ለ2018 የሩሲያ የአለም ዋንጫ በብሄራዊ ቡድኑ ቦታ ማግኘት እፈልጋለሁኝ ብሎል። ጀሰስ ሀገሩ ብራዚል በወዳጅነት ጨዋታ ጃፓንን 3፣1 ስታሸንፍ በጨዋታዉ ጎል ማስቆጠር ችሎል። (Goal)



የመርሲሳይዱ ክለብ ኤቨርተን የበርንላዩን አሰልጣኝ የሆነዉ ሳን ዱችይን ወደ ጉዲሰን ፓርክ ማምጣት ይፈልጋሉ ተብሎል። (Daily Mirror)



የባየርሙኒኩ ተጫዋች የሆነዉ ቲያጎ አልካንትራ ወደፊት ወደ እናት ክለቡ ባርሴሎና መመለስ እንደሚፈልግ ተናግሮል። ስፔናዊዉ አማካኝ አሁን በጀርመን ደስተኛ ነኝ ብሎል። (Sun)


የ25 አመቱ ብራዚላዊ አጥቂ ኔይማር ባርሴሎናን ለቆ ወደ ፈረንሳዩ ሃብታም ክለብ ፒ.ኤስ.ጂ ከተዛወረ በኃላ በክለቡ ደስተኛ እንዳልሆነና በክረምቱ እንደሚለቅ መነገሩን አስመልክቶ ሲጠየቅ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ እንባ ቀድሞት ታይቷል።  (Mirror)



የአስቶን ቪላው ቴክኒካል ዳይሬክተር ስቲቭ ራውድ ቀጣዩ የአርሰናል ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ይሆናሉ በሚል ግምት ተሰጥቶአቸዋል።   (Daily Mail)



የአርሰናሉ አሰልጣኝ አርሰን ዌንገር የ28 አመቱን ቺሊያዊ አጥቂ አሌክሲስ ሳንቼዝ በ24 አመቱ ጀርመናዊ የፒ.ኤስ.ጂ አማካይ ዩሃን ድራክስለርን ወደ ኤምሬትስ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ማዛወር ይፈልጋሉ።     (Daily Star)



የባርሴሎናዉ ተጫዋች ምትሀተኛዉ ሊዩነል ሜሲ ባለፉት ጨዋታወች 506 ሹት በላሊጋ አድርጎል።ከሱ በተቃራኒ የምንግዜም ተቀናቃኙ የሪያል ማድሪዱ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በስሌት ደረጃ በጣም ያነሰ ሆኖል።     (Daily Mail)



ብራዚላዊዉ ኮከብ ኔይማር ጁኔር በፈረንሳዩ ክለብ ፖሪሴንት ጀርሜን ደስተኛ አለመሆኑ ትናንት ባደረገዉ ቃለ መጠየቅ ላይ ምላሽ ሲሰጥ ሲያለቅስ ታይቶል። (Mirror)



አትሌቲኮ ማድሪድ የማንችስተር ዩናይትዱን አማካኝ አንድሬ ሄሬራን ለማስፈረም ፍላጎት አሳይተዋል። ሄሬራ በክለቡ ያለዉ ኩንትራት በክረምቱ መጨረሻ ያበቃል።    (AS via Daily Mirror)



ብራዚላዊዉ የ25 አመቱ ኮከብ ኔይማር ሪያል ማድሪድን ሊቀላቀል ይችላል ተብሎል። ምክንያቱም ፒኤስጂ የቼልሲዉን አጥቂ አልቫሮ ሞራታን ሊያስፈርሙ ማሰባቸዉን ተከትሎ ነዉ ተብሎል። (Goal via El Larguero)



የክርስቲያን ፓላሱ አሰልጣኝ ሮይ ሆድሶን የአርሰናሉን አማካኝ ጃክ ዊልሸርን በጥር ወር የዝውው መስኮት ለማስፈረም እንደሚፈልጉ ተናግረዋል ሲል The
Telegraph ዘግቧል።

Friday, November 10, 2017

አርብ አመሻሽ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



✔  PSG LINE UP CONTE


PSGዎች በቻምፒየንስ ሊጉ ላይ ግማሽ ፍፃሜ መድረስ የማይችሉ ከሆነ አሰልጣኙን ለመቀየር ወስነዋል። እናም የቼልሲው አለቃ አንቶኒዮ ኮንቴ የክለቡ ባለቤቶችን ቅድመ ሁኔታ የሚያሟሉ ናቸው ብሏል Le Parisien.



ምንም እንኳን ጣሊያናዊው አሰልጣኝ በስታምፎርድ ብሪጁ ክለብ የሚያቆየው ኮንትራት እስከ 2019 ያለው ቢሆንም ከባለስልጣናቱ ጋር ተቃቅሮአል።


በሌላ በኩል ደግሞ የኡናይ ኢምሬ የሊግ ዋኑ ኮንትራታቸው በቀጣዩ ክረምት ላይ ኤክስፓየር የሚያደርግ ይሆናል። ምንም እንኲን በሊጉ እስካሁን ምንም ሽንፈት ባይደርስበትም የመባረር ጫና ውስጥ ይገኛል።




✔   BARCA MAKE £105M COUTINHO BID


ባርሴሎናዎች የሊቨርፑሉን አማካይ ፊሊፕ ኩቲንዎን ለማዛወር የ£105 million ሂሳብ አቀረቡ ያለን የስፔኑ እትም  Sport ነው።


የካታላኑ ክለብ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ኩቲንዎን ለማዛወር ያልተሳካ ሙከራ አድርገው ከሽፎባቸዋል። አሁን ግን ብራዚላዊውን ተጭዋች ለማስፈረም የተሻሻለ ሂሳብ በመያዝ በድጋሚ ሙከራ ለማድረግ ተሰናድተዋል።



እንደ ሪፖርቱ ከሆነ ምንም እንኳን ሊቨርፑሎች በተደጋጋሚ ግዜ ከባርሴሎና የቀረበላቸውን ሂሳብ በክረምቱ ውድቅ ቢያደርጉትም በቀጥታ የ £132m ሂሳብ የሚቀርብላቸው ከሆነ ግን ሊለቁት ይችላሉ።


✔   ARSENAL SET OZIL ASKING PRICE



አርሰናሎች ብፕጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ሜሱት ኦዚልን ለመልቀቅ የ£30 million ሂሳብ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ ብሏል Daily Star ጋዜጣ።


መድፈኞቹ ጀርመናዊውን አማካይ ለመሸጥ ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ኮንትራቱ በ2017-18 አመት ላይ ይጠናቀቃል ተብሏል። እናም የማንቸስተር ዩናይትዱ አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ በሪያል ማድሪድ ሳለ ያሰለጠነውን አማካይ ወደ ኦልትራፎርድ በማዛወር በድጋሚ አብሮት መስራት ይፈልጋል።


✔   MAN UTD AGREE DEAL FOR EMBALO



ማንቸስተር ዩናይትዶች የቤኔፊካውን ታዳጊ ኮከብ ኡማሮ ኢምቦሎን ከወዲሁ ለማዛወር ቅድመ ስምምነት ላይ ደረሱ ብሏል Mirror .


የ16 አመቱ የቀኝ ክንፍ ተጫዋች በዚህ አመት በተደረጉ የፖርቹጋል ከ17 አመት በታች 18 ጨዋታዎች ላይ 15 ጎሎችን በማስቆጠር የበርካታ ትላልቅ አውሮፓ ክለቦችን ትኩረት መሳብ ችሎ ነበር። ያም ሆኖ ተጭዋቹ እስካሁን ድረስ ምንም የፖርቹጋል ፕሪሚየር ሊጋ ጨዋታ አላረገም።


✔   BARCELONA SCOUTING FEKIR



ባርሴሎናዎች የሊዮኑን የፊት መስመር ተጭዋች ናቢ ፊከር እድገት ሁኔታ በቅርበት ሆነው እየተከታተሉት ይገኛል ያለው ደግሞ Marca ነው።


የ24 አመቱ ተጭዋች በዚህ የውድድር አመት ላይ ለሊግ ዋኑ ክለብ ድንቅ ብቃቱን እያሳየ ሲሆን የባርሴሎናው ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ሮበርት ፈርናንዴዝ ሊዮኖች በዩሮፓ ሊጉ ኤቨርተንን ሲያሸንፉ በአካል ተገኝተው ገምግመውታል።


የካምፕ ኑው ግዙፍ ክለብ ለተጭዋቹ ዝውውር ጥያቄ ለማቅረብ የተሰናዱ ሲሆን ከፊሊፕ ኩቲንዎ ይልቅ በቀላሉ እንደሚያገኙትም ያስባሉ።


✔  OTHER SHORT STORIES




▶ ፖል ፖግባ ፣ ማይክል ካሪክ እና ማርኮስ ሮሆ ከማንቸስተር ዩናይትድ ሁለተኛው ቡድን ጋር ልምምድ ሰርተዋል።      [ESPN]


▶ ዌስትሃም ዩናይትዶች በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ የበርንማውዙን ሃሪ አርተር እና በክረምቱ ጠይቀውት የነበረውን ደግሞ ዊልያም ካርቫልዮ ለማዛወር ጥያቄ ያቀርባሉ።    (Source: Daily Mirror)


▶ ክሪስታል ፓላሶች አሰልጣኝ ሮይ ሆድሰን የአርሰናሉን አማካይ ጃክ ዊልሸር በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ለማስፈረም ጥያቄ ያቀርባሉ።   (Source: Telegraph)


▶ ባየር ሙኒኮች የኢንተር ሚላኑን አጥቂ ማውሮ ኢካርዲን ለማዛወር የሚደረገውን ፉክክር ከአርሰናል እና ቼልሲ ጋር ተቀላቅለዋል።     (Source: Don Balon)


▶ ታዋቂው የኢንተርኔት ኦንላየን ሽያጭ ተቋን Amazon በማንቸስተር ሲቲ ከመጋረጃው ጀርባ የሚሰሩ ተከታታይ የዶክመንተሪ ፊልሞች ስራ ላይ ለክለቡ ቢያንስ የ£10m ሂሳብ ለመክፈል ተስማምተዋል።     (Source: tariqpanja )


▶ ማንቸስተር ሲቲዎች ለብራዚላዊው አጥቂ ገብርኤል ሄሱስ አዲስ ሳምንታዊ የተሻሻለ የ£100,000 ደሞዝ ሊከፍሉትሽያሰቡ ሲሆን ሳምንታዊ የ£30,000 ጭማሪ ያለው ነው።   (Source: Daily Mail)


▶ ሰርጂዎ አጉዌይሮ በ2019 የውድድር አመት ላይ ማንቸስተር ሲቲን በመልቀቅ ወደ አሳዳጊ ክለቡ ኢንዲፐንዴንቴ እንደሚመለስ ተናገረ።
(Source: Daily Mirror)

Thursday, November 9, 2017

ሃሙስ አመሻሽ ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



⃣  MOU TO LEAVE MAN UTD FOR PSG


ማንቸስተር ዩናይትዶች በክረምቱ ጆዜ ሞሪንዎ ክለቡን በመልቀቅ ወደ ፈረንሳዩ ሃብታም ክለብ ፒኤስጂ እንደሚያመሩ እርግጠኞች ሆነዋል ሲል The Sun ዘገበ።


ምንም እንኳን የፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ወገን ሰዎች የሞሪንዎን የፓሪስ ዝውውር ወሬዎች ቢያጣጥሉአቸውም የክለቡ ሰዎች ግን ሰውዬው የፔፕ ጋርዲዮላውን ቡድን በዝውውርም ሆነ በቡድን ግንባታ በልጦ የመፎካከር አቅም እንደሌለው ስለተረዳ የቀድሞው የቼልሲ እና ሪያል ማድሪድ አለቃ ክለቡን በመልቀቅ ሊሄድ እንደሆነ ስጋት አድሮባቸዋል።


ከሦስተኛው አዲሱ ክለቡ ጋር እንዲሁ የቻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ የማሸነፍ እድል እንደሌለው ያስባል። ይሄንን ህልሙን ከበቂ የዝውውር ባጀት ጋር ሊያቀርብለት የሚችለው እና ቻምፒየንስ ሊጉን ሊያሸንፍ የሚረዳው ቡድን የፈረንሳዩ ሃብታም ክለብ ብቻ እንደሆነም ያምናል።


⃣   Sponsored By ዜናዎቹን ስፖንሰር ያደረገላችሁ ..



⃣   MAN UTD TRACKING ARTHUR


ማንቸስተር ዩናይትዶች የግሬሚዮውን አማካይ አርቱር ሜሎ ለማስፈረም እየተከታተሉት ይገኛሉ ሲል Daily Mail ዘገበ።


የ21 አመቱ ብራዚላዊ በዚህ አመት ምርጥ ብቃቱን እያሳየ ያለ ሲሆን በኦክቶበር ወር ላይ ብሄራዊ ቡድኑ ለሚያደርገው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ ቡድኑን እንዲቀላቀል ጥሪ ተደርጎለታል።


ያም ሆኖ ማንቸስተር ዩናይትዶች ተጭዋቹን ለማስፈረም ገፍተው የሚሄዱ ከሆነ ከቼልሲ፣ ባርሴሎና እና አትሌቲኮ ማድሪድ ፉክክር ይጠብቃቸዋል ተብሏል።





⃣   MAN UTD MONITORING BARCA'S UMTITI


ጆዜ ሞሪንዎ የተዳከመውን የተከላካይ ክፍል ለማደስ ሲሉ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ የባርሴሎናውን ተከላካይ ሳሙኤል ኡምቲትን እየተከታተሉት ነው ብሏል  Mirror  ጋዜጣ።


ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ የቡድኑን የተከላካይ መስመር ለማጠናከር ጠንካራ ፍላጎት ያላቸው ሲሆን ምንም እንኳን ኤሪክ ቤይሊን ለማጣመር በሚል በክረምቱ የ£30 million ሂሳብ በማውጣት ከቤኔፊካ ያዛወሩት ተከላካይ ቪክተር ሊንደሎፍ ሊጉን መልመድ ተድኖት ከዋናው ቡድን ውጪ እስከመደረግ ደርሷል።


⃣   ZIDANE MAKES HAZARD NO.1 TARGET



የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ዚነዲኔ ዚዳን የቸልሲዉን ጨዋታ ቀማሪ ኤደን ሀዛርድን በቀጣዩ ክረምት የማስፈረም ተቀዳሚ አማራጭ አድርገዉታል ተብሎል።


ብዙም ታማኝነት የሌለዉ የስፔኑ ጋዜጣ ዶን ባሎን የማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ በምርጥ ተጫዋቾች ላይ አይናቸዉን ማሳረፋቸዉ ተከትሎ
አሁን ደግሞ ወደ ቼልሲዉ ኮከብ ኤደን ሀዛርድ ላይ ፊታቸዉን አዙረዋል።


ዚዳንም የአጥቂዉ ክፍላቸዉ መዳከሙን ተከትሎ የአጥቂያቸዉን ቦታ ተጫዋቾች ተተኪ ከአሁኑ ለማስፈረም ስራቸዉን ጀምረዋል።


ዛዳንም ከዚህ ቀደም የቶተንሃሙን አጥቂ ሄሪ ኬንን የኮከባቸዉ ክርስቲያኖ ተተኪ ለማድረግ እንቅስቃሴ ላይ ነዉ። በተጨማሪም ደግሞ የጁቬንትሱን ኮከብ
አርጀንቲናዊዉ ፖዉሎ ዲባላን የጋሬዝ ቤል ተተኪ በማድረግ ወደ በርናባዉ መዉስድ ይፈልጋሉ።


ሁኖም ግን አሁንም በዚህ ሳያበቃ ቤልጄማዊዉ ኮከብ ኤደን ሀዛርድን የካሬም ቤንዜማ ተተኪ እንዲሆንላቸዉ በማሰብ እናስፈርምህ ሊሉት ከተጫዋቹ ጋር ንግግር ሊያደርጉ ነዉ ተብሎል።


ማድሪድ ኮከቦቹን ወደ ስፔን ለመዉስድ ከአሁኑ በቅርበት ሁነዉ እንቅስቃሴወቻቸዉን በጥንቃቄ ይተከታተሉ ነዉ ሲል Don Balon ዘግቧታል።


⃣   BARCA & MADRID TARGET TO COST AT LEAST €30M


የላሊጋዉ ክለቦች ባርሴሎና እና ሪያል ማድሪድ የፊላሚኒጎዉን ወጣት ተጫዋች ላይ አነጣጥረዋል፣ ሁኖም ተጫዋቹን ሊንኮልን በ€30 million ለማስፈረም ተፋጠዋል።


ማርካ እንዳለዉ ከሆነ በህንድ አስተናጋጅነት የተካሄደዉ ከ17 የአለም ዋንጫ ላይ ተሰልፎ ለሀገሩ ብራዚል ጥሩ ብቃቱን ያሳየዉ ሊንኮልን በፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር በ€45 million ስምምነት ሊያደርግ ተቃርቦ የነበረ ቢሆንም ሳይፈርም ቀርቶል። ሁኖም የክለብ ጎደኛዉን ቪኒኪዩስ ጁኔርን ተከትሎ በአሁን ባለበት ክለብ ፍላሚንጎ ቀርቶል።


ከአሁኑ በሁለት ትልልቅ ክለቦች የእናስፈርም ጥያቄ ለልጁ ጥሩ እድል ነዉ ተብሎል ምክንያቱም ከወዲሁ በወጣትነቱ እዉቅናን ያተርፋል ተብሎል።   (Marca)



⃣   MOYES TO ADD TWO TO FOUR IN JANUARY


ከሁለት ቀን በፊት የለንደኑን ክለብ ዌስታሃም ዩናይትድን የተረከቡት አሰልጣኝ ዳቪድ ሞይስ በጥር ሁለት እና አራት ተጫዋቾች ማስፈረም እንደሚፈልግ
ተናግሮል።


ጋዜጣዉ ኢቪኒግ እስታንዳርድ እንዳለዉ ከሆነ ሞይስ የክለቡን ጥልቀት ለማስፋት ሲል የግድ ተጫዋቾችን ማስፈረም አለበት ተብሎል። ሁኖም ዳቪድ ሞይስ ተጫዋቾቹ የሚያስፈረም ደግሞ ከቀድሞ ክለቦቹ ከሆኑት ማንችስተር ዩናይትድ እና ኤቨርተን ነዉ። ሞይስ ከቀድሞ ሁለቱ ክለቦቹ በዛ ያሉ ተጫዋቾችን በጃቸዉ ማስገባት እንደሚፈልጉ ጋዜጣዉ Evening standard  ጨምሮ ዘግቧል።


⃣   MAN CITY PREP MILINKOVIC-SAVIC BID


ማንችስተር ሲቲ የላዚወን አማካኝ ሚሊንኮቪች ሳቪክን በጥር ለማስፈረም ተዘጋጅተዋል።


ሰርቢያዊዉ አማካኝ ሳቪክ በሌሎች ክለቦችም ይፈለጋል። ከክለቦቹ መካከል፦ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ጁቬንትስ እና ሪያል ማድሪድ ይገኙበታል።


ማንችስተር ሲቲ ተጫዋቹን በፈረንጆች አዲስ አመት በጥር ወር  ላይ ለማስፈረም ከአሁኑ ከክለቡ ጋር ንግግር ጀምረዋል ተብሎል።   (Source፦ Sky sport)


⃣   JACK WILSHER WANTED TO STAY



"ባሁን ሰአት ትኩረት ያደረኩት አሁን ባለኝ ቀሪ ኮንትራት ላይ ብቻ ነው። የወደፊቱ በራሱ ግዜ ይስተካከላል። ማድረግ ያለብኝ ከጉዳት ነፃ መሆን ብቻ ነው። በአርሰናል መቆየት እፈልጋለሁ። ይሄንን ለብዙ ጊዜያቶች ያህል ተናግሬዋለው። ወደ ሙሉ የአካል ብቃት ጥንካሬዬ የመጣሁት ገና አሁን ነው። አሁን ባለሁበት ክለብ እጅግ በጣም ደስተኛ ነኝ። በብልሃት እየተጫወትኩ ነው ያለሁት። ወደ ዋናው ቡድን ቋሚ ተሰላፊ ለመሆን እየሞከርኩ ነው በፕሪሚየር ሊጉሽተሰልፌ መጫወት እፈልጋለሁ።"   -  ጃክ ዊልሸር ስለ አርሰናል ቆይታው።


⃣   OTHER SHORT TRANSFER NEWS





ሪያል ማድሪዶች የቶተንሃሙን አጥቂ ሃሪ ኬን በማስፈረም የካሪም ቤንዜማ ተቀዳሚ ተመራጭ ተተኪው ሊያደርጉት ይፈልጋሉ።   (Source: Diario Gol)


አርሰናሎች ስሙ በተደጋጋሚ ግዜ ከማንቸስተር ዩናይትድ ዝውውር ጋር እየስተነሳ ያለውን ጀርመናዊ አማካይ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ የሚለቁት ከሆነ ለዝውውሩ የ£30m ሂሳብ ይጠይቃሉ።   (Source: Daily Star)


ፓሪሰን ዥርሜዮች የኤሲ ሚላኑን ታዳጊ ግብ ጠባቂ ጂያንሉጂ ዶናሩማ ማስፈረም ይፈልጋሉ።
(Source: TuttoMercatoWeb)


አትሌቲኮ ማድሪዶች የክለባቸውን ኮከብ አንቶኔ ጋሬዝማንን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ በ€100m የውል ማፍረሻው ሂሳብ ሊሸጡት ይችላሉ።   (Source: AS) 

Wednesday, November 8, 2017

ዕሮብ ምሽት ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች

P
MAN UTD WON'T RECALL PEREIRA እንደ Superdeporte ሪፖርት ከሆነ ቫሌንሺያዎች በውሰት ከማንቸስተር ዩናይትድ የወሰዱት አማካይ አንድሪያስ ፔሬራ በእናት ክለቡ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ እንደማይወሰድባቸው ተማምነዋል ብሏል። ዩናይትዶች ልጁን በውሰት ሲሰጡት ውሉ ላይ ከፈለጉት በጥር የመውሰድ መብትን ያካተቱበት ቢሆንም ቫሌንሺያዎች በላሊጋው ጥሩ ብቃት እያሳየላቸው የሚገኘውን የክንፍ ተጫዋች ዩናይትዶች መልሰው እንደማይወስዱባቸው ተስፋ አድርገዋል።
MOU TOLD TO SELL BEFORE BUYING ጆዜ ሞሪንዎ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ አዳዲስ ተጫቾችን ማዛቀር የሚፈልግ ከሆነ በቅድሚያ በቡድኑ ውስጥ ያሉ አላስፈላጊ ተጭዋቾችን መሸጥ እንዳለበት በክለቡ ተነግሮአቸዋል ሲል የዘገበው BBC ነው። የኦልትራፎርዱ ክለብ የሰሞዝ ክፍያ ጣሪያ ከባለፈው አመት በ13.5% ጭማሮ እንዳሳየ የፋይናንስ ሪፖርቶች የጠቆሙ ሲሆን የክለቡ ቦርድ አዳዲስ ተጭዋቾች ቡድኑን ከመቀላቀላቸው በፊት የደሞዝ ወጪ ቢሉ አሁን ካለበት እንዲወርድ ይፈልጋሉ። ሪፖርቱ አክሎ እንደገለፀው ከሆነ በ2014 የዝውውር መስኮት ላይ በ£27 million ሂሳብ ቀያዮቹ ሰይጣኖችን የተቀላቀለው ሉክ ሾው ክለቡን የሚለቅ የመጀመሪያው ተጭዋች ይሆናል።
MADRID LINE UP MATA BID ሪያል ማድሪዶች የማንቸስተር ዩናይትዱን አማካይ ዩሃን ማታ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለማስፈረም ጥያቄ ያቀርባሉ ሲል Express ጋዜጣ ዘገበ። ማታ ቡድኑ ባደረጋቸው የቅርብ ጨዋታዎቹ ላይ ቋሚ ተሰላፊ መሆን ያልቻለ ሲሆን ኮንትራቱ በዚህ ክረምት ላይ የሚጠናቀቅ በመሆኑ ዩናይትዶች በነፃ ዝውውር በሲዝኑ መጨረሻ ላይ ከሚለቅባቸው በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ በመሸጥ ከ29 አመቱ ስፔናዊ ዝውውር ገንዘብ ሊያገኙበት ይፈልጋሉ ተብሏል። ማታ በማድሪድ ታዳጊዎች ሲስተም ውስጥ ሰልጥኞ ያለፈ ተጫዋች ሲሆን ወደ ልጅነት አሳዳጊው ክለብ በርናባው መመለስን ይፈልግ ይሆናል ሲክ ዘገባው አካሏል።
BARCA PLAN JANUARY CLEAR OUT ባርሴሎናወች ተዘጋጅተዋል በጥር 3 ተጫዋቾች ለመሸጥ። ባርሴሎና በአሁኑ ሰአት በጉዳት ምክንያት ክለቡን እያገለገለ እማይገኘዉን አርዳ ቱራን በጥር ለሌላ ክለብ ለመሸጥ አስበዋል። እንዱሁም አሰልጣኝ ኤርኔስቶ ቫልቬርዴ ሌሎኞችን ቶማስ ቨልማሪን እና አሌክስ ቪዳል ለመሸጥ ማሰባቸዉን ገልፀዋል። ቫልቬርዴም ሁለቱን ቪዳልን እና ቨርማሊን የመሸጡ ምክንያት የተባለዉ ደግሞ በክረምቱ ያስፈረሙት ፖርቹጋላዊዉ ኔልሰን ሲሞዲ እና ጥሩ ብቃቱን እያሳየ የሚገኘዉ ስፔናዊዉ ሰርጆ ሮቤርቶ ቦታቸዉ መያዙ ነዉ ተብሎል። በዚህም 3 ተጫዋቾች ካፕኑን ለቀዉ መሄዳቸዉ አይቀርም ተብሎል። (the Sun)
DE LIGT TOPS BARCA WISHLIST ባርሴሎና የ18 አመቱን የአያክስ አምስተርዳሙን ተከላካይ ማቲጅስ ዲሊጊትን በቀጣዩ ክረምት ለማስፈረም አስበዋል። ሪፖርቱ ሙንዶቭ ዲፖርቲቮ እንዳለዉ ከሆነ ታዳኒዉን ተጫዋች ለማስፈረም ባርሴሎና የልጁን እንቅስቃሴ ከስር ከስር የተከታተሉት ነው ተብሎል። በተያያዘ ዜና ባርሴሎና የፖላ ሜራዉን ወጣት ተጫዋች ዩሪይ ሚናን ወደ ላ ሊጋዉ ለማምጣት ማሰባቸዉን ጋዜጣው ጨምሮ ዘግቦታል። (mundov deportivo)
Sponsored By
PSG TO SELL £70M DUO IN JANUARY የፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ፒኤሲጂ ከመግዛት ወደ መሸጥ ተዘዋዉሮል። ፖሪሴንት ጀርሜን አርጀንቲናዊዉ አጥቂ አንጂል ዲ ዲማሪያን እና ብራዚላዊዉ ሉካስ ሞራን በ€70 million የዝውውር ሂሳብ በጥር የዝውውር መስኮት ለመሸጥ ተዘጋጅቶል ተብሎል። የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤሲጂዎች ቅርብ ሰው እንዳለዉ ከሆነ ሁለቱ ተጫዋቾች በመጠነኛ እና በተመሳሳይ ዋጋ ለመሸጥ እንዳሰቡ ተናግረዋል። ሁኖም ሁለቱ ተጫዋቾች በትልልቅ ክለቦች ይፈለጋሉ በዚም የጨዋታ አቀጣጣዩ አንጅል ዲ ማሪያ በስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና በጥብቅ ይፈለጋል ተብሎል። አርጀንቲናዊዉ በክረምቱ ለባርሴሎና ይፈርማል ቢባልም ሳይፈርም መቅረቱ ይታወሳል። ሁኖም አሁን በድጋሜ ዲማሪያም በጥር ወር የካታሎኑን ባርሴሎና ይቀላቀላል ተብሎ ይታሰባል። ሌላኛዉ ብራዚላዊዉ ኮከብ ሉካስ ሞራ በክለቡ በተደጋጋሚ ቦታ ማግኘት አልችል ብሎ ቆይቶል። ሁኖም ሉካስ በጥር ሰማዩችን ቼልሲወችን ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል ሲል Sky sport ዘግቧል።
OZIL DEMANDS WILSHERE'S NO.10 SHIRT ሜሲት ኦዚል በአርሰናል ቤት እንድቆይ ከፈለጋቹህ የጃክ ዉሊሼርን 10 ቁጥር መለያ ማሊያ ስጡኝ ብሎል። የ10 ቁጥርን መለያ ማይሰጡት ከሆነ ክለቡን እለቃለሁኝ ብሎል። ካለበለዚያ ጀርመናዊዉ ኢንተርናሽናል አርሰናልን ለቅቄ ወደ ማንችስተር ዩናይትድን በመቀላቀል የ10 ቁጥር መለያ አገኛለሁኝ ሲል ለክለቡ ሰዎች ነግሮአቸዋል ተብሎል። ኦዚል እስከ ሲዝኑ መጨረሻ በአርሰናል አዲስ ኩንትራት የማይፈርም ከሆነ ፍላይ ኤምሬትስን ለቆ ማንችስተር ዩናይትድን መቀላቀሉ አይቀርም ተብሎል። (daily mail)  
ፀሐፊ፦ ሙሴ አማረ አዘጋጅና አርታኢ፦ መንግስቱ ደሳለኝ

Report - አይቴል ሞባይል ለስድስተኛ ጌዜ የትምህርት መርጃ መሳርያዎችን በደብረ ማርቆስ ከተማ ድጋፍ አደረገ



አይቴል ሞባይል ለስድስተኛ ጌዜ የትምህርት መርጃ መሳርያዎችን በደብረ ማርቆስ ከተማ ድጋፍ አደረገ!!!!



አይቴል ሞባይል በትላንትናው ለት ማለትም ጥቅምት 28 2010 ዓ.ም በደብረ ማርቆስ ከተማ በአዲስ ሕይወት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ291 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ መሳርያዎችን ድጋፍ አድርጎአል።



አይቴል ሞባይል ይህን ፕሮግራም ሲያዘጋጅ በያዝበዉ አመት ብቻ ለስድስተኛ ጌዜ ሲሆን ይህ ሰናይ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ስንገልፅ በደስታ ነዉ፡፡ አይቴል ሞባይል በተመሳሳይ ሁኔታ በባሕር ዳር፣ ሐዋሳ፣ ጎንደር፣ ኮምቦልቻ፣ መቀሌ እና አዲስ አበባ (ሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር) በሚገኙ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የትምህርት መርጃ መሳርያዎችን ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ነዉ፡፡




በዚህ ተግባሩ አይቴል ሞባይል ሁሌም የማህበረሰቡ አንድ አካል መሆኑን እያሳየ ይገኛል። ከዚህ በፊት አይቴል ሞባይል ኢትዮጵያ ጥቅምት 14 2010 ዓ.ም የሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበርን በመጎብኘት የተለያዩ ስጦታዎችን ቦታው ድረስ በመሄድ  የትምህርት መሳርያ መርጃ ቁሳቁስ ለ305 ተማሪዎችና መምህራን ድጋፍ ያደረገ ሲሆን አይቴል ሞባይል በያዝነዉ ወር 10ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ደግሞ በአማራ ክልል በሚገኙት ከተሞች በጎንደር፣ ባህር ዳር እና ኮምቦልቻ ከተሞች ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ስራዎችን መስራቱ የሚታወስ ነዉ።



አይቴል ሞባይል ኢትዮጵያ በየሳምንቱ የሚደረጉ የተለያዩ አውሮፓ ሊጎችን ትላልቅ ጨዋታዎች እያስገመተች ለትክክለኛ ገማቾች ሽልማት ታበረክታለች።



አይቴል ሞባይል ኢትዮጵያ በተለያዩ የሃገሪቷ ክፍሎች ለችግረኛ ተማሪዎ የደብተር ፣ መፅሃፍትና መማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጋለች ፤ ወደፊትም ታደርጋለች።



እርስዎም የአይቴል ቤተሰብ ይሁኑና ይሸለሙ!




እርስዎም በአይቴል አዳዲስ ሞዴል የሞባይል ምርቶች ህይወትዎን ፣ አኗኗርዎን እና ስራዎን ቀለል እያደረጉ የአይቴል ቤተሰቦችን /Itel Family/ በተለያዩ ማህበራዊ ገፆቻችን በኩል በመቀላቀል አባል በመሆን ከሽልማቶቻችን ፤ ከበጎ አድራጎታችን ገፀ በረከቶች ተቋዳሽ ይሆኑ ዘንድ እየጋበዝን።



 ከታች የሚገኘውን የitel mobile ገፃችንን ፌስቡክ ገፃችንን Like አድርገው በመቀላቀል በየሳምንቱ የሚደረጉ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ግምት በማስቀመጥ ከሽልማቶቻችን ከስጦታዎቻችን ተካፋይ መሆን ይችላሉ..
👉 www.facebook.com/itelmobile

Tuesday, November 7, 2017

ማክሰኞ ምሽት ላይ የወጡ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች






MONACO & BARCA HAD MBAPPE
AGREEMENT


ባርሴሎና እና ሞናኮዎች የ18 አመቱ ታዳጊ ባለተሰጥዎ ተጭዋች ኬይላን ምባፔ በረብጣ የዝውውር ሂሳብ የፈረንሳዩን ክለብ ፒ.ኤስ.ጂን ከመቀላቀሉ በፊት ከባርሴሎና ጋር ሙሉ ለሙሉ ተስማምቶ ጨርሶ ነበር ያለን L'Equipe ነው።


እንደዘገባው ከሆነ ስምምነቱ ኬይላን ምባፔን ወደ ካታሎኑ ክለብ እንዲያመራ እና በተቃራኒው አርዳ ቱራን ወደ ሞናኮ እንዲዛወር በወረቀት ደረጃ ያለቀ ቢሆንም ተጭዋቹ ግን የስምምነቱን ፊርማ ማኖር አልቻለም።


ምባፔ በኃላ ላይ ሳይጠበቅ ለPSGዎች በአንድ አመት የውሰት ውል እና በቀጣዩ ክረምት በ€180 million የቋሚ ዝውውር የፓሪሱን ክለብ ለመቀላቀል መስማማቱ ይታወሳል።





MENDES WANTS €100M BARCA DEAL
FOR JAMES


የህምስሮድሪጌዝ ወኪል የሆነው ሜንዴዝ ደንበኛው በባየር ሙኒክ የቋሚ ውሉን እንዲፈርም ካደረገ በኃላ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ደግሞ በ€100 million, ሂሳብ ባርሴሎና እንዲዛወር ለማድረግ አቅዷል ያለው የስፔኑ ጋዜጣ Don Balon ነው።


ባየር ሙኒኮች ሮድሪጌዝን በሁለት አመት የውሰት ኮንትራት ያስፈረሙት ባለፈው ክረምት ሲሆን በስምምነታቸው መሰረት የሚፈልጉት ከሆነ የ€60m ሂሳብ ለሪያል ማድሪድ በመክፈል በቀጣዩ ክረምት ላይ በቋሚ ዝውውር የሚያስፈርሙበትን አማራጮች ተስማምተዋል።


ያም ሆኖ ሮድሪጌዝ ግን ባየር ሙኒኮች ካርሎ አንቼሎቲን በማሰናበታቸው ደስተኛ ያልሆነ ሲሆን ከሱ በተጨማሪም ቲያጎ አልካንትራ እና አርትሮ ቪዳልም በአሊያንዝ አሬናው ክለብ እስካሁን መረጋጋት ተስኖአቸዋል ተብሏል።


ስለሆነም ወኪሉ ሜንዴዝ ደንበኛው ወደ ባርሴሎና እንዲዛወር የሚፈልግ ሲሆን ተጫቹ ወደ ካምፕ ኑ የመሄድ ፍላጎት አለመያዙና ወደ ማድሪድ መመለስ መፈለጉ ለወኪሉ አስቸጋሪ ያደርግበታል ተብሏል።



NAVAS TO REPLACE CECH AT ARSENAL?


አርሰናሎች የሪያል ማድሪዱን ግብ ጠባቂ ኬይለር ናቫስ የፒተር ቼክ የረጅም ግዜ ተተኪ በመሆን ወደ ኤምሬትስ  እንዲዛቀር ፍላጎት እንዳላቸው የስፔኑ እትም Diario Gol ዘገበ።


የናቫስ የሪያል ማድሪድ ቆይታ ባሁን ሰአት እርግጠኛ ያልሆነ ሲሆን ኮስታሪካዊው ኢንተርናሽናል ክለቡ በተደጋጋሚ ግዜ የማን.ዩናይትዱን ዴቪድ ደ ሂያ ለማዛቀር ተንቀሳቅሷል በሚሉ ዜናዎች ደስተኛ አልሆነም።


ሊቨርፑሎች ከወዲሁ ናቫስን የማዛወር ፍላጎት እንዳላቸው ለስፔኑ ክለብ ያሳወቁ ቢሆንም አሁን ደግሞ የአርሰናሉ አለቃ አርሰን ዌንገር ተጫቹን የቼክ ቁ1 ምትክ ለማድረግ ፈልገውታል።




ARSENAL EYE £10M DEAL FOR FORMER PLAYER


አርሰናሎች ኦጉዝሃን ኦዝያካፕን በድጋሚ መልሰው በ£10 million በማስፈረም ወደ ክለቡ ካመጡት በኃላ የሜሱት ኦዚልን ቦታ እንዲሸፍንላቸው ይፈልጋሉ ሲል የቱርኩ ድህረ ገፅ Turkish-Football ዘገበ።


ኦዝያካፕ አርሰናልን በመልቀቅ የቱርኩን ቤሺክታሽ ክለብ የተቀላቀለው በ2012 ላይ ሲሆን ወደእዛ ካመራ በኃላ ብቃቱን ተጠቅሞ ጥሩ እንቅስቃሴ በቱርኩ ሊግ እያደርገ ይገኛል።


አማካዩ በዚህ የውድድር አመቱ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊጉ ውድድር ላይ ባሳየው ድንቅ ብቃት ሳቢያ ፈላጊ ክለቦችን ያገኘ ሲሆን አርሰን ዌንገር በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ለ25 አመቱ ተጭዋች ጥያቄ ለማቅረብ ተሰናድተዋል። ሜሱት ኦዚል አዲስ ኮንትራት አልፈርምም በማለቱ በክረምቱ ክለቡን እንደሚለቅ በመስጋታቸው ሊተኩት ይፈልጋሉ።


MOURINHO WANTS VARANE FOR DE GEA


ጆዜ ሞሪንዎ ራፋኤል ቫራንን በዴቪድ ደ ሂያ የሪያል ማድሪድ ዝውውር ስምምነት አካል በማድረግ ወደ ኦልትራፎርድ ሊያመጡት ይፈልጋሉ ሲል የዘገበው Don Balon ነው።


የማንቸስተር ዩናይትዱ ግብ ጠባቂ የሪያል ማድሪዶች የክረምቱ ቀዳሚ ቁ1 የዝውውር ኢላማቸው ያደረጉት ሲሆን ጆዜ ሞሪንዎ በበኩላቸው ስፔናዊው ወደ ላ ሊጋው ይመለሳል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል።


ሆኖም በምላሹ ፖርቹጋላዊው ከማስሪድ የዝውውር አካል በማስረግ ተጭዋች ማግኘት የሚፈልጉ ሲሆን ፈረንሳዊውን ኢንተርናሽናል ተከላካይ የዝውውሩ አካል እንዲሆንላቸው የመረጡት ቀዳሚው ተጫዋች ሆኑአል።





FENERBAHCE OFFER SHAW UTD
ESCAPE


የቱርኩ ክለብ ፌነርባቼ የማንቸስተር ዩናይትዱ ግራ ተመላላሽ ተከላካይ ሉክ ሾው ካለበት ቅዥት ሊያነቃው የሚችል የዝውውር ጥያቄ ሊያቀርቡለት ነው ያለው የFanatik እትም Football365 ዋቢ በማድረግ ነው።


የ22 አመቱ ተከላካይ በጆዜ ሞሪንዎ ከጉዳት ከተመለሰ ሁለት ድፍን ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም የመሰለፍ እድል እየተሰጠው ግን አይደለም። እንደውም በ2017-18 አመት ላይ ቋሚ ተሰላፊ የሆነበት ብቸኛው ጨዋታው በካራቦን ካፕ ላይ የተሰለፈበት ነው።


LUIZ FROZEN OUT AFTER QUESTIONING CONTE


ዴቪድ ሉዊዝ ከእሁዱ የማንቸስተር ዩናይትድ ጨዋታ ውጪ እንዲሆን የተደረገው በቡድኑ ታክቲክ ዙሪያ ከአንቶኒዮ ኮንቴ ጋር መስማማት ስላልቻለ ነው ብሏል The Times ጋዜጣ።


ብራዚላዊው ተከላካይ ሰማያዊዎቹ ማን.ዩናይትድን ከመግጠማቸው በፊት በስምንት የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። ሆኖም ሳይጠበቅ በእሁዱ ጨዋታ ላይ ከስኳዱ ውጪ እንዲሆን ተደርጎአል።


እናም ሪፖርቱ እንደዘገበው ከሆነ ተከላካዩ ከቡድኑ ውጪ የተደረገው ከጨዋታው በፊት በተፈጠረ የታክቲክ አለመግባባት ሳቢያ ነው።





CHELSEA CONSIDER DIAKHABY MOVE



ቼልሲዎች የሊዮኑን ተከላካይ ሙክታር ዲያባይ ለማዛወር እንቅስቃሴ ሊያደርጉ ተሰናድተዋል ያለው ደግሞ Daily Mail ነው።


የፈረንሳይ ከ21 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አባል የሆነው ታዳጊ ተከላካይ በሊግ ዋኑ ክለብ በዚህ የውድድር አመት ላይ በተሰለፈባቸው ጭ8ዋታዎች በሙሉ ድንቅ እንቅስቃሴውን እያደረገ ሲሆን ማንቸስተር ሲቲ እና ጁቬንቱሶች ሳይቀሩ ተጫቹን ለማዛወር ከወዲሁ መልማዮቻቸው ወደ ፈረንሳይ በመላክ እየገመገሙት ይገኛሉ።


ሆኖም አንቶኒዮ ኮንቴ ክለባቸው የዝውውር ፉክክሩን በማሸነፍ ተጫቹን ከሁለቱ ክለቦች በመቅደም እንደሚያስፈርሙት ተማምነዋል ሲል ዘገባው አትቷል።

(አዘጋጅ እና ፀሐፊ፦ መንግስቱ ደሳለኝ)

Monday, November 6, 2017

ሰኞ ምሽት ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች




ARSENAL & CITY WANT £5M AJAX MIDFIELDER


የእንግሊዞቹ ክለቦች የሆኑት አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ የኒዉዘርላንዱ ክለብ የሆነዉ የአያክስ አምስተርዳሙን ተጫዋች ፍሬንኪ ዲጆንግን በ€5 million ለማስፈረም ፉክክር ዉስጥ ገብተዋል።


ዘ ሰን እንዳለዉ ከሆነ የ20 አመቱን ወጣቱን ተጫዋች አምና በኢሮፖ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ ክለቡ አያክስ ከ ማንችስተር ዩናይትድ ሲጫወቱ   ሌላኛዉ የፕሪሜር ሊግ ክለብ የሆነዉ ቼልሲ በልጁ ብቃት በመሳባቸዉ ባለፈዉ ክረምት ሊያስፈርሙት ቢሞክሩም ሳይሳካለት ቀርቶል።


አማካኙ በሁለቱ የፕሪሜር ሊግ ክለቦች አርሰናል እና ማን ሲቲ  መፈለጉ ተከትሎ አንዳቸዉ ልጁ ወደ እንግሊዝ ማስኮብለላቸዉ አይቀርም ተብሎል።


LIVERPOOL AND INTER WANT DAVID SILVA




ሊቨርፑል እና ኢንተር ሚላን የማንችስተር ሲቲዉን የጨዋታ አቀጣጣይ ዳቪድ ሲሊቫ ለማስፈረም ፍላጎት አሳይተዋል።


ሲሊቫ በማንችስተር ሲቲ ጥሩን ጊዜ እያሳለፈ ቢገኝም ተጫዋቹ በክለቡ ጥሩ ወራዊ ደሞዝ አያገኝም በዚህም ምክንያት ሊቨርፑል እና ኢንተር ተጫዋቹን ጥሩ ሳምንታዊ ደሞዝ የሚከፍሉት ከሆነ ተጫዋቹ ክለቡን ይለቃል ተብሎ ይታሰባል።


የ31 አመቱ ጎልማሳ ዳቪድ ሲሊቫ በማን ሲቲ ያለዉ ኩንትራት በፈረንጆች 2019 ይጠናቀቃል።


ነገር ግን ሲሊቫ በፔፕ ጋር ዲወላ መወደዱ ክለቡ ለተጫዋቹ ጥሩ ደሞዝ በማቅረብ በክለቡ ሊያቆዩት እንደሚችሉ ተነግሮል።     (daily mail)


CITY TO RIVAL MAN UTD FOR ESPANYOL LEFT-BACK




ሁለቱ ማንችስተር ሲቲ እና ማንችስተር ዩናይትድ የስፓኞሉን የግራ መስመር ተመላላሹን አሮን ማርቲን ለመስፈረም ፉክክር ዉስጥ ሊያደርጉ ነዉ።


ፔፕ ጋርዴዉላ በክረምቱ የዝዉዉር መስኮት ከሪያል ቤትስ ያስፈረሙት ቤንጃሜን ሜንዴ በአሁኑ ሰአት በጉዳት ምክንያት ክለቡን ማን ሲቲ እያገለገለ አይገኝም። ሁኖም የሜንዴ ጉዳት ለእረጅም ጊዜ ከሜዳ የሚያርቀዉ መሆኑን ተከትሎ የቦታዉ ተተኪ ለማድረግ ሲል ሲቲ ተጫዋቹን ለማስፈረም ከፍተኛ የዝውውር ሂሳብ ያቀርባል ተብሎል።


ሁኖም ሁለቱ የማንችስተር ከተሞች የ22 አመቱን ወጣት ለማስፈረም የጥር ወር የዝውውር መስኮት እየተጠባበቁ ነዉ ተብሏል ሲል sky sport ዘግቧል።


BARCA WATCH CHELSEA & MAN UTD STARS




የባርሴሎና ቴክኒካል ሴክሪታር የሆኑት ሮበርት ፈርናንዴዝ እና ዩርባኖ ኦርቴጋ ትናንት በስታምፎርድ ብሪጅ ቼልሲ ማንችስተር ዩናይትድን 1፣0 በሸነፈበት ጨዋታ ላይ የቼልሲ እና የማን ዩናይትድ ተጫዋቾችን ተመልክቶቾዋል።


ከተጫዋቾች መካከል በቼልሲ በኩል በጨዋታዉ አመቻችቶ ያቀበለዉ ሴዛር አዝብሊኪታ እና በጨዋታዉ የማሸነፊዋን ጎል ያስቆጠረዉ አልቫሮ ሞራታ ሲሆኑ፤በማንችስተር ዩናይትድ በኩል ተቀይረዉ ወደ ሜዳ የገቡትን አንድሬ ሄሬራን እና አንቶን ማሪሲያል ናቸዉ።


ሁኖም አራቶቹ ተጫዋቾች በባርሴሎና አለቆች ተወደዋል በዚህም ባርሴሎና የማስፈረም ስራ ሊሰራ ይችላል ተብሎል።     (bbc)


MAN UTD WANT DONNARUMMA TO
REPLACE DE GEA




ጆዜ ሞሪንዎ የዴቪድ ደ ሂያ ምትክ በማድረግ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ለማዛወር ሲሉ ከኤሲ ሚላኑ ግብ ጠባቂ ጂያንሉጂ ዶናሩማ ጋር በየግዜው ንግግር ላይ መሆናቸውን የስፔኑ ህትመት Don Balon ዘገበ።


ዴቪድ ደ ሂያ በተደጋጋሚ ግዜ ኦልትራፎርድን በመልቀቅ ወደ ትውልድ ሃገሩ ክለብ ወደሆነው ሪያል ማድሪድ ከሰባት አመታት የዩናይትድ ቆይታው በኃላ በክረምቱ ቡድኑን መልቀቅ ይፈልጋል። በቅርቡ ደግሞ የፈረንሳዩ ክለብ ፒ.ኤስ.ጂዎች ደ ሂያን ለማዛወር ፉክክሩን ከማድሪድ ቀድመውት እየመሩት መሆኑ ሲዘገብ ስፔናዊው ግብ ጠባቂ የ€70 million ሂሳብ ቀርቦለታል ተብሏል።


ስለሆነም ጆዜ ሞሪንዎ ደ ሂያን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ እንደሚያጡት ስለተሰማቸው ክለቡ የኤሲ ሚላኑን ዶናሩማ በማዛወር የስፔናዊው ቁ1 ተተኪ እንዲሆንላቸው ይፈልጋሉ።


OTHER SHORT STORIES



ዌስትሃም ዩናይትዶች ክለባቸው በፕሪሚየር ሊጉ ደካማ ውጤት ማስመዝገቡን ተከትሎ አሰልጣኙን ስላቨን ብሊች አባረዋል። በምትኩ የቀድሞው የምልን.ዩናይትድ እና ኤቨርተን አሰልጣኝ የነበሩት ዴቪድ ሞዬስ ክለቡን እንደሚይዙት ይጠበቃል።  
(Source: @JimWhite)



ፋቤጋስ ማን.ዩናይትድን ካሸነፉ በኃላ: "በዛሬው ጨዋታ ኳስ በብዛት ተቆጣጥረናል። የጎል ማግባት እድሎችን ፈጥረናል እንዲሁም ጥሩ ተከላክለናል። እንደ ትልቅ ቡድን ነው የተጫወትነው። በዛሬው ፐርፎርማንሳችን ልንኮራ ይገባል። ሊያልቅ አካባቢ ትንሽ ከብዶን ነበር። ምናልባት አብዝተን  ተከላክለናል። ሆኖም በኳስ ቁጥጥር እንበልጥ ነበር ይሄ ደሞ ያጣነውና የጎደለን ነገር ነበር። መከላከል ምርጥ ቢሆንም ጥሩ እግር ኳስ መጫወትም አለብን"     [ለSky sports]



ጆዜ ሞሪንዎ ከቼልሲው ሽንፈት በኃላ: “ትልልቅ የሆኑ ከባባድ ጭ9ዋታዎችን አድርገን መጥተናል። ቶተንሃም፣ ሊቨርፑል እና ቼልሲ ያደረግናቸው ጨዋታዎች ያለ ወሳኝ ልጆቻችን ነው።“



ጆዜ ሞሪንዎ አንቶኒዮ ኮንቴን ስላለመጨበጣቸው: "ጨዋታው እንዳለቀ ወዲያውኑ ከሜዳው ተሰወረ። ሆኖም የምክትሉን እጅ ጨብጫለሁ። በመሰረቱ እሱንም ጨበጥኩ ምክትሉ አንድ ነው ለውጥ የለውም"


(አዘጋጅና አርታኢ መንግስቱ ደሳለኝ)
ፀሐፊ - ሙሴ አማረ

Featured Post/ቀጣይ ልጥፍ

የዝውውር ዜናዎች

  ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር...