Tuesday, November 27, 2018

ማክሰኞ ምሽት የወጡ አዳዲስ የዝውውር ወሬዎች



ሜሱት ኦዚል በአርሰናል የመቆየቱ ነገር አጠራጣሪ እየሆነ መጥቷል። ተጭዋቹ ቡድኑ ከሜዳ ውጪ በሚያደርገው ጨዋታዎች ላይ ቤንች ላይ መቀመጡ አላስደሰተውም።

ኡናይ ኤምሬ በበኩላቸው ቡድኑ ከኢንተርናሽናል እረፍት በፊት ከክሪስታል ፓላስ ጋር ባደረገው ጨዋታ ላይ ነጥብ ሲጥል ለቡድኑ ባደረገው አስተዋፅዎ ደስተኛ አይደሉም። ከዛም በበርንማውዙ ጨዋታ ላይ ተጠባባቂ አድርገውታል። ተጭዋቹ ኢምሬትስን የሚለቅ ከሆነ ማን.ዩናይትዶች አማካዩን የማዛወር የተሻ እድል አላቸው።  (ምንጭ፦ johncrossmirror)

.

ማንቸስተር ሲቲዎች የፖርቹጋሉን የ21 አመት ብሄራዊ ቡድን ተጭዋች ስቴፈን ኢውስታኪዮ ለማዛወር እየተከታተሉት ነው። ለቼቫስ የሚጫወተው ባለተሰጥዎ በባርሴሎና፣ ሪያል ቤቲስ እና ስፖርቲንግም ጭምር ይፈለጋል። ኮንትራቱ ላይ የ£13.3m ውል ማፍረሻ አለው።     (ምንጭ፦ Daily Mail)

.

ጋላታሳራዮች የሊቨርፑሎቹን አጥቂ ዶሚኒክ ሶላንኬ እና ዲቮክ ኦርጂን የማዛወር እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
(ምንጭ፦ Daily Mirror)

.

ኦስማን ዴምቤሌይ ለባርሴሎና ክለብ አመራሮች የጥር የዝውውር መስኮት ከመከፈቱ በፊት ከክለቡ እንዲለቁት መወትወቱን ቀጥሎበታል። ስሙ ከአርሰናል ዝውውር ጋር መያያዙን ተከትሎ በጥር ክለቡን መልቀቅ ይፈልጋል።   (ምንጭ፦ Daily Mail)

.

ኤሲ ሚላኖች የቼልሲውን እና የእንግሊዙን ኢንተርናሽናል መሃል ተከላካይ ጋሪ ካሂል እንዲያስፈርሙት ቀርቦላቸው ሳይቀበሉት ቀርተዋል።
(ምንጭ፦ Calciomercato)

.

ማንቸስተር ዩናይትዶች የቦሩሲያ ዶርትመንዱን አማካይ አክስል ዊትሰል መከታተላቸውን አሁንም ቀጥለውበታል። ምንም እንኳን ክለቡ በክረምቱ ብራዚላዊውን አማካይ ፍሬድ ቢያዛውርም ሞሪንዎ አሁንም የአማካይ ክፍሉ ችግር እንዳልተቀረፈ ተረድተውታል።   (ምንጭ፦ Daily Star)

.

የቀድሞው የአርሰናል አለቃ አርሰን ዌንገር ወደ አሰልጣኝነት ስራቸው መመለስ የሚፈልጉ ሲሆን ኒኮ ኮቫችን ለማሰናበት የተዘጋጁት ባየር ሙኒኮች ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ቀጣዩ የቡድናቸው አለቃ አድርገው ሊሾሙአቸው እያጤኑበት ነው ተብሏል።
(ምንጭ፦ Telegraph)

.

የቀድሞው እንግሊዛዊ ኢንተርናሽናል አሽሊ ኮል በአሜሪካው የ MLS ሊግ ክለብ LA Galaxy ተለቋል።   (ምንጭ፦ LAGalaxy)

.

ጎንዛሎ ሂጉዌይን ቼልሲን የመቀላቀል ፍላጎት አለው። አርጀንቲናዊው አጥቂ በናፖሊ ከማውሪዚዮ ሳሪ ጋር አንድ ላይ የሰራ ሲሆን በድጋሚ የለንደኑን  ክለብ ተቀላቅሎ ከአሰልጣኙ ጋር በድጋሚ መስራት ይፈልጋል።  (ምንጭ፦ Corriere dello Sport)

.

ኔይማር እና ክለቡ PSGዎች ብራዚላዊው ኮከብ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ለዝውውሩ የ€200 ሚሊዮን ዩሮ ሂሳብ የሚቀርብላቸው ከሆነ ወደ ላ ሊጋው እንዲዛወር ፍቃዳቸውን እንደሚሰጡት ከወዲሁ ቅድመ ስምምነት ቃል ገብተውለታል። (ምንጭ፦ Betevé)

.

ሪያል ማድሪዶች የጁቬንቱሱን ፓብሎ ዳይባላ ለማዛወር የነበራቸውን ምኞች እንደማይሳካ ተስፋ አስቆርጧቸዋል። ከእርሱ ይልቅ በክረምቱ ብራዚላዊውን ኮከብ ኔይማር ወደ በርናባው ለማዛወር ሙከራ ለማድረግ ወስነዋል።
(ምንጭ፦ Calciomercato)

.

የቼልሲው የፊት መስመር ተሰላፊ ኤዲን ሃዛርድ ወደ ፈረንሳዩ ክለብ PSG ይዛወራል መባሉን አስተባበለ። ሆኖም የ27 አመቱ ቤልጂየማዊ ኮከብ በክረምቱ ክለቡን ሊለቅ እንደሚችል ፍንጭ ሰትቷል።
(ምንጭ፦ Canal+)

.

ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃሞች የሳምፕዶሪያውን የ22 አመት ተከላካይ ጃኪም አንደርሰን ሁኔታ በቅርበት በመከታተል ላይ ናቸው።  (ምንጭ፦ Daily Mirror)

.

Official: ማይክ ዲን የፊታችን እሁድ የሚደረገውን ተጠባቂ የለንደ ደርቢ አርሰናል እና ቶተንሃም ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በመሃል ዳኝነት እንደሚመሩት FAው አሳውቋል።

.

አርሰንልን ሲጫውቱ ክለቡ የውጤት ድርቅ ይመታዋል የሚባልላቸው እና ከቀድሞው የአርሰናል አለቃ አርሰን ዌንገር ጋር በተደጋጋሚ ውዝግብ ውስጥ ሲገቡ የታዩት ዳኛ ማይክ ዲን በአንድ ወቅት ከቬንገር ጋር ስለፈጠሩት ዱላ ቀረሽ ግብግብ ተጠይቀው፦

"ከጨዋታው በኃላ ወደኔ ሲመጣ ለዱላ ተጋብዞ በንዴት መንፈስ ነበር። ጣቶቹን ወደኔ እየጠቆመ ደጋግሞ 'አንተ ታማኝ ዳኛ አይደለህም' ሲል ይናገረኝ ነበር። 'ስለዚህ አጭበርባሪ ነህ እያልከኝ ነው?' ስል መለስኩለት። 'አሁንም እደግመዋለው አንተን ላምንህ አልችልም በፍፁም' ሲል በድጋሚ መለሰልኝ"

"ከዛም 'እንደዚህ ጨዋታዎች ላይ ስትበድለን ዛሬ የመጀመሪያህ አይደለም፤ ሁልግዜም ትበድለናለህ፤ አንተኮ ፕሮፌሽናል ዳኛ መሆን ይጠበቅብሃል። አንተ ክብረ ቢስ የሆንክ ዳኛ ነህ' ሲል ወረደብኝ። በመሃል የዌስብሮም የሜዳ ላይ ኦፊሰሮች በነሃላችን ገብተው ካለሁበት የስቴዲየሙ ክፍል ይዘውት ወጡ" -  ሲል ምን ያህል ከፈረንሳዊው አለቃ ጋር ያን ወቅት ዱላ ቀረሽ ለሆነ ፀብ ተቃርበው እንደነበር ተናግሯል።
(ምንጭ፦ TheSun)

.

በርካታ የአውሮፓ ክለቦች ሊቨርፑል፣ አርሰናል እና ማንቸስተር ሲቲን ጨምሮ የሊዮኑን አማካይ ታንጋይ ንዶምቤሌይን ሁኔታ በቅርበት ሆነው በመከታተል ላይ ናቸው። ተጭዋቹ የ £55 million ዋጋ ያወጣል ተብሏል።  (ምንጭ፦ Anfieldhq)

.

ሊቨርፑሎች ክሪስቲያን ፑሊሲችን ከቦሩሲያ ዶርትመንድ በ£70 million ፓውንድ ሂሳብ ሊያዛውሩት ይችላሉ። ሆኖም። አሜሪካዊውን አማካይ ማስፈረም የሚችሉት በ2019 የዝውውር መስኮት ላይ ብቻ ከሆነ ነው።   (ምንጭ፦ LiverpoolEco)

.

ማንቸስተር ሲቲዎች በበኩላቸው አሌክሳንደር ዚቺንኮን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለመሸጥ የነበራቸውን እቅድ ሙሉ ለሙሉ ሰርዘውታል። ይሄ የሆነው ቤንጃሚን ሜንዲ ጉዳት ስላጋጠመው ነው።
(ምንጭ፦ TelegraphDucker)

.

ሪያል ማድሪዶች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ የማን.ሲቲውን ተፈላጊ ባለተሰጥዎ አማካይ ብራሂም ዲያዝን ለማዛወር ሙከራ ያደርጋሉ። ለዝውውሩ ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥማቸው ይረዱታል። በጥር የማይሳካላቸው ከሆነ ግን በክረምቱ ኮንትራቱ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ያዛውሩታል። ተጭዋቹ በክረምቱ ወደ በርናባው ለማምራት ቅድመ ስምምነት ላይ ደርሷል ተብሏል።    (ምንጭ፦ ellarguero)

.

ሜሱት ኦዚል ሳይጠበቅ አርሰናልን ሊለቅ ይችላል የሚሉ ወሬዎች መሰማት ጀምረዋል። ኤምሬትስን ከለቀቀ ማን.ዩናይትድ አማካዩን የማዛወር የተሻለ እድል አላቸው ተብሏል።     (ምንጭ፦ Express)

.

ሞዬስ : "በኔ ዘመን ቶኒ ክሩስ ወደ ማን.ዩናይትድ ለመምጣት ሙሉ ለሙሉ ተስማምቶ ነበር። ከነ ባለቤቱ አግኝቼው በግል ተነጋግረን ነበር። ባየር ሙኒክ እያለ ወደ ዩናይትድ ለመምጣት በሁሉም ነገር ላይ ከስምምነት ደርሰን ነበር።"   (ምንጭ፦ Bild)

.

ያፕ ሄንኪንሰን በባየር ሙኒክ እየተከሰተ ስላለው የቡድኑ ቀውስ ዝምታቸውን ሰብልረዋል:

"በቡድኑ ውስጥ መልአክ የሆኑ እና ሰይጣን የሆኑ ሁለት አይነት ሰዎች አሉ። በጉዳት ሳቢያ የማይጫወቱ ደግሞ የቡድኑ ቁልፍ ተችዋቾችም አሉ። በክለቡ አናት ላይ የተከመረ ትልቅ የችግር ተራራ ይገኛል።" - ሲል አስገራሚ ምላሽ ሙኒክ ላይ ሰጥተዋል።    (ምንጭ፦ Westdeutsche Zeitung)

Monday, November 26, 2018

ሰኞ ምሽት የወጡ ተጨማሪ አዳዲስ የዝውውር ዜናዎች



ማንቸስተር ዩናይትዶች የናፖሊውን መሃል ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለማዛወር የተሻለ እድል አላቸው።   (ምንጭ፦ M.E.N)

.

ኦስማኔ ዴምቤሌይ በጥር የዝውውር መኮት ላይ ክለቡ ባርሴሎና እንዲለቀው ጥያቄ አቅርቧል። የእርሱ ክለቡን መልቀቅ የቀድሞው ብራዚላዊ ኮከብ ኔይማር ወደ ክለቡ እንዲመለስ በር የሚከፍት ነው ተሏል። ዴምቤሌይ በአርሰናል እንደሚፈለግ ይታወሳል።   (ምንጭ፦ Goal)

.

PSGዎች የማንቸስተር ዩናይትዱን ስፔናዊ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደ ሂያን ለማዛወር በሚያደርጉት ጥረት ላይ ከጁቬንቱሶች ከፍተኛ ፉክክር ይጠብቃቸዋል።  (ምንጭ፦ Sun Sport)

.

የማንቸስተር ዩናይትዶች አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ ለዩሃን ማታ የሦስት አመት ኮንትራት ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። የ30 አመቱ ስፔናዊ በሲዝኑ መጠናቀቂያ ላይ ከኮንትራቱ ነፃ ይሆናል።
(ምንጭ፦ Mail)

.

ጆሴ ሞሪንዎ የዌስትሃሙ አጥቂ አርናቶቪችን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በማስፈረም ክለቡን ወደ ቶፕ 4 ውስጥ አስገብቶ ሲዝኑን እንዲያጠናቅቁ እንዲረዳቸው ይፈልጋሉ። ለተጭዋቹ ዝውውር የ50 ሚ.ፓ ሂሳብ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።
(ምንጭ፦ Sunday Mirror)

.

ቼልሲዎች ኤዲን ሃዛርድን በሪያል ማድሪድ እንደሚነጠቁ ማመን ጀምረዋል። የስፔኑ ሃያል ክለብ ቤጂየማዊውን ለማዛወር ከወዲሁ እንቅስቃሴ መጀመራቸው የተነገረ ሲሆን ክለቡ በክረምቱ ሊያዛውር ከሚፈልጋቸው ጋላክቲኮዎች ቀዳሚው ሆኑአል።   (ምንጭ፦ OK Diario)

.

የባየር ሙኒኩ አለቃ ኒኮ ኮቫች ገና በመጀመሪያው ዙር የቡንደስሊጋ የውድድር አጋማሽ ላይ ከክለቡ ለመሰናበት ተቃርበዋል። አሰልጣኙ ቡድኑን በሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ማሸነፍ ከተሳናቸው በኃላ የክለቡ ባለስልጣናት ትእግስታቸው አልቋል።
(ምንጭ፦ Sun Sport)

.

አርሰናሎች የማንቸስተር ዩናይትዱን ፔሬራ ለማዛወር በሚፈረገው ፉክክር ላይ ተቀላቀሉ። ፔሬራ በፕሪሚየር ሊጉ መቆየት የሚፈልግ ሲሆን በሲዝኑ መጠናቀቂያ ላይ አዲስ ኮንትራት እስካልፈረመ ድረስ ከኮንትራት ነፃ በመሆኑ ክለቡን በነፃ መልቀቅ ይችላል። ሆኖም መድፈኞቹ ተጭዋቹን ከማዛወር ከቼልሲ ፉክክር ይጠብቃቸዋል።  (ምንጭ፦ Mirror)

.

ሴስክ ፋቤጋዝ ከቤሺክታሾች የእናዛውርህ ጥያቄ ቀርቦለታል። ያም ሆኖ ኤሲ ሚላኖች የቼልሲውን አማካይ ለማዛወር የተሻለ እድል ይዘዋል ተብሏል።
(ምንጭ፦ Sunday Express)

.

ፒር ኤምሬክ ኦበምያንግ በሁሉም ውድድሮች በዚህ ሲዝን ላይ 10 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል። ይሄ ሪከርድ የአርሰናሉ ጋቦናዊ አጥቂ አምና እስከ አፕሪል ወር ድረስ ያላሳካው ነው። (ምንጭ፦ swaka)

.

አሌክሳንደር ላካዜቲ በትላንቱ የመድፈኞች ድል ባደረጉበት ጨዋታ ላይ ያልተሰለፈው መጠነኛ የህመም ስጋት ስላለበት ነው ተብሏል። ሆኖም የአጥቂው ጉዳት ቀላል በመሆኑ በዩሮፓ ሊጉ ጨዋታ ላይ ይመለሳል ተብሏል።  (ምንጭ፦ Mirror)

.

ሮብ ስለ ኡናይ ኤምሬ እና አርሰን ዌንገር ልዩነት: “
"ትልቁ ልዩነት አሁን ማጥቃት ብቻ ሳይሆን እንዴት መከላከል እንሳለብን ማወቃችን ነው። እንዴት የተቃራኒ ክፍል ቦታ ጥቃት እንፈፅማለን ከዛም ወዲያውኑ ቡድኑ ሲጠቃ ወዲያው ተደራጅተን በሚገባ እንከላከላለን ከዛም በፍትነት በመልሶ ማትቃት የምንሄድበት መንገድ ሁሉ ተቀይሯል። ያ ነው ትልቁ ልዩነት።"

"ቡድኑ በቶፕ አራት ውስጥ ገብቶ ቢያጠናቅቅ እና አንድ ዋንጫ ቢያነሳ ለኔ አመቱ የስኬት ይሆናል ባይ ነኝ።" ሲል አስተያየቱን አጠቃሏል።
Skysports)

.

'በቶፕ 4 ውስጥ ገብተን የቻምፒየንስ ሊግ ቦታን ማስጠበቅ ካለብን ከዚህም በላይ መሻሻል ይኖርብናል' - ያሉት ደግሞ የአርሰናሉ አለቃ ኡናይ ኤምሬ ናቸው።  (ምንጭ፦ ArsenalNews)

.

ፍራንክ ሪበሪ በሴፕተምበር ወር ላይ ቡድኑ ከባየርን ሌቨርኩሰን ጋር ከመጫወቱ ቀደም ብሎ የቤተሰብ ጉዳይ እንዳለበት በማስፈቀድ ከአሊያንዝ አሬና ስቴዲየም ለቆ ሲወጣ ፎቶግራፍ ያነሳው የነበረን ጋዜጠኛ እንደመታው ተነግራል። ሪቤሪ በወቅቱ የፎቶግራፈሩን ትከሻ ጨምድዶ በመያዝም ያነሳውን ፎቶ ወዲያውኑ እንዲያጠፋውም በጩሃትና በዱላ አስገድዶታል።   (ምንጭ፦ Ozzywessi)

.

ፔፕ ጋርዲዮላ የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ ፉክክር ላይ ሲጠየቅ: "የሊጉ ፉክክር ከናዳል፣ ፌደረር እና ጆኮቪች የቴኒስ ፉክክር ጋር ተመሳሳይ ነው። አንዱ ከአንደኛው የተሻለ ሆኖ እንዲመጣ ግፊት ያሳድርበታል። ምክንያቱም ይተዋወቃሉ። ይሄንን ፉክክር በስፖርቱ እንፈልገዋለን፤ ልክ እንደ አትሌቲክሱ ሁሉ። የሲቲ ተጭዋቾች ይሄንን ያውቁታል ምን ያህል ፉክክር እንዳለብን እኔ አልነግራቸውም። ሊቨርፑል ምን ያህል ጠንካራ ቡድን እንደሆነ ራሳቸው ያውቁታል።" - ሲል ስፔናዊው አሰልጣኝ ሊቨርፑል የሊጉ እውነተኛ ተፎካካሪያቸው ክለብ እንደሆነ ጠቁሟል።

.

ማንቸስተር ሲቲዎች የPSGውን አማካይ አድሪያን ራቢዮት ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ባርሴሎናን ተቀላቅለዋል። የ23 አመቱ ተጭዋች በፓሪሱ ክለብ ኮንትራቱን እንደማያድስ መናገሩ የሚታወስ ሲሆን በጁቬንቱስና በቶተንሃምም በትብቅ ይፈለጋል። ኮንትራቱ በጁን 30; 2019 ላይ እንደሚጠናቀቅ ይታወቃል።   (ምንጭ፦ Téléfoot)

.

"እርግጥ ነው በጥር የዝውውር መስኮት ክለቡን አይለቅም።" - ሲሉ የርገን ክሎፕ ፋቢንዎ በሊቨርፑል እንደሚቆይ ተናግረዋል። በቅርብ በወጡ ሪፖርቶች መሰረት ብራዚላዊው ኮከብ በሊቨርፑል መረጋጋት ስለተሳነው ክለቡን ይለቃል ተብሎ ሲወራ እንደነበር ይታወሳል።  (ምንጭ፦ LiverpoolEco)

.

የማንቸተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ክለቡ ስድስት ተጭዋቾችን በጥር የዝውውር መስኮት እንዲሸጥ ድምፅ ሰጥተዋል። በዚህ መሰረት ክለቡን እንዲለቁ ስሞሊንግ (48.8%), አሌክሲስ (37.6%), ቫሌንሺያ (35.3%), ሮሆ (17.4%) እና ዳርሜይን (7.5%) ናቸው።   (ምንጭ፦ M.E.N)

.

Liverpool and Chelsea receive Asensio boost

የሪያል ማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎረንቲኖ ፔቴዝ የሊቨርፑል እና የቼልሲ የዝውውር ኢላማ የሆነውን ማርኮ አሴንሲዮ በሌላ ተጭዋች ለመተካት አስበዋል ሲል Don Balon ዘገበ።

የፊት መስመር ተጭዋቹ የክርስቲያኖ ሮናልዶን ክፍተት ይሸፍናል ተብሎ ተስፋ ቢጣልበትም ለቡድኑ ውጤታማነት ምንም አስተዋፅዎ ማድረግ ተስኖት ታይቷል።

ማድሪዶች ስማቸው በተደጋጋሚ ግዜ ከኤዲን ሃዛርድ ዝውውር ጋር ተያይዞ የተነሳ ሲሆን የአሴንሲዎ አቋም ካልተሻሻለ ተጭዋቹን በመልቀቅ በቤልጂየማዊው ኮከብ ይተኩታል።

.

West Ham to resist Man Utd interest in Arnautovic

ዎስትሃም ዩናይትዶች ማርኮ አርናቶቪችን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በማንቸተር ዩናይትድ ሊነጠቁ ይችላሉ የሚሉ በርካታ ዘገቦች ቢሰሙም ተጭዋቹን ለዋቆየት የቻሉትን ሁሉ ሊያደርጉ ተዘጋጅተዋል ሲል London Evening Standard ዘግቧል።

አጥቂው በዚህ የውድድር አመት ላይ ጥሩ አቋም ላይ የሚገኝ ሲሆን ምንም እንኳን መዶሻዎቹ ከስቶክ ሲቲ ሲያዛውሩት ከከፈሉት የ £23 million ወይም (€26m/$29.5m) ሂሳብ በእጥፍ የሚያተርፊበት ሂሳብ ከዩናይትድ ይቀርብላቸዋል ቢባልም ላለመቀበል ተዘጋጅተዋል።

.

Isco looking for Madrid escape

አማካዩ ያለውን እምቅ ችሎታ አውጥቶ እንዲጠቀም ወደሚያደርገው ክለብ መዛወር ይፈልጋል። የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ኢስኮ ክለቡን ለመልቀቅ አስቧል ሲል Don Balon ዘግባል።

የቡድኑ አሰልጣኝ ሳንቲያጎ ስላሬ በክለቡ ትልቅ ለውጥ ለማድረግ ያቀዱ ሲሆን ኢስኮ ክለቡ ሊሰዋቸው ካሰባቸው ተጭዋቾች መካከል ይገኝበታል። ተጭዋቹ ቡድኑ ካደረጋቸው ያለፉት 5 ጨዋታዎች ውጪ ሆኑአል።

.

Suarez would prefer Arsenal move

የቀድሞው የማንቸስተር ሲቲ ተጭዋች ዴኒስ ሱዋሬዝ ወደ እንግሊዝ መመለስ ይፈልጋል።

እንደ AS ዘገባ ከሆነ ተጭዋቹ ወደ ደቡቡ እንግሊዝ ክለብ አርሰናል ለመዛወር ይፈልጋል።

ስፔናዊው ማን.ሲቲን በመልቀቅ ወደ ካምፕ ኑ ክለብ ከተዛወረ ወዲህ የሚፈልገውን ያህል የመሰለፍ እድል እያገኘ አይደለም።

ቼልሲ እና ቫሌንሺያ ተጭዋቹን የማዛወር ፍላጎት ቢኖራቸውም መድፈኞቹ ግን ከወዲሁ ፉክክሩን እንዳሸነፉት ይታመናል።

Saturday, November 24, 2018

የማን.ዩናይትዱ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደሂያ ወኪል ጆርጅ ሜንዴዝ ጣሊያን ቱሪን ይገኛል



ጁቬንቱሶች ሱፐር ኤጀንቱን ጆርጅ ሜንዴዝ በመቅጠር የማንቸስተር ዩናይትዱን ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደ ሂያን ወደ ቱሪን የማዛወር ተልዕኮ ሰጥተውታል - በዚህ ሳቢያ ጆዜ ሞሪንዎ በጉዳዩ ላይ ክፉኛ ብስጭት ውስጥ ናቸው

እውቁ ፖርቹጋላዊ አደራዳሪ የዴቪድ ደ ሂያ ወኪል ሲሆን ግብ ጠባቂው በኦልትራፎርድ የመጨረሻ አመት ውሉ ላይ ሊገባ ተቃርቧል።

ዩናይትዶች ተጭዋቹን ለተጨማሪ 12 ወራት ውሉን የማራዘም መብቱ በጃቸው ነው። ስለዚህ አዲስ የኮንትራት እድሳቱ ባይፈረምና ቢቀር ተጭዋቹን በ2020 የውድድር አመት ላይ በነፃ የዝውውር ሂሳብ ያለምንም ችግር ወደፈለገበት ክለብ ስፔናዊው ማምራት ይችላል።

እንደ SunSport ዘገባ ከሆነ ዩናይትዶች ኮንትራቱ ሲጠናቀቅ ደ ሂያን የማጣት ትልቅ ስጋት ውስጥ ገብተዋል።

ሞሪንዎ ባለፈው ወር ላይ እንዳሉት ከሆነ የቀድሞው የአትሌቲኮ ማድሪድ ኮከብ ደ ሂያ በክለቡ እንደሚቆይ 'እርግጠኛ ስላለመሆናቸው' ተናግረው ነበር።

እናም ጁቬንቱሶች ስፔናዊውን ወደ ጣሊያን ለማስኮብለል በሚያደርጉት ጥረት ላይ ወኪሉ ጆርጅ ሜንዴዝ ላይ ልዩ ትኩረት አድርገው መስራት ጀምረዋል።

የጣሊያኑ ተነባቢ ጋዜጣ Tuttosport እንዳለው ከሆነ ሜንዴዝ ሁለት ደንበኞቹን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ወደ ቱሪን እንዲያመጣ ተጠይቋል። እነርሱም ዴቪድ ደ ሂያ እና ጀምስ ሮድሪጌዝ ናቸው።

ሮድሪጌዝ በአሁን ሰአት በባየር ሙኒክ በውሰት ተሰጥቶ በመጫወት ላይ ሲሆን ከሲዝኑ መጠናቀቅ በኃላ በሙኒክ ይቆይ አይቆይ የታወቀ ነገር የለም።

የክለቡ የSporting director የሆኑት Fabio Paratici እንዳሉት ከሆነ ክለቡ የዎልቭሱን ሩበን ኔቬስ በጥር የማዛወር እቅድ እንዳለው ተናግረው ነበር። ይሄም ተጭዋች ሌላኛው የሜንዴዝ ደንበኛ ነው።

ማንቸስተር ዩናይትዶች ከሰር አሌክስ ፈርጉሰን ክለቡን መልቀቅ በኃላ ውጤታማነታቸው በፍጥነት እየቀነሱ መምጣታቸው የሚታይ ሲሆን ዴቪድ ደ ሂያ ግን የቡድኑ ወሳኙ ሰው መሆኑን ቀጥሏል።

ተጭዋቹ በ2011 ወደ ክለቡ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ከተዛወረ በኃላ ከሰባት አመታቱ ውስጥ ለአራት ጊዜያቶች ያህል የክለቡ የአመቱ ኮከብ ተጭዋች በሚል ተመርጧል።


Eric Steele ስፖናዊውን ኢንተርናሽናል በእንግሊዝ ለመጀመሪያዎቹ ሁለት አመታት ያህል አሰልጥኖት ነበር። አሁን ክለቡን ስለመልቀቅ ማሰቡ ለሱ የሚያስገርም ዜና እንዳልሆነ ተናግሯል።

ግለሰቡ በግብ ጠባቂዎች ልዩ የUnion podcast, ላይ እንደተናገረው ከሆነ : "አሁን ደ ሂያን እምትጠይቁት ከሆነ በማንቸስተር ዩናይትድ ላይ ሙሉ ትኩረቱ እንደሆነ ይነግራችኊል።"

"እጅግ የተሳኩ አመታት አሉት። ከተጭዋቾቹም ሆነ ከደጋፊዎቹ ጋር ልዩ ቅርርብ አለው። ሆኖም እርሱ አሁን አሸናፊ መሆን ይፈልጋል። አሁን ክለቡን ስለመልቀቅ ሊያስብ ይችላል። የሚፈልጋቸውን ድሎች አሁን በዩናይትድ አገኝ ይሆን ብሎ ራሱን መጠየቁ አይቀርም"

"ሌሎች ተፎካካሪ ክለቦች በደንብ ሲጠናከሩ ተመልክቷል። ፉክክሩ አይሏል።

"እርሱም አሁን እድሜው 28 ነው። የብቃቱ ጫፍ ላይ ነው። ስለ ድል ማሰቡ ትክክለኛው ሰአቱ ነው።

"እኔ በግሌ በክለቡ እንዲቆይ እፈልጋለሁ። ማንቸተር ዩናይትድን ቢያጠናክር ለሊጉም ቢቆይ ብዬ እመኛለሁ"

ዴቪድ ደ ሂያ በማንቸስተር ዩናይትድ ኮንትራታቸው ሊጠናቀድ ከተቃረቡ 10 ተጭዋቾች መሃከል አንዱ ነው። አንቶኒ ማርሻል እና ዩሃን ማታም ይገኙበታል።

Thursday, November 22, 2018

ቼልሲዎች አንቶኒ ማርሻልን በጥር የዝውውር መስኮት በልውውጥ ውል ሊያስፈርሙት አቅደዋል



CHELSEAዎች አንቶኔ ማርሻልን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለማዛወር ወጥነዋል። ማውሪዚዮ ሳሪ የጆዜ ሞሪንዎን ባለተሰጥዎ የፊት መስመር ተጫዋች ለማስፈረም ሲሉ ዊሊያንን ያካተተ የልውውጥ ዝውውር ለማድረግ አስበዋል።

ቀያይ ሰይጣኖቹ የአንቶኔ ማርሻልን ኮንትራት በአንድ አመት ተጨማሪ ውል ለማራዘም አክቲቬት ያደረጉት ሲሆን ፈረንሳዊው የክንፍ መስመር ተጫዋች የቀረበለትን የረጅም አመት ውል ሳይቀበለው መቅረቱ ይታወሳል።

ዩናይትዶች አሁን በጥሩ ብቃት ላይ የሚገኘውን የቡድኑ ባነተሰጥዎ ተጭዋች በክለቡ እንዲቆይላቸው አዲስ በድምሩ የጉርሻ ክፍያዎችን ጨምሮ የ£45 million አምስት አመት ውል ሊያቀርቡለት ተሰናድተዋል።

ሆኖም እንደ Sky Sports ተረዳውት ብሎ እንደዘገበው ከሆነ በቡድኑ እና በተጭዋቹ መሃከል ከስምምነት ላይ ለመድረስ ከጫፍ አልተደረሰም። እናም ቼልሲዎች ለዝውውሩ አማራጭ ተጭዋች ለዩናይትዶች በመስጠት በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ወደ ለንደን ሊያስኮበልሉት አቅደዋል።

ማርሻል በቅርቡ በክለቡ የቀረበለትን ሳምንታዊ የ£160,000 ደሞዝ ሂሳብ ውል ውድቅ አድርጎታል። ሆኖም ክለቡን መልቀቅ እንደማይፈልግና አሁን በማንቸስተር እንደተረጋጋ ገልፆአል።

ምንም እንኳን ከጆዜ ሞሪንዎው ቡድን ባለፈው አመት አብላጫውን ጨዋታዎች ከቄሚ አሰላለፍ ውጪ ቢደረግም አዲስ ውል ስለሚፈርምበት ሁኔታ ከክረምቱ የዝውውውር መስኮት ግዜ ጀምሮ በክለቡና በተጭዋቹ መካከል ንግግር ከጀመሩ ቆይተዋል። ከዛ ጊዜ በኃላ ደግሞ የተጭዋቹ የግል ብቃት ከምንግዜውም በላይ ጨምሮ ታይቷል።

ቼልሲዎች በአሁኑ ወቅት የማንቸስተር ዩናይትዱን ክንፍ ማርሻል በክንፍ ተጭዋቻቸው ዊሊያን መቀያየር እንደሚፈልጉ ጭምጭምታዎች መሰማት ከጀመሩ ቆየት ብለዋል።

ዊሊያን በበኩሉ ከቀድሞው የቼልሲ አለቃው ጆዜ ሞሪንዎ ጋር በድጋሚ የመስራት እድሉን ቢያገኝ ፖርቹጋላዊውን ከመቀላቀል እንደማያቅማማ ተናግሮ ነበር። ሞሪንዎ በበኩላቸው የብራዚላዊው የረጅም ግዜ አድናቂ ናቸው።

ዊሊያን እንዳለው ከሆነ: "ሞሪንዎ እስካሁን አብሬ ከሰራሁአቸው አሰልጣኞች መሃከል ምርጡ ነው። ጥሩ ግንኙነት አለን። ጓደኛሞች ነን።

"አንዳንዴ እናወራለን። መልዕክቶችን በስልክ እንድለዋወጣለን። በWhatsApp በደንብ እናወራለን። እርሱ ታላቅ አሰልጣኝ ነው። በእርሱ የሰለጠንኩባቸውን ግዝያቶች ተዝናንቼባቸዋለሁ። አንድ ቀን አብሬው እንደምሰራም ተስፋ አለኝ"

(ምንጭ፦ Thesun)

Tuesday, November 20, 2018

ማን ዩናይትዶች ለሴኔጋላዊው ያቀረቡት ሪከርድ የ77 ሚ.ፓ ሂሳብ ውድቅ ተደረገ


ማንቸስተር ዩናይትዶች ሴኔጋላዊውን ተከላካይ ለማዛወር ለክለቡ የአለም የተከላካዮች ውዱን ዋጋ የ77 ሚሊዮን ፓውንድ ሂሳብ አቅርበው ነበር። ሆኖም የካሊዱ ኩሊባሊ ክለብ ናፖሊዎች የዝውውር ሂሳቡን ውድቅ አድርገውባቸዋል።

ዛሬ አርጀንቲናዊው እውቅ ጋዜጠኛ ታይክ እንዳለው ከሆነ ለ27 አመቱ ተከላካይ ዝውውር የቀረበውን የ£77 million ሂሳብ ናፖሊዎች ወዲያውኑ ውድቅ አድርገውታል። ዩናይትዶች ሴኔጋላዊውን ኢንተርናሽናል ተጭዋች ማዛወር ከፈለጉ ለዝውውሩ £89m ሂሳብ ይዘው ካልመጡ እንደማይለቁላቸው የሴሪአው ክለብ አሳውቋቸዋል።

በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትዶች IVAN PERISIC ከኢንተር ሚላን በቅናሽ የዝውውር ዋጋ በጥር ሊያዛውሩት ይችላሉ።

ኢንተር ሚላኖች ተጭዋች የመሸጥ ግዴታ ውስጥ ናቸው። እንደ Calciomercato ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ የጣሊያኑ ክለብ ፔሪሲችን ለመልቀቅ የ£31million ሂሳብ ከቀረበላቸው በቂ ነው።

ኢንተሮች በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር በFinancial Fair Play regulations ምክንያት ማስጠንቀቂያ የደረሳቸው ሲሆን እስከ መጪው ጁን ወር ድረስ ክለቡ የ £44m ሂሳብ ካላስመዘገበ ለቅጣት ሊዳረግ ስለሚችል ተጭዋቾችን ለመሸጥ ሊገደድ ይችላል ተብሏል።

ማክሰኞ ምሽት የወጡ አዳዲስ የዝውውር ዜናዎች

ፈረንሳዊው አማካይ ፖል ፖግባ ለቅርብ ሰዎቹ እንዳለው ከሆነ ማንቸስተር ዩናይትድን በመለቀ ወደ ጁቬንቱስ መመለስ እንደሚፈልግ ተናግሯል።
(ምንጭ፦ Corriere dello Sport)


PSGዎች የማንቸስተር ዩናይትዱን መሃል ተከላካይ ኤሪክ ቤይሊን ለማዛወር የሚደረገውን ፉክክር ተቀላቅለዋል። ተጭዋቹ ከጆዜ ሞሪንዎ ምርጫ ውጪ ከሆነ ቆይቷል።  (ምንጭ፦ Daily Mail)


ጁቬንቱሶች ሄክቶር ሄሬራን ለማዛወር የሚደረገውን ፉክክር ተቀላቅለዋል። ሜክሲኮአዊው ኢንተርናሽናል ከፖርቶ ጋር ኮንትራቱን ያላደሰ ሲሆን ጁቮንቱሶች የክረምት የዝውውር መስኮት ከመከፈቱ ቀደም ብለው ጥር ላይ የቅድመ ኮንትራት ስምምነት ሊያፈራርሙት አስበዋል።  (ምንጭ፦ Record)


ባርሶሎናዎች አሁንም የቀድሞ ኮከባቸውን ኔይማር ለመመለስ ጠንክረው እየሰሩ ነው። የ26 አመቱ ብራዚላዊ ኮከብ የካታላኑን ትልቅ ክለብ በድጋሚ ቤቱ የማድረግ ፍላጎት አለው።  (ምንጭ፦ MARCA)


ኤዲን ዤኮ ሳይጠበቅ የሪያል ማድሪድ የዝውውር ኢላማ ሆኑአል። ክርስቲያኖ ሮናልዶ ክለቡን ከለቀቀ በኃላ ቦታውን የሚተካ ሁነኛ ጎል አዳኝ አጥቂ ያጡ ሲሆን ዤኮ ይሄንን ችግር እንደሚቀርፍላቸው ተስፋ ጥለውበታል።   (ምንጭ፦ AS)


ቼልሲዎች የጁቮንቱሱን ግራ ተመላላሽ ተከላካይ አሴክስ ሳንድሮን ለማዛወር የ£50 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ሊያቀርቡ ነው።  (ምንጭ፦ Daily Express)


ጁቬንቱሶች የማንቸስተር ዩናይትዱን የ21 አመት አጥቂ ማርከስ ራሽፎርድ ወደ ቱሪን ለማዛወር ከወዲሁ ዶሴ ማቀናበር ጀምረዋል። እንግሊዛዊውን አጥቂ በክረምቱ ለማዛወር ተስፋ ሰንቀዋል።
(ምንጭ፦ The Times)


ሪያል ማድሪዶች በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ የPSGውን አጥቂ ኔይማር ማዛወር የማይችሉ ከሆነ እንግሊዛዊውን የቶተንሃም አጥቂ ሃሪ ኬን ወደ በርናባው የማዛወር እቅድ ይዘዋል።
(ምንጭ፦ Tuttosport)


ሊቨርፑሎች የፍራንክፈርቱን አጥቂ ሉካ ጆቪችን ለማዛወር አልመዋል። የርገን ክሎፕ የፊት መስሩን ተጭዋች በማዛወር የሮቤርቶ ፊርሚኖ ሽፋን እንዲሆናቸው ይፈልጋሉ።   (ምንጭ፦ Football London)


ጆዜ ሞሪንዎ ቤልጂየም አይስላንድን ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ባለፈው አርብ በስቴዲየም ተገኝተው ጨዋታውን የተከታተሉት ሲሆን የዶርትመንዱን አማካይ አክስል ዊትሰል እንቅስቃሴ ገምግመዋል።
(ምንጭ፦ Het Laatste Nieuws)


ዣካ በአርሰናል የሚያቆየውን አዲስ ኮንትራት በክረምት ስለመፈረሙ:  “ክለቡ እስከ 2023 ድረስ የሚያቆየኝ አዲስ ኮንትራት እንድፈራረም ማቀዱ ይበልጥ ያስደሰተኝ ጉዳይ ነው። ቡድኑ ለኔ ትልቅ አድናቆት እና ተፈላጊነት እንዳለኝ እንዲሰማኝ አድርጒል። ለክለቡ ራሴን እንደ አንድ አስፈላጊው ሰው እንድቆጥር አድርጎኛል።"

"እስካሁን በክለቡ ድንቅ የውድድር አመት ያሳለፍኩበት ሲዝን ነው። ያለጥርጥር በዚህ አመት ወደፊት እንደተራመድኩ ይሰማኛል። ወደ ክለቡ ከመጣሁ ወዲህ እያሳለፍኩ ያለሁት ድንቅ አመት ነው። ለዚህም የአዲሱ አሰልጣኝ ተፅህኖ ቀላል ሚባል አይደለም"  (ምንጭ፦ Aargauer Zeitung)


ቨርጂል ቫንዳይክ ከጀርመን ጋር ነጥብ ከተጋሩበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኃላ የመሃል ዳኛውን ስለምን እንደዛ ቀርቦ በጆሮው ሲያናግረው እንደነበር ተጠይቆ ሲመልስ: "ልቡ ተሰብሮ ነበር። በእንባ አይኖቹ ሞልተው መሃል ላይ ፈዞ ቆሞ ነበር። እንዲበረታ ነግሬዋለሁ፤ ጨዋታውን በጥሩ ሁኔታ መርቶታል። ያልኩት ነገር ትንሽ ነገርና ማፅናናት ብቻ ነው።" - የዕለቱ ዳኛ Ovidiu Hategan ጨዋታውን የመሩት እናታቸውን በሞት እንዳጡ በተረዱበት ቀን ነው።


ሮቢ ፎውለር እንዳለው ከሆነ ቀያዮቹ በዚህ የውድድር አመት የሊጉ ውድድር ላይ ቶፕ 4 ውስጥ ገብተው ብቻ ለመጨረስ ከሆነ የሚጫወቱት ትልቅ ውድቀት ነው። ቡድኑ በዚህ ወርቃማ የየርገን ክሎፕ ዘመን ዋንጫዎችን ማንሳት እንዳለበት አሳስቧል። "ለኔ ይሄ ተቀባይነት የለውም። እኔ ቡድኔ ቶፕ 4 ውስጥ ጨረሰልኝ ብዬ የምፈነጥዝ ደጋፊ አይደለሁም። ዋንጫዎችን ከቡድኑ እጠብቃለሁ።"
(ምንጭ፦ skysports)


የላ ሊጋው ዋና አስተዳዳሪ ጃቪየር ቴባስ : "እኔ ቀድሞውንም ቢሆን ከ2 አመታት በፊት ስናገረው የነበረ ጉዳይ ነው። ፒ.ኤስ.ጂ እና ሲቲዎች እያጭበረበሩ ነው ስለዚህ አሁን እየተደረገባቸዉ ያለው ምርመራ አላስገረመኝም። የUEFA ማህበር በጉዳዩ ዙሪያ የሆነ ነገር ማድረጉ ተገቢ ነው። የነርሱ አካሄድ የአለም እግርኳስ አካሄድን ባላንስ ያዛባ ነው። እንደዚህ አይነት ቡድኖችን መቅጣት ተገቢ ነው።"
(ምንጭ፦ Goal)


ማንቸስተር ሲቲዎች ኮሎምቢያዊውን የ17 አመት አማካይ አንድሬስ አማያን ለመዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ሮማን ተቀላቅለዋል። ተጭዋቹ ለአትሌቲኮ ሁሊያ በመጫወት ላይ ሲሆን ለዝውውሩ የ£2.7 ሚሊየን በቂ ነው ተብሏል።   (ምንጭ፦ TMW)


ቼልሲዎች የቡድናቸው አምበል እና ተከላካይ ጋሪ ካሂል በጣሊያኑ ሴሪ አ ክለብ ኤሲ ሚላን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ኢላማ ተደርጎአል።
(ምንጭ፦ 90min)


የቼልሲው አጥቂ ኦሊቨር ዥሩድ ሰማያዊዎቹን ለመልቀቅ ተሰናድቷል ስለሚባለው የዝውውር ጭምጭምታ ሃሰት መሆኑን ገልፆ ይልቅ በክለቡ በመቆየትና ቋሚ ተሰላፊ ለመሆን ጠንክሮ እንደሚሰራ ገልፆአል።  (ምንጭ፦ 90min)


ማቲዮ ኮቫሲች በበኩሉ ከሪያል ማድሪድ ወደ ቼልሲ ያደረገው የውሰት ውል ቋሚ አድርጎ ስለመፈረም አለመፈረሙ ጉዳይ ዙሪያ እንዲጠየቅ እንደማይፈልግ ለጋዜጠኞች ተናግሯል።  (ምንጭ፦ 90min)

Monday, November 19, 2018

Moments: የፈርዲናንድ የህይወት ትራጀዲ (ከመንሱር አብዱልቀኒ)



"ክቡራትና ክቡራን የዚህ ሽልማት አሸናፊ… ሪዮ ፈርዲናንድ!" የሚለው የምስራች ከመድረክ ላይ ሲሰማ አዳራሹ በጭብጨባ ቀለጠ። ሪዮ ቄንጠኛ ሱፍ ኮቱን ቆልፎ አጠገቡ ተቀመጠችውን ሴት ጉንጭ ስሞ ወደ መድረኩ አመራ። ሜይ 14 ቀን 2018…።

የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል በቴሌቪዥን ዘጋቢ ፊልሞች ዘርፍ  "Being Mum and Dad" በሚለው በቢቢሲ ቴሌቪዥን በተላለፈው ፊልሙ የባፍታ ሽልማት ማግኘቱ ነበር።

ባማረው የለንደን ሮያል ፌስቲቫል አዳራሽ ለሽልማቱ ምስጋናውን ሲያቀርብ ሪዮ እምባ ይተናነቀው ነበር።

በሜይ 2015፣  ከጥቂት ወራት የካንሰር ህመም በኋላ ሬቤካ ፈርዲናንድ ከሪዮና ከሶስት ህፃናት ልጆቿ በሞት ተለየች። ህመሙ ፈጥኖ በመላው ስውነቷ በመዛመቱ ለ34 ዓመቷ ሬቤካ አጣዳፊ ነበር። ባለቤቱ ባላሰበው ፍጥነት ከጎኑ የተለየችበት ሪዮ በድንገት ሰማይ ተደፋበት፣ ምድሩ ሁሉ ጨለመበት። ህፃናቱን ያለእናት ስለማሳደግ ማሰቡ በራሱ ዳገት ሆነበት። ልጆቹን አይውጣቸው ነገር፣ ምን እንደሚያደርጋቸው ጨነቀው።

"ህይወቴ ሁሉ ጨለማ ውስጥ ገባ። ጓዳዬ ገብቼ ለብቻዬ ተንሰቅስቄ ማልቀስ የዘወትር ልማዴ ሆነ። አልወጣልህ አለኝ። የሚሰማኝ የተለየ ስሜት ነበር። እንደ እግር ኳስ ተጫዋችነቴ የመልበሻ ቤት መንፈስ የተጠናወተኝ ነኝና ስሜታዊ ጉዳቴን ለማንም ማማከር አልፈለግኩም። ለራሴው ይዤው ተብከነከንኩ።

"ልጆቼ 'እናት የሌለን ለምንድነው?' ብለው ቢጠይቁኝስ? ምን መልስ ይኖረኛል? …በሐዘንና ጭንቀት ተጎዳሁ። ከዚህ ስሜት ለመሸሽ ከመጠን በላይ አልኮል ማዘውተር ጀመርኩ።"

ምሽት ወደ ልጆቹ መኝታ ቤት ይገባል። አልጋቸው ጎን ሆኖ ከገጠመው ሃዘን ሌላ ነገር ማሰብ አይችልም።

"የሬቤካ ከጎናችን መለየት ያብሰለስለኛል። ከዚያ ወደታችኛው ፎቅ እወርድና በሃዘንና ተስፋ መቁረጥ ከአልኮል መጠጥ ጋር ግብግብ እይዛለሁ። አለቅሳለሁ፣ እጠጣለሁ፣ እጠጣለሁ፣ እጠጣለሁ…።"

ሎሬንዝ (11 ዓመት) እና ታቴ (9 ዓመት) ወንዶች ናቸው። ሶስተኛዋ ቲያ 6 ዓመቷ ነበር። እናታቸውን ቢያጡም በአያታቸው ተፅናኑ። የሪዮ እናት መኖሪያ ቤት ልጆቹ ለሚኖሩበት ሰፈር ቅርብ ስለነበር ህፃናቱ የአያታቸውን ፍቅር በማግኘታቸው ደስተኞች ነበሩ። ከትምህርት ቤት በፊት፣ በኋላና በሌላም ጊዜ ህጻናቱ የአያታቸውን ዳበሳና ምክር ለመዱ። ግን ይህም ብዙ አልቆየም። በጁላይ 2017፣ ሪዮ ባለቤቱን በሞት ከተነጠቀ ሁለት ዓመት ሳይደፍን የሚወዳት እናቱን በተመሳሳይ በሽታ አጣ።

ካንሰር በአጭር ጊዜ ውስጥ ሪዮ ፈርዲናንድን ያለ እናትና ሚስት፣ ልጆቹን ደግሞ ያለ እናትና አያት አስቀራቸው። ልጆቹም በፈተና ውስጥ አለፉ።

"በህይወቴ ሁሉ ምሳ አዘጋጅቼ፣ ምሳ ዕቃ ቋጥሬላቸው አላውቅም። ሬቤካ በህይወት ሳለች ማልደው ተነስተው፣ ቁርስ ተመግበውና ተዘገጃጅተው ወደ ትምህርት ቤት ሊወጡ 10 ደቂቃ ሲቀራቸው እኔ ከአልጋዬ መነሳትን የለመድኩ ሰው ነኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ ምሳ የቋጠርኩላቸው ቀን ግን በጣም ረፈደባቸው።"

ሃዘኑ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ ቤት ሰርቶበት ራሱን ስለማጥፋት ማሰብ ጀመረ። አልኮል ማዘውተሩ ደግሞ ራስህን ግደል የሚለውን ርኩስ ሃሳብ አበረተባት። ያን ጊዜ በርካታ ሰዎች ሊረዱት መጡ። የምክር አገልግሎትም አላጣም። በመከራ የተልፈሰፈሰው የኳስ ሜዳ ጀግና የሚያሳሱትን ልጆቹን እየተመለከተ ተፅናና። ለእነርሱ ሲል መኖር እንዳለበት ራሱን አሳመነ። እነርሱም እንዲጠነክሩ የእርሱ መፅናት አስፈላጊ ነበር።

የከበደ ሃዘን ተጭኖት ከወደቀበት እንደ ምንም ሲነሳ ፈርዲናንድ "እናትም፣ አባትም ሆኖ መኖር" የሚለውን መፅሐፉን አሳተመ። የተጋፈጠው ፈተና ተመሳሳይ ርዕስ ባለው የቴሌቪዥን ዘጋቢ ፊልም ላይ ተተረከ። ፊልሙን ያየ ሁሉ ሪዮን አፅናናው።

"ከፊልሙ መለቀቅ በኋላ በየመንገዱ ላይ ወጣቶች፣ ጎልማሶች፣ አዛውንቶችና አያቶች ሲያገኙኝ ስለእግር ኳስ ማውራትን ትተው እንድበረታ በምክራቸው ይደግፉኝ ነበር" ይላል ሪዮ  - ስለዶክመንተሪው ሲናገር።

ሟች ሬቤካ፣ ሊዛ የተባለች ጓደኛ ነበረቻት። ከህልፈቷ በኋላ ሬቤካ ለሊዛ የተናገረችውን ሪዮ የሰማው ዘግይቶ ነበር። ያቺ መልካም ሴት በሞት አፋፍ ላይ ሳለች ስለሪዮ የወደፊት ህይወት ምኞቷን ለሊዛ ገልፃላታለች።

"ሪዮ የሌላ ሴት ስለመሆኑ ማሰብ በራሱ ለእኔ ሞት ነው። ነገር ግን ብቸኛ ስለመሆኑ ማሰብ ደግሞ ይበልጥ የሞት፣ ሞት ይሆንብኛል። ስለዚህ እኔ ከሞትኩ ከጎኑ የማትለይ አፍቃሪና ደጋፊ ታስፈልገዋለች። ሪዮ በህይወቱ ሁሉ ደስተኛ እንዲሆን እፈልጋለሁና አፍቃሪ ማግኘት አለበት።"

ዘጋቢ ፊልሙ የባፍታን ሽልማት በማሸነፉ ስሙ ሲጠራ ፈርዲናንድ ከመቀመጫው በመነሳት ኮቱን ቆልፎ የሳማት ሴት ኬት ራይት ትባላለች። የ27 ዓመቷ የሪያሊቲ ቴሌቪዥን ተዋናይት ተጫዋቹ ሃዘኑን እንዲረሳ ያስቻለችው፣ ሟች ባለቤቱ የተመኘችለት ሴት ሆና ተገኘች። በያዝነው የፈረንጆች ወር መጀመሪያ በአቡዳቢ፣ ሪዮ ፈርዲናንድ ለሌላ ዘላቂ ህይወት በኬት ራይት ጣት ላይ የቃልኪዳን ቀለበት አኖረ። ጥንዶቹ ሲተጫጩ ሶስቱም ህፃናት በአጠገባቸው ቆመው የአባታቸውን ደስታ መመለስ ይመለከቱ ነበር።

(ምንጭ ፦ መንሱር አብዱልቀኒ ፌስቡክ ገፅ)

Saturday, November 17, 2018

ቅዳሜ ምሽት የወጡ አዳዲስ የዝውውር ዜናዎች



ቼልሲዎች የ20 አመቱን አሜሪካዊ ኢንተርናሽናል የቦሩሲያ ዶርትመንድ አማካይ ክሪስቲያን ፖሊሲችን ለማዛቀር ተቃርበዋል። ዝውውሩን በጥር ወር ላይ ለማጠናቀቅ እየሰሩ ይገኛል።
(Source: Daily Mail)

.

ጁቬንቱሶች የሊቨርፑሉን የ25 አመት ብራዚላዊ አማካይ ስፍራ ተጭዋች ፋቢንዎን ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ኤሲ ሚላንን ተቀላቀሉ።
(Source: Sport Mediaset)

.

ሪቨር ፕሌቶች ፓላሲዎን ለሪያል ማድሪድ ሸጠዋል መባሉን አስተባበሉ። ከአርጀንቲና ማምሻውን የወጡ በርካታ ሪፖርቶች ሪቨር ፕሌቶች አማካያቸውን ኢዝኩዌል ፓላሲዎስን ለሪያል ማድሪድ በ€20 million ወይም (£17.7m/$22.8m) ሂሳብ ሸጠውታል ቢባልም አስተባብለውታል።

.

አርሰን ዌንገር PSGዎች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ የአርሰናሉን አማካይ አሮን ራምሴይን እንዲያስፈርሙት ጥቆማ ሰጥተዋል። የመድፈኞቹ አማካይ ውል በቀጣዩ ክረምት የሚጠናቀቅ ሲሆን ወደ በነፃ የዝውውር ውል ወደፈለገበት ክለብ መፈረም ይችላል። እናም Daily Mirror ጋዜጣ እንዳለው ከሆነ የቀድሞው የክለቡ አለቃ ዌንገር የፈረንሳዩ ክለብ ተጭዋቹን ከባየር ሙኒክ መንጋጋ መንጥቀው እንዲያስፈርሙት ምክር ሰጥተዋቸዋል።

.

ባርሴሎናዎች የአያክሱን ኮከብ ታዳጊ አማካይ ፍራንክ ዲ ጆንግ ቁጥር አንድ የዝውውር ኢላማቸው አድርገውታል እንደ Mundo Deportivo ከሆነ። የካታላኑ ክለብ የሰርጂዎ ቡስኬትን የረጅም ግዜ ተተኪ በማፈላለግ ላይ ሲሆኑ ዲ ጆንግ ከክለቡ ስካውቲንግ ሪፖርት ላይ ጎልቶ የወጣ አመካይ በመሆኑ ዋነኛ የዝውውራቸው ኢላማ ሆኖአል።

.

ማንቸስተር ሲቲዎች በዳርኮ ግያቢን ዝውውር ፉክክር ላይ አርሰናል እና ዎልቭሶችን ረተዋል። እንደ The Sun ዘገባ ከሆነ ለተጭዋቹ ዝውውር £300,000 ብቻ ይከፍላሉ። ውሉ ተጭዋቹ የሲቲን ዋና ቡድን ሰብሮ የሚገባ ከሆነ ክፍያው ወደ £1 million ሊያድግ ይችላል። የፊል ፎደንን ፈለግ እንደሚከተል ሲቲዎች ተማምነውበታል።

.

ኮሎምቢያዊው አጥቂ ራድሜል ፋልካዎን በጥር እንዲያስፈርሙት ለሪያል ማድሪዶች ቀርቦላቸዋል። እንደ Marca ዘገባ ከሆነ የቀድሞው የአትሌቲኮ ማድሪድ ኮከብ በአዲሱ የቲየሪ ሄነሪ ቡድን ውስጥ አንዳንዴ ሲጫወት አንዳንዴ ሲቀመጥ ተመልክቷል። ምንም እንኳን ኮልምቢያዊው አጥቂ በሞናኮ የሚያቆየው የ18 ወራት ውል ያለው ቢሆንም በአዲሱ አመት ላይ ወኪሉ ወደ ማድሪዱ ከተማ ክለብ ሊመልሰው እየሰራ ይገኛል።

.

የማን.ዩናይትዱ ሊቀመንበር ውድዋርድ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ የአትሌቲኮ ማድሪዱን መሃል ተከላካይ ዲያጎ ጎዲንን እንደሚያዛውሩት እርግጠኛ ሆነዋል። Daily Star እንዳለው ከተጭዋቹ ክለብ ጋር ከወዲሁ ድርድር ላይ ሲሆኑ በክረምቱ ፈልገው ያጡትን ኡራጓዊ ተከላካይ ወደ ኦልትራፎርድ ውድዋርድ በግዜ ድርድር ላይ በመሆናቸው ጆዜ ሞሪንዎ በጥር ያገኙታል።

.

አርሰናሎች በአዲስ መልክ ሊመሰረት እንቅስቃሴ ላይ በሆነው የEuropean Super League የመመስረት ሃሳብ ውይይት ላይ መሳተፋቸውን አመኑ። ሆኖም መድፈኞቹ እንዳሉት ከሆነ ፕሪሚየር ሊጉን ሊጎዳ የሚችል የትኛውም ጉዳይ ላይ ተሳትፎን እንሰማያደርጉ አረጋግጠዋል።

Friday, November 16, 2018

ያ ምሽት ፖል ስኮልስ፣ ያ ማሊያ አንድሬስ ኢኔሽታ (የአሸናፊውና ተሸናፊው ወግ)



"ስለዚያ የፍፃሜ ጨዋታ ሳስብ፣ የሚታወሰኝ የመጨረሻው 30 ደቂቃ ነበር" ይላል ኤሪክ አቢዳል። ስለ2011ዱ ቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ እያወራ ነው። ገና ሊጠናቀቅ ግማሽ ሰዓት እየቀረው የማንቸስተር ዩናይትድ ተጫዋቾች መሸነፋቸውን አምነው ተቀበሉ። የባርሴሎናን የምሽቱን ኃያልነት ምንም አይነት ጥረት ሊቀለብሰው እንደማይችል ዩናይትዶች ቀድመው ተረዱ። እንደው ቦክስ አይደል ፎጣ አይወረወር ነገር!

የባርሳ ልጆች ይጫወቱታል። በእግሮቻቸው ቅብብል ሜዳውን በአይነ ህሊናዊ መስመሮች ይሸረካክቱታል፣ ያለ እጅ ንክኪ ይከፋፍሉታል፣ ያለ ቢላዋ ይበልቱታል። እኒያ ታላቅ ጀግና ሰር አሌክው ፈርጉሰን እንኳን ዓይኖቻቸው በካታላኑ ጥበባዊ ትርምስ ቦዘው ስልት የተሟጠጠበት የጦር መሪ መስለዋል።

ኢኒዬሽታ ለቻቪ…፣ ቻቪ ለሜሲ ይሰጠዋል።… ከዚያ ቡስኬትስ ይመጣና ይቀበላል፣ መልሶ ያቀብላል። ፒም-ፓም…፣ ፒም-ፓም…፣ ፒም-ፓም…።

"እንግሊዛዊያኑ ተጫዋቾች ተማረሩ" አቢዳል ስለመጨረሻው 30 ደቂቃ ትውስታውን ቀጠለ።

"ዌምብሌይን ወደ ግዙፍ ሮንዶ (መሐል ባልገባ) ስለቀየርንባቸው ብስጭት ገባቸው። ሊያቆሙን አቃታቸው። አቅመ ቢስ ሆኑ።

"የብልግና ቃላትን ጨማምረው የብስጭታቸውን ያህል ይናገራሉ። ምን ቀራቸው…፣ ከፀሃይ በታች ባለ ስድብ ሁሉ ይጮሃሉ። ይገርማል። ከቡድን ጓደኞቼ አንዳንዶቹ ተጫዋቾቹ በቋንቋ ምክንያት ምን እያሉ እንደሆነ አልገባቸውም ነበር። እኔ ግን ተረድቼዋለሁ። "…በቃኮ! አልቆልናል፣ ሞተናልኮ። በቃ! ለምን አይበቃችሁም?" ሲሉን ጨዋታው ሊያልቅ ገና 25 ደቂቃ ይቀረው ነበር።

ቻቪ፣ ኢኒዬሽታ፣ ቡስኬትስ ቀጠሉ። ፒም-ፓም…፣ ፒም-ፓም…፣ ፒም-ፓም…።

አቢዳል እንከን የለሽ የቡድን ስራ፣ ወደ ውብ ጨዋታ ሲቀየር እያስተዋለና ራሱም እየተጫወተ ነበር። በህልም ዓለም የሚታሰበው ሁሉ እየሆነ ነው። ለእርሱ ልዩ፣ ከልዩም ልዩ ጨዋታ ነበር።

አቢዳል በመጀመሪያው አሰላለፍ ውስጥ ይካተታል ብሎ የገመተ አልነበረም። በጉበቱ ላይ የካንሰር ዕጢ መገኘቱ ከተነገረ ገና ሁለት ወር መሆኑ ነው። መጥፎው ዜና በተሰማ ማግስት ከጨዋታ በፊት መልበሻ ቤት ገብቶ ጓደኞቹን አበረታቷል። ከሁለት ቀን በኋላ ወደ ቀዶ ጥገናው ክፍል ሲገባ፣ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ለተጨዋች ጓደኞቹ "ጉበቱን የሚሰጠኝ" እያለ ይቀልድባቸው ነበር። ሜይ 28 ደግሞ በዌምብሌይ ለፍፃሜው ተሰለፈ።

"ልዩ የሆነብኝ ፑዮልና ቻቪ ዋንጫውን እንዳነሳ ዕድል ስለሰጡኝ ወይም በዌምብሌይ የሞቀ ድባብ ምክንያት እንዳይመስላችሁ። በፉትቦሉ ጥራት እንጂ…" ይላል።

ያኔ አንድሬስ ኢኒዬሽታ በችሎታው ተራራ ጫፍ ላይ ነበር። ዌምብሌይ ከጉዳት ነፃ የሆነበት የመጀመሪያው የፍጻሜ ጨዋታ ሆነለት። እንደ እምቦሳ እየፈነጠዘ፣ እንደ ልባም ፈረስ እየጎደፈረ፣ ኳሷን በተዓምራዊ ፍጥነትና ጥበብ ወደፈለገው ቦታ እየላካት ያዛታል።

የኦርኬስትራው አካል ቢሆንም አቢዳል ተመልካችም ጭምር ነበር። ካታላኑ በኳስ ቅብብል ያለድምፅ ያዜማሉ። ጥበብ በኢኒዬሽታ ያማረ መልኳን ስትገልጥ ፈረንሳዊው ተከላካይ እየታዘበ ይደመማል።

ቻቪ የአቢዳልን ትውስታ ያጠናክራል።

"…አዎን! አቢ እውነቱን ነው። ሩኒ ወደ እኔ መጣና አነጋገረኝ። 'አይበቃችሁም እንዴ? በቃ አሸንፋችኋልኮ' አለኝ። ሰዓቱ ግን 80ኛ ደቂቃ ገደማ ነበር። 'በቃ ኳሱን ማንሸራሸራችሁ ይብቃ  ' ይለኝ ነበር።…"

አያልቅ የለ የፍፃሜው ፊሽካ ተሰማ። ፔፕ ጋርዲዮላና ልጆቹ አሳምነው 3ለ1 አሸነፉ። ባርሳ የአውሮፓ ሻምፒዮን ተባለ።

ካርለስ ፑዮል የአምበልነቱን ጥብጣብ በፍቃደኝነት በአቢዳል ክንድ ላይ አሰረው። ከካንሰር ህመም በህክምና ጥበብ የተመለሰው አቢ ዋንጫውን በክብር ሲያነሳ ስኮልስ ባለ 18 ቁጥሩ ነጭና ቀዩን ማሊያ ለብሶ ትዕይንቱን ፈዞ ይመለከታል። በእውነት ይህን ያህል ተበልጠን እንሸነፋለን ብሎ አልገመተም ነበር።

በዚያች ምሽት፣ በለንደን የእግር ኳስ ካቴድራል ተሸናፊው ሰራዊት ዩናይትድ ቢሆንም፣ የድል አድራጊዎቹን ልብ ቀድሞ በአድናቆት ያቀለጠ ተጫዋች ከዚያ ወገን ውስጥ አለ። የባርሳ ከዋክብት ከፖል ስኮልስ ጋር መጫወትን ሲመኙ ኖረዋል። ቻቪ እጅጉን ያደንቀዋል፣ ኢኒዬሽታ "ምነው ከእርሱ ጋር በአንድ ቡድን ውስጥ ባጫወተኝ" እያለ አልሟል።

የእርሱን ማሊያ "እኔ እወስድ፣ እኔ እወስድ" እያሉ ሲጨቃጨቁበት አቢዳል ሰምቷል። በዚያ ምሽት አድናቂዎቹ በድል ደስታ ሰክረው ሳለ ስኮልስ ግን ከእነ ማሊያው ቆሞ የሽንፈቱን ራስ ምታት ያዳምጥ ነበር።

ተሸናፊው የአሸናፊዎቹን ፓርቲ እየታዘበ የዌምብሌይ ሜዳ አልበቃህ ብሎት፣ በእግሩ የነካው ሁሉ ወርቅ ሲሆንለት ያየው አንድሬስ ወደ እርሱ መጥቶ ማሊያውን ሲጠይቀው ሳይደነቅ አልቀረም።
                             
… ኢኒዬሽታ በተወለደበት ፎንቴያልቢያ የወይን እርሻ ባለቤት ነው። ከእርሻውም ጎን የወይን ጠጅ መጥመቂያ ፋብሪካ አለው። እዚያው መኖሪያ ቤቱን ገንብቷል። ከቤቱ ጓዳዎች በአንዱ፣ በወይን ጠጅ ማከማቻ ክፍል ግድግዳ ላይ በመስተዋት ፍሬም ውስጥ አንድ ብርቅዬ ማሊያ በክብር ተሰቅሏል። ፖል ስኮልስ በዌምብሌይዋ ምሽት የለበሰው ያ ማሊያ።

Thursday, November 15, 2018

ጆዜ ሞሪንዎ ያቺን ሰአት (በመንሱር አብዱልቀኒ)

ሞውሪንሆ ያቺን ሰዓት

በሪያል ማድሪድ መልበሻ ቤት የበግ ለምድ የለበሰ ተኩላ አለ። ጆዜ ሞውሪንሆ አድብቶ የሚያስጠቃቸውን የዚህን ፍልፈል ማንነት አላወቁም። ዕረፍት ነሳቸው። የመልበሻ ክፍሉን ድብቅ መረጃዎች ለጋዜጦች የሚሰጠው ማነው? ጆዜ ቆረጡ። "መጋለጥ አለበት" አሉ።

የጋዜጦችን ዕለታዊ ወሬ ሰብስበው በየማለዳው ጠረጴዛቸው ላይ የሚያስቀምጡላቸውን ሰዎች በወኪላቸው ዦርጌ ሜንዴዝ ኩባንያ "ጄስቲፊዩት" በኩል ቀጠሩ። ሰዎቹ ሚድያ የተነፈሰውን ሁሉ… እንደወረደም ይሁን ተብራርቶና ተተንትኖ ለአለቃቸው ያቀርባሉ።

የጆዜ ቀን ዘወትር ከማለዳው 2:00 ሰዓት ላይ ይጀምራል። በልምምድ ማዕከሉ በሚገኘው ቢሯቸው የጋዜጣ ላይ ዘገባዎችን፣ አስተያየቶችንና የቲቪ ፊልሞችን በማየት አይናቸውን ይገልጣሉ። ሚድያው የቡድኑን ምስጢር ሁሉ ይዞ መውጣቱን ቀጥሏል። ጆዜ አንጀታቸው እያረረ መልስ ያላገኙለትን ጥያቄ ይጠይቃሉ። ፍልፈሉ ማነው?

የመረጃውን ጥራት ሲመለከቱት ደግሞ በቡድኑ አባላት መካከል ባሉ ሰዎች በኩል የሚወጣ ምስጢር አልመስልህ አላቸው። የሆነ…፣ የተደበቀ ድምፅ መቅጃ ሳይኖር እንደማይቀር ጠረጠሩ። በድብቅ ንግግሮቻቸውን የሚያደምጥ ካልሆነ በስተቀር ያቦኩት ሳይጋገር ለአደባባይ ሊበቃ አይችልም።

ቡድኑ ከጨዋታ በፊት በሚያርፍበት ሆቴል ውስጥ የሚሰሩ ሁለት የፅዳት ሰራተኞች ድብቅ መቅረፀ ድምፅ እንዲፈልጉ አዘዟቸው። ሼራተን ሚራሲዬራ ተበረበረ፣ በየጥጋጥጉ ተፈተሸ። ምንም አልተገኘም።

ጆዜ ጦፉ። ቀጣዩ ጨዋታ ኤልክላሲኮ ስለሆነ ደም፣ ደም ሸቷቸዋል። ሲብስባቸው ለክለቡ ከፍተኛ አለቆች የተጫዋቾቻቸውንና ሰራተኞቻቸውን የስልክ ምልልስ እንዲጠልፉና የሚያወሩትን እንዲቆጣጠሩ ጠየቋቸው። አንዳንድ ተጫዋቾች ነገሩ በማስጠንቀቂያ መልክ ተነገራቸው። በእጅ ስልኮቻቸው በኩል የሚያወሩትን ነገር ይዘትና የሚያነጋግሩትን ሰው ማንነት እንዲመርጡ ተመከሩ።

አፕሪል 16 ቀን 2011፣ በቤርናቢዩ ከባርሳ ጋር ከመጫወታቸው ጥቂት ሰዓታት ቀደም ብሎ ማርካ ጋዜጣ "ዛሬ ፔፔ ይሰለፋል፣  ኬዲራ እና አሎንሶ ያጣምሩታል" ሲል ሜሱት ኦዚል ተጠባባቂ እንደሚሆን ዘገበ። እንደገና ምስጢር አፈተለከ።

ሰዓቱ ደርሶ ቡድኑ ሊሟሟቅ ሲወጣ ተጫዋቾች በሜዳው ላይ ያልተለመደ ነገር አስተዋሉ። ሳሩ ከወትሮው ይልቅ ረዝሟል። በቅጡ አልታጨደም። ረጅምና ደረቅ ነው። የባርሳን የኳስ ሂደት ለማወክና ለማዘግየት መሆኑ ግልፅ ሆነላቸው።

በጨዋታው ማድሪድ በትዕዛዝና በኃይል መከላከልን መረጦ አፈገፈገ። ባርሳዎች ደግሞ ኳሱን አብዝተው በእግራቸው ስር አቆዩ። ሁለት ፍፁም ቅጣት ምቶች ተሰጡና ሁለቱም ተቆጠሩ። አንድ በሮናልዶ፣ አንድ በሜሲ። የመጨረሻ ውጤት? ... 1- 1።

ከዚህ ጨዋታ በፊት ከጋርዲዮላ ባርሳ ጋር በተገናኙባቸው ሁለት ጨዋታዎች 0-2 እና 2-6 ተሸንፈዋልና አሁን ባያሸንፉም የቤርናቢዩ ደጋፊዎች እፎይታን አገኙ። አቻው ውጤት ግን የሪያልን የዋንጫ እድል የሚያጠብ ነበር።

ጆዜ ተጫዋቾች በመልበሻ ቤት እስኪሰባሰቡ ጠብቀው ማንባረቅ ጀመሩ። ስድብ አዘል የስፓኒሽ ቃላት እንደ በረዶ ውሽንፍር በተጫዋቾቹ ላይ ዘነቡ።

"ከሃዲዎች ናችሁ! ከዳተኞች! የማትታመኑ ናችሁ! ስለቡድኑ አሰላለፍ ለማንም እንዳትናገሩ ነግሬያችሁ ነበር። እናንተ ግን ከእኔ ወገን እንዳልሆናችሁ አሳያችሁ። የውሻ ልጅ ሁሉ! ብቸኛው ጓደኛዬ ግራኔሮ ብቻ ነበር። አሁን ግን እርሱንም ማመን እየቸገረኝ ነው። ብቻዬን ተዋችሁኝ። ከገጠሙኝ ቡድኖች ሁሉ እንደዚህ ከዳተኞች የበዙበት ስብስብ አይቼ አላውቅም…።"

የአሰልጣኙ ቁጣ ማለቁን ሳይጠብቅ ኢኬር ካሲያስ ጥሏቸው ወደ መታጠቢያ ክፍሉ ገባ። አንዳንዶቹም ተከተሉት። ንዴት እንደ ጉሽ ጠላ አናታቸው ላይ የወጣባቸው አሰልጣኝ በአፍታ እብደት አጠገባቸው ያገኙትን ሬድ ቡል በካልቾ ጠለዙት። ቆርቆሮው በኃይል በሮ ከግድግዳው ጋር ሲላተም እግረ መንገዱን በውስጡ የያዘውን ፈሳሽ በአቅራቢያው በሚገኙ ተጫዋቾች ፊት ላይ ረጨው።

ያኔ ጆዜ በንዴት በግነውና ተጨማሪ ስድቦችን አስከትለው፣ እየተቆጡ በመልበሻ ቤቱ ወለል ላይ በጉልበቶቻቸው ተንበረከኩ። ሲነሱም በዓይናቸው ስር እምባቸውን ይጠራርጉ ነበር። ዛቻ አስከትለው ለቁጣቸው ማሳረጊያ አበጁለት።

"ግዴለም! ለ[ፍሎሬንቲኖ] ፔሬዝ እነግረዋለሁ። ራሱ ወሬ አቀባዩን ፈልጎ ያጋልጠው። በቪዬትናም ብሆን ኖሮ፣ በጓደኛችሁ ላይ እንዲህ ስትቀልዱ ብመለከት ሽጉጤን መዝዤ በደፋኋችሁ ነበር…።"

Wednesday, November 14, 2018

የማርኮ አርናቶቪች ወኪል ደንበኛው በጥር የዝውውር መስኮት ወደ አንድ ትልቅ ክለብ ሊዛወር መሆኑን ገለፀ



አርናቶቪች እንዳለው ከሆነ ዌስትሃምን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ መልቀቅ ይፈልጋል።

አዉስትሪያዊዉ ኮከብ ከምርጥ ተጭዋቾች ጎን መጫወት እፈልልለሁ ያለ ሲሆን ወኪሉ እና ወንድሙ የሆነው ዳንዥል እንዳለው ከሆነ ቀጣይ ሊዛወር የሚፈልግበት ክለብ የተሻለ ትልቅ ቡድን ነው።


MARKO ARNAUTOVIC ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግ በመናገር የክለቡን ደጋፊዎች አስደንግጧል።

የዌስትሃሙ አንበል ባለፈው ሲዝን ላይ የቡድኑ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ የጨረሰ ሲሆን ቡድኑ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን እንዳይወርድ ያድነናል ብለው ተፋ ያደረጉበት ተጭዋቻቸውም ነበር።

ሆኖም የቀድሞው የስቶክ ሲቲው ሰው ኮከብ በከፍተኛ ደረጃ መጫወት እፈልጋለሁ ብሏል። ወንድሙ እና ወኪሉ ዳንዥል ለአውስትሪያው ጋዜጣ Kurier እንዳለው ከሆነም ..

"አሁን ቀጣይ ክለብ ላይ ለመጫወት ተዘጋጅቷል።"

አርናቶቪች በበኩሉ ..
"አሁን የ29 አመት ሰው ነኝ። ይሄ ጥር እድሜዬ ነው።
ከምርጥ ተጭዋቾች ጋር መፎካከር ራሴን ማየት መፈለጌ ኖርማል ነው።

"ሆኖም በዚህ ጉዳይ ላይ ወንድሜን በጣም አምነዋለሁ።"

የአርናቶቪች ወንድም ተጭዋቹ በ2017 ላይ ከስቶክ ሲቲ ወደ መዶሻዎቹ በ£25 million የዝውውር ሂሳብ እንዲዛወር ያደረገ ወኪሉም ነው። እናም አሁንም ለተጭዋቹ ገዢ ክለብ ለመፈለግና ለመደራደር ቢዚ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ለአውስትሪያው ጋዜጣ እንዳለው ከሆነ ..

"አሁን ተጭዋቹ በፕሪሚየር ሊጉ የመጫወት በቂ ልምድ አዳብሯል። ይሄ ሊግ ደሞ ምርጥ ተጭዋቾች የሚገኙበት ሊግ ነው። ሆኖም ማርኮን ለመሰለ ጎበዝ ተጭዋች ደግሞ በዌስትሃም ብቻ መጫወት ትልቁ ግብ አይደለም።

"የዌስትሃም ቡድን አንዱ ትልቁ አካል እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም የተሻለ ክለብ መቀየሩ የሚቻል ነገር ነው።

"ለትልቅ ክለብ መጫወት አለበት። ማርኮ ለቀጣይ ስቴፑ አሁን ዝግጁ ሆኑአል። እንደርሱ አይነት ተጫዋች ለመውረድ በሚታገል ቡድን ውስጥ መጫወት የለበትም። ከፍ ባሉ ደረጃዎች ባላቸው ውድድሮችም ላይ መሳተፍ አለበት።

"ማርኮ ለዌስትሃም መጫወቱን ወዶታል። ክለቡን።እና ደጋፊዎቹን ከልቡ ይወዳል።"

የማርኮ አርናቶቪች የእግርኳስ ህይወት ስታቶች..

• ለትዌንቴ ክለብ : 59 appearances - 14 goals
• ለኢንተር ሚላን : 3 appearances - 0 goals
• ለወርደር ብሬመን : 84 appearances - 16 goals
• ለስቶክ : 145 appearances - 26 goals
• ለዌስትሃም : 46 appearances - 16 goals

"በጥር ሊለቅ የሚችልበት አማራጮች አሉን። እንደውም በክረምቱ ክለቡን ለመልቀቅ በጣም በጣም ተቃርቦ ነበር"

ማንቸስተር ዩናይትዶች የ29 አመቱን ተጭዋች ያስፈርማሉ በሚል በክረምቱ በተደጋጋሚ ስማቸው ሲነሳ ቆይቷል። እናም አሁንም በድጋሚ በጥር ወር ፊርማውን ለማግኘት እንደሚንቀሳቀሱ ይጠበቃል።

Tuesday, November 13, 2018

ማክሰኞ ምሽት የወጡ ተጨማሪ አዳዲስ የዝውውር ዜናዎች



ማንቸስተር ዩናይትዶች ምንም እንኳን አሌክሲስ ሳንቼዝ ክለቡን የመልቀቅ ፍላጎት ቢኖረውም እና እነሱ መሸጥ ቢፈልጉም በረብጣ ሳምንታዊ ደሞዙ ምክንያት ገዢ ክለብ ላናገኝ እንችላለን የሚል ስጋት ገብቷቸዋል።  (Source: Daily Telegraph)

.

የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች የ Brexit Deal ላይ ሊወያዩ ነው። ውይይቱ ፍሬያማ ሆኖ ተቀባይነትን የሚያገኝ ከሆነ በእያንዳንዱ ቡድን ውስጥ የሚጫወቱ የውጭ ሃገራት ቡድኖች አሁን ካሉበት 17 ወደ 12 ይወርዳል። ይሄ ማለት ደግሞ ሃገር በቀል ተጭዋቾችን ቁጥር ወደ 13 ከፍ ያደርጋል።  [Sky Sports]

.

ኬቨን ዲ ብሪያን ከተባለለት ጊዜ በፍጥነት አገግምም ወደ ሜዳ ሊመለስ ነው። ተጭዋቹ የቀድሞ ክለቡን ቼልሲ በዲሴምበር ወር ለመግጠም ብቁ ይሆናል። ዲ ብርያን ባሁን ሰአት ዲሰምበር 4 ላይ ዋትፎርድ ጨዋታ ላይ ለመመለስ ግብ አድርጎ እየሰራ ይገኛል።  [Guardian]

.

ጆዜ ሞሪንዎ ሁለቱን ተከላካዮቻቸውን ማርኮስ ሮሆ እና ኤሪክ ቤይሊን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በመሸጥ ከሽያጩ በሚያገኙት ገንዠብ ላይ ጨምረው ከቶቢ አልደርዌልድ እና ሚላን ክሪኒያር አንዳቸውን ለማስፈረም አስበዋል።
(Source: Daily Telegraph)

.

ምንም እንኳን በፊፋ ፋይናንሺያል ፋየር ፕላይ ህግ ጥሰት ምርመራ እየተደረገባቸዉ ቢሆንም ማንቸስተር ሲቲዎች የአያክሱን አማካይ ፍራንክ ዲ ጆንግን በ£50 ሚሊዮን የዝውውር ሂሳብ ለማዛወር አሁንም ሙከራ ላይ ናቸው።   (Source: Sun Sport)

.

ጁቬንቱሶች የቦሩሲያ ዶርትመንዱን እንግሊዛዊ የፊት መስመር ተሰላፊ ጃዶን ሳንቾ ለማዛወር እውነተኛ ፍላጎት አሳድረዋል።  (Source: Calciomercato)

.

የPSG'ው ብራዚላዊ ተመላላሽ ተከላካይ እግርኳስ በቃኝ ብሎ ከማቆሙ በፊት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጫወት ፍላጎት እንዳለው ገለፀ።
(Source: Daily Telegraph)


.

የማንቸስተር ዩናይትድ ተጭዋቾች ጆዜ ሞሪንዎ አማካዩን ኒማንያ ማቲች በቀጣዩ ጨዋታ ላይ ተጠባባቂ እንዲያደርጉት ይፈልጋሉ።  (Times)

.

ጆዜ ሞሪንዎ ኒማንያ ማቲች አቋሙ መውረዱ በግልፅ እየታየ ባለበት ሁኔታ ላይ ቋሚ ተሰላፊ ማድረጋቸው በተጭዋቾቹ መሃከል ጥያቄ አስነስቷል። አንዳንድ የቡድኑ ተጭዋቾች እና ስታፎች ተጭዋቹ የቱንም ያህል አቋሙ ቢወርድ የማይነካ እንደሆነ አምነዋል።   (times)

.

ሳንቲያጎ ሶላሪ እስከዚህ የውድድር አመት መጨረሻ ድረስ የክለቡ ቋሚ አሰልጣኝ በመሆን ከጊዜያዊ አሰልጣኝነት በቋሚነት ተሹመዋል።  (Source: AS)

.

ማንቸስተር ዩናይትዶች የአንቶኒዮ ቫሌንሺያን ኮንትራት ለተጨማሪ አንድ አመት ለማራዘም ንግግር በማድረግ ላይ ናቸው።   (guardian)

.

የአርሰናሉ ግብ ጠባቂ በርናንዶ ሌኖ እንዳለው ከሆነ ቢድኑ ዎልቭስን ከመግጠማቸው ከጥቂት ሰአታት በፊት በቡድኑ ቅድመ ዝግጅት ስብስብ ወቅት በከባድ ጉዳት ቀዶ ጥገና ያደረገውን አጥቂ ዳኒ ዌልቤክን በpre-match ቡድኑ ውስጥ እንዲካተት በማድረግ ፊት ለፊት አግኝተው እንደጎበኙት አሳውቋል።    (Standard)

.

ቪክቶር ሊንደሎፍ የ2018 የአመቱ የሲውዲን ምርጥ ተጭዋች በሚል የSwedish Golden Ball ሽልማት አሸነፊ መሆን ችሏል።

.

ማንቸስተር ዩናይትዶች የሁለቱን ስፔናዊ አማካዮች ዩሃን ማታ እና አንደር ሄሬራን ኮንትራት ለማራዘም ከተጭዋቾቹ ጋር ድርድር ማድረግ ጀምረዋል።  (men)

.

ማንቸስተር ሲቲዎች የደቡብ አፍሪካውን ከ17 አመት በታች አምበል ግብ ጠባቂ Constandino ወይም በቅፅል ስሙ ‘Costi’ Christodoulou, ለሁለት ሳምንት የሙከራ ጊዜ ሰጥተው ራሱን እንዲያሳይ ጋብዘውታል።    (Times Live)

.

አሌክሳንደር ላካዜቲ ከአርሰናል ክለብ ዶክተሮች ጋር ጥልቅ ምክክር እና ቼክ አፕ ካደረገ በኃላ ከፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን ደርሶት የነበረውን ጥሪ ሳይቀበለው ቀርቷል።   (Mail)

.

ናቢ ኪየታ በሊቨርፑሉ አለቃ የርገን ክሎፕ ስር በመሰልጠኑ 'እድለኛ' እንደሆነ ተናግሯል። ተጭዋቹ አክሎም የእንግሊዘኛ ችሎታውን ለማሻሻል ጠንክሮ ቋንቋውን እያጠናው መሆኑን ገልፆአል።

.

የ2018 የNorthwest Football Awards, በሚል በተዘጋጀው የሽልማት ስነስረአት ላይ የሊቨርፑል ክለብ ተጭዋቾች እና ክለቡ በአምስት ዘርፎች ሽልማት ማግኘታቸው ተሰምቷል። በመድረኩ ላይ የእውቅና ልዩ ሽልማታቸው ያገኙት ግለሰቦች ወይም ቡድኖች በእግርኳሱ ዘርፍ ሜዳ ላይም ሆነ ከሜዳ ውጪ ባለፈው አመት ሲዝን ላይ በሰሩአቸው ውጤታማ ተግባራት የተመረጡ ናቸው። (liverpoolfc)

.

ሽልማት ከወሰዱባቸው ዘርፎች መሃከል ሞሃመድ ሳላህ የPlayer of the Year, ሽልማትን ሲወስድ ተከላካዩ Trent Alexander-Arnold ደግሞ በተስፈኞች ጎራ የhome Rising Star of the Year, በሚል ተሸልሟል። ከሊቨርፑል ሴቶች ቡድን ደግሞ and Niamh መጪ ተስፈኛዋ ሴት ተጭዋች Women’s Rising Star of the Year በሚል ዘርፎች አሸናፊ መሆን ችለዋል።

.

የአርሰናል አካዳሚ ውጤት የተባለውና መጪው የአርሰናል ብሩህ ተስፋ የሆነው በውሰት ለጀርመኑ ቡንደስሊጋ ክለብ የሚጫወተው ሪስ ኔልሰን የቡንደስሊጋው የወሩ ምርጥ ወጣት ተጭዋች ‘Rookie of the Month’ በሚል ተሸልሟል።

.

የጀርመን ብሄራዊ ቡድን ተጭዋቾች እንደሁል ግዜው እንደሚያደርጉት በሌፕዚክ ትምህርት ቤቶች በመሄድ ከተማሪዎቹ ጋር ጥያቄ እና መልስ ያካሂዳሉ። የመጀመሪያው ጥያቄ የተጠየቀው ደግሞ ሎሪ ሳኔ ሲሆን ጠያቂው የአምስተኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ታዳጊ ነው ...

"ሳኔ ሜሱት ኦዚል ካሁን በኃላ ለጀርመን ብሄራዊ ቡድን አይጫወትም። በዚህ ዙሪያ አንተስ ምን ትላለህ?" ሲል ቢጠይቀውም ሳኔ በመሳቅ ሳይመልስለት በዛው አልፎታል።   (Plettigoal)

.

ቼልሲዎች የባርሴሎናውን አማካይ ተጫዋች ዳኒ ሱዋሬዝ በጥርየዝውውር መስኮት ላይ ለማዛወር ፍላጎት አሳድረዋል። ተጭዋቹ በካታላኑ ክለብ በቂ የመሰለፍ እድል እያገኘ ባለመሆኑ ክለቡን ሊለቅ ይችላል።   (90min)

.

ቤንጃሚን ሜንዲ በህመም ምክንያት እራሱን ከፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን ጥሪ ካገለለ በኃላ በInstagram አካውንቱ የለጠፈው ..

"በተቻለ ፍጥነት እመለሳለሁ! I’ll be
back asap"

.

ኤደርስን ስለ ማንቸስተር ደርቢ: "ከዩናይትዶች በእጥፍ የተሻልን ነበርን። እንደውም በደንብ ወደፊት ገፍተን መጫወት ብንችል ኖሮ የጎሉ መጠን ከዚህም በላይ በሰፋ ነበር"

 .

የቀድሞው የዌስትሃም፣ ቼልሲ እና እንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አማካይ ጆ ኮል ከእግርኳስ መገለሉን በይፋ አስታወቀ።   (Source:  SkySports)

.

ማንቸስተር ዩናይትዶች የተመላላሽ ተከላካዩን የአሽሊ ያንግን ኮንትራት ለአንድ ተጨማሪ አመት ለማደስ ንግግር እያደረጉ ይገኛል።  (Source: SkySports)

.

ጆዜ ሞሪንዎ ቡድኑን በዚህ የውድድር አመት ላይ በቶፕ 4 ውስጥ ደረጃ ይዞ እንዲጨርስ የማያደርጉት ከሆነ ክለቡ እንደሚያሰናብታቸው ተሰምቷቸዋል። ክለቡ የቶተንሃሙን ሞሪሲዮ ፖቸቲንዎ የፖርቹጋላዊው ምትክ ለማድረግ አቅዷል።  (Source: Sun Sport)

Monday, November 12, 2018

የጆዜ ሞሪንዎ የስንብት ወቅት ተቆርጧል፤ ክለቡ ምትካቸውንም ከወዲሁ ለይቷል



JOSE MOURINHO ከማንቸስተር ዩናይትድ መንበራቸው የሚሰናበቱበት ወቅት በግልፅ ተቀምጧል።

አሰልጣኙ በዚህ የውድድር አመት ላይ ቡድኑን ለቻምፒየንስ ሊጉ ውድድር ካላበቁት ይሰናበታሉ።


ዩናይትዶች ባሁን ሰአት በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ 8ተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። በደርቢው ጨዋታ ከተሸነፉ በኃላ ደግሞ ከመሪው ማን.ሲቲ ደግምም በ12 ነጥብ እርቀዋል።

በቀጣዩ የውድድር አመት ቡድኑ በቻምፒየንስ ሊግ የማይሳተፍ ከሆነ ሞሪንዎ መሰናበቱ እርግጥ ነው። የኦልትራፎርዱ ክለብ አሁንም ሞሪሲዮ ፖቼቲንዎን ከልብ ያደንቃሉ። ሆኖም አርጀንቲናዊው አለቃ በቶተንሃም በፈረመው ውስብስብ ኮንትራት ሳቢያ ክለቡን የመልቀቅ እና ቀያዮቹን የመቀላቀል እድሉ የጠበበ እንዲሆን አድርጎታል።

ሁለቱም ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሪያል ማድሪድ አርጀንቲናዊውን አለቃ ለማምጣት በጥብቅ ይፈልጋሉ ሆኖም የስፐርሱ አስተዳዳሪ ዳንኤል ሌቪ አሰልጣኙን ሞሪሲዎ ፖቸቲንዎ ላለመነጠቅ የማያደርገው ነገር አይኖርም።

ማድሪዶች ጊዜያዊ አሰልጣኝ ያደረጉት ሳንቲያጎ ሶላሪ ለአራት ተከታታይ ጨዋታዎች ካሸነፉ በኃላ የክለቡ ቋሚ አሰልጣኝ በማድረግ የሁለት አመት ኮንትራት ሰጥተውት ቋሚ አሰልጣኝ አድርገውታል።

ሆኖም ሶላሪ የቀድሞው የአርጀንቲና ቡድን አጋሩ ፖች በክረምቱ በቶተንሃሞች የሚለቀቁ ከሆነ ቦታውን ለሃገሩ ልጅ አስረክቦ ለመነሳት አያቅማማም።

ሞሪንዎ ባለፈው አመት ላይ በኦልትራፎርድ የሚያቆየውን አዲስ ኮንትራት የተፈራረመው ባለፈው አመት ላይ ነው። ሆኖም እርሱን ለማሰናበት ክለቡ መክፈል የሚጠበቅበት ሂሳብ የአመት ደሞዙ የሆነውን የ£15m ሂሳብ ብቻ ነው።

የቀድሞው የቼልሲ አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ ቡድኑን ይበልጥ ለማጠናከር ከቅርብ ጎረቤት ተቀናቃኛቸው ማን.ሲቲ እኩል በዝውውር እንቅስቃሴው በቂ ሂሳብ ክለቡ ማውጣት እንዳለበት በመናገር ቅሬታቸውን ገልፀው ነበር።

እንዲሁም መረጃው እንዳለው ፖርቹጋላዊው በክለቡ ስታንዳርዶች ላይ ጥያቄ ማንሳታቸው የሚታወቅ ሲሆን ለቅርብ ጔደኞቻቸው እንዳሉት ከሆነ ሁሉም ነገር በክለቡ 'ሁለተኛ ደረጃ' የሚሰጠው ነው።

ሞሪንዎ በክለቡ የተጭዋቾች ምልመላ ላይ እና የምልመላው ኔትዎርክ ላይ ጥያቄ ያላቸው ሲሆን ክለቡ ትልልቅ ተጭዋቾችን ለማዛወር የሚጠቀምባቸው የድርድር ስልቶትም ለሞሪንዎ የማይዋጡላቸው ኃላ ቀር መንገዶች ናቸው።

እንዲሁን በክለቡ የጉዞ አሬንጅመንቶች ላይ በተለይ ለቻምፒየንስ ሊጉ ከጁቬንቱስ እና ቫሌንሺያ ጋር ከመጫወቱ በፊት ቡድኑ በተደጋጋሚ በመዘግየት ለቅጣት መዳረጉ ሞሪንዎ ጥያቄ ያነሱበት ጉዳይ ነው።

ምንም እንኳን የክለቡ አስተዳዳሪዎች በቅርቡ ቡድኑ በሊጉ ላይ ያሳየውን መሻሻል በመደገፍ ድጋፋቸውን ለጆዜ የሰጡ ቢሆንም የቻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ግን ምንም ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም።

የትንሹ ሊዮኔል ሜሲ ህልም እና "ፒቤ" (ከመንሱር አብዱልቀኒ)



በዚያች ምሽት ሊዮ ሰማያዊውን ኳስ በአልጋ ውስጥ ሸሽጎ ጋደም አለ። አባት ሆርጌ ወደ መኝታ ክፍሉ ሲገባ እንዳላየ ሆኖ በአልጋው ላይ፣ ከልጁ ጎን ተቀመጠ።

"ግን አቧራውን ጠርገኸዋል?"

"አዎ አባዬ!" ... ሊዮ ኳሱን ደበቅ በማድረግ፣ ፈጠን ብሎ
የተለደፈበትን ቀይ ጭቃ ጠራረገ። ኳሱ ለልደት ስጦታ ከተበረከተለት አንድ ዓመት ሆኖታል። በሮዛሪዮ አቧራማ መንደሮች ላይ ሲለፋ ቆይቶ፣ የአዲስነት ገፅታውን አጥቷል። ተቦጫጭሯል፣ ተፋፍቋል። የሊዮ ምርጡ ጓደኛ ቆሽሾም ቢሆን ማታ አብሮት ይተኛል።

"ፀሎት አድርሰሃል?" አባት ጠየቀ።

"አዎን አባዬ! ፈጣሪ ቁመቴን እንዲያረዝምልኝ ጠይቄዋለሁ!" ሊዮ መለሰ። ገና ከጨቅላነቱ በኳስ ፍቅር የተለከፈው ታዳጊ ጭንቀት የተሰጥኦ ሳይሆን የተክለ ሰውነት ነበር። ፀሎቱም አምላክ የሌለውን እንዲሰጠው የሚማፀንበት ሆኗል።

ትንሹ ልጅ የቁመቱ ነገር እንዲህ ሲያስጨንቀው ማየት የአባትን ልብ የሚሰብር ነበር። በጎንዮሽ ተመልክቶት አዘነ። የጥፋተኝነት ስሜት አስጨነቀው። ለዚህ ተፈጥሯዊ ችግር መፍትሔ ለማግኘት አባት ከሚችለውም በላይ ቢሆን ጥረት ማድረግ እንዳለበት አመነ።

"የፒቤን ታሪክ ጓደኞችህ አውርተውልህ ያውቃሉ? ሲያወሩ ሰምተህ ታውቃለህ?"

"ፒቤ?... ፒቤ ምንድነው?" ሊዮ የአባቱን ጥያቄ በጥያቄ መለሰ።

"ፒቤ ማለት እግር ኳስን በሰፈር ጎዳናዎች ላይ በመጫወት ያደገ፣ ልዩ ተሰጥኦን የታደለ አርጀንቲናዊ ልጅ ማለት ሲሆን በብቃት ድሪብል ማድረግ የሚችሉት ብቻ የሚጠሩበት ስያሜ ነው።"

"እንደ ማራዶና አይነቱ?"

"አዎን! ልክ እንደ ማራዶና ማለት ነው። ማራዶና የዘመናችን ፒቤ ነው።"

"እና ታሪኩ የማራዶና ነው?"... የታዳጊው ሊዮ ጥያቄ ቀጠለ።

ሆርጌ ረጋ ብሎ መልስ ሰጠው።

"አይ! አይደለም ልጄ! ታሪኩ የማራዶና ሳይሆን ያንተ ነው"

ሊዮ እጅግ ተደሰተ። ሲያድግ ፕሮፌሽናል ተጫዋች መሆንና በማራዶና ስር መሰልጠን ምኞቱ ነበርና የአባቱ ወሬ አበረታው። ብሩህ ተስፋ አሳየው። ሆርጌ ታሪኩን እየተረከለት፣ ሊዮም እያደመጠ ወደ አባቱ ዞሮ ፈገግ እንዳለ፣ እንደተደሰተ እንቅልፍ አሸንፎት፣ አሸለበ።

…የዚያች ሌሊት ህልም፣ ተራ ህልም አልነበረም። በዚህ ዘመን እየሆነ ያለውን ሁሉ ቀድሞ፣ በለጋ ዕድሜው አርቆ ያየበት የእንቅልፍ ዓለም መነፅር ነበር!
                             
                                * * *

... ሊዮኔል ሜሲ ገና የአምስት ዓመት ታዳጊ ነበር። በሮዛሪዮ ከተማ፣ በ525 ኤስታዶ ደ ኢስራኤል ጎዳና በሚገኘው የቤተሰቡ መኖሪያ ቤት ጀርባ በሚገኘው ትንሽ ሜዳ ላይ  ኳስ በመጫወት ላይ ሳለ ወደ ጎሉ በድንገት ሲመለከት በሁለቱ የእንጨት ቋሚዎች መካከል ዲዬጎ ማራዶና ቆሞ አገኘው። ጥቁር ማሊያ ለብሶ በበረኛነት ግቡን ይጠብቃል።

ማራዶናን ሲመለከት ሊዮ በድንጋጤ ቆመ። ይህን ሲያይ፣ ዲዬጎ ይጮህበት ጀመር። "ሊዮ እንዳትቆም፣ ቀጥል! ቀጥል! ምታ!  ጨዋታው ያንተው ነው ፒቤ!"

ሊዮ ኳሷን ወደ ፊት በቄንጥ ገፋ አደረጋት፣ ወደ ቀኝ አጠፋት፣ ከዚያ በግራ እግሩ ጠበቅ አድርጎ በዲዬጎ ግራ በኩል ላካት። በማራዶና አናት ላይ ተንሳፋ፣ በግቡ አግዳሚ እንጨት ስር አልፋ ከመረቡ ጋር ተገናኘች።

ሊዮ እጁን ወደ አየሩ ዘርግቶ፣ በድል አድራጊነት ስሜት ወደ ማራዶና ተመለከተ። ሙከራውን ማዳን ባለመቻሉ በብስጭት የጦፈ ሰው ሲጠብቅ ያልገመተው ሆኖ ተገኘ። ዲዬጎ ደስተኛና ሳቂታ ሆኖ ያበረታታው ጀመር።

"አበጀህ! ሊዮ! ...ምትሃታዊ ነበር! አበጀህ!... ላ ኑኤስተራ!"

ዲዬጎ ተደስቶበት ሜሲን በሁለት እጆቹ  አንከብክቦ፣ እንደ ሳንቲም ወደ ላይ ወረወረው። ትንሹ ልጅ ወደ መሬት ከመውረድ ይልቅ በአየር ላይ ተንሳፈፈ። ቁልቁል ቢመለከት ማራዶና እያነሰ፣ እያነሰ ሄደ። ዲዬጎም ለመጨረሻ ጊዜ ጮክ ብሎ ነገረው።

"ሊዮ...! በእውነት አንተ ፒቤ ነህ!..."

ማራዶና ይህን ሲናገር ሜሲ በላዩ ላይ የተከመረው ፍርሃት ጥሎት ሲሸሽ ተሰማው። ወደ መሬት ሳይመለስ ዲዬጎን እንዲህ አለው።

"ፒቤው አንተ መስለኸኝ ነበርኮ!"

የማራዶና ድምፅ በደመናው ውስጥ እያስተጋባ ምላሹ ተሰማው።

"አዎን ሊዮ!... እኔ ፒቤ ነኝ። አንተ ደግሞ ቀጣዩ ፒቤ ትሆናለህ!"

ሊዮ ያየውን ማመን አልቻለም። አሁንም ተንሳፏል። ወደ ላይ ከፍታው ጨምሯል። ውሃ ውስጥ ያለ ይመስል፣ በመታጠቢያ ቤት ገንዳ ውስጥ እያስመሰለ እንደ ዋናተኛ እንደሚጫወት ሁሉ፣ በደመናው መካከል ይዋኛል። ቀና ሲል አይኖቹ የፀሐይዋን ነፀብራቅ ሊቋቋሙ አልቻሉም። የጨረሩ ድምቀት ከእንቅልፉ አነቃው።

ከህልም ዓለም ሲመለስ…፣ ራሱን በአልጋው ላይ፣ በአልጋ ልብሱ መካከል በደረቁ ሲዋኝ አገኘው። አቅፎ የተኛት ሰማያዊዋ ኳስ ከአልጋው ተሽቀንጥራ ወርዳ፣ በክፍሉ ወለል ላይ፣ መስኮቱ ስር ቆማ አገኛት።

ነግቷል።

"ይገርማል! ይገርማል!"... እያለ ሊዮ በመገረም፣ ከአልጋው ተነሳ። ለብቻው ያወራ ነበር።

"ምኑ ነው የሚገርመው?" አያቱ ሴሊያ መልስ ሰጡት።

"አያቴ፣ ከእስካሁኑ ሁሉ ምርጡን ህልም አየሁ።"

"እሺ! በቃ! ወደ ግራንዶሊ እየሄድን ምን እንዳለምክ ትነግረኛለህ!"

"ግራንዶሊ? እዚያ ምን እንሰራለን? ጨዋታ ልናይ?"... አለ ሜሲ፣ የአልጋ ልብሱን አንስቶ ወደ አያቱ አናት አቅጣጫ በመወርወር።

"እንዴ! ሄደህ ጨዋታ ማየት ብቻ ነው የምትፈልገው?" ሴሊያ በአናታቸው ላይ የተከመረውን ጨርቅ በማውረድ፣ ፀጉራቸውን እያስተካከሉ ጠየቁት።

"አይ! መጫወትም እፈልጋለሁ እንጂ!"

ሜሲ በዚያች ጠዋት ግራንዶሊ ለተባለው የህፃናት ቡድን ተመዝግቦ ለመጫወት ይሞክር ዘንድ አያቱ ወደ ቦታው ሊወስዱት አስበዋል....።

                              * * *

(የሊዮ ሜሲ አስደናቂው ህይወት ከሚለው የማይክል ፓርት መፅሐፍ ተወስዶ በአጭሩ ለመፃፍ እንዲመች ተብሎ የቀረበ)
                               * * *
(ምንጭ፦ መንሱር አብዱልቀኒ ፌስቡክ ገፅ)

Saturday, November 10, 2018

ዕለተ እሁድ በሳምንቱ መጨረሻ የወጡ አዳዲስ ከ30 በላይ የዝውውር እና ሌሎችም ዜናዎች


➣ ፖል ፖግባ እና ሮሚዮ ሉካኩ ከዛሬው የማንቸስተር ደርቢ ጨዋታ በፊት ለጨዋታው ብቁ መሆን አለመሆናቸውን የአካል ብቃት ምርመራ ያደርጋሉ።   [Mail]

.

➣ የአያክሱ መሃል ተከላካይ ማቲያስ ዲ ሊዥት ወደ ጁቬንቱስ ለመዛወር ሲል ከማንቸስተር ሲቲ እና ከባርሴሎና የቀረቡለትን ጥያቄዎች ውድቅ ለማድረግ ዝግጁ ነው።  (Calciomercato)

.

➣ ጆዜ ሞሪንዎ: "ሉካኩ ዝግጁ ነኝ ካለ የምፈልገው ያንን ነው። የቡድኑ መልሶ ማገገም አባላትም እየሰሩልኝ ያሉት በዚህ ዙሪያ ነው"  [Mail]

.

➣ ስፔናዊው የማንቸስተር ዩናይትድ አማካይ ዩሃን ማታ በክረምቱ የተጭዋቾ የዝውውር መስኮት ላይ ክለቡን በነፃ በመልቀቅ ወደ አርሰናል ለመዛወር ተዘጋጅቷል።  (Source: talkSPORT)

.

➣ ኦስማኔ ዴምቤሌይ ባርሴሎናዎች ሪያል ቤቲሲን ከሚገጥመው ቡድን ስብስብ ውጪ ሆኑአል። ቫልቬርዴ በቅርቡ ማልኮምን "ትልቅ የሆነ የግል አቲቲውድ አለው" በማለት ብራዚላዊውን አድንቆ ዴምቤሌይን ያሳነሰበትን አስተያየት ሰጥቷል። አሰልጣኙ ፈረንሳዊውን ኮከብ ከቡድኑ ውጪ ማድረጉ በሁለቱ መካከል ያለው ግንኙነት መበላሸቱን ያመላከተ ነው ተብሏል።  ተጭዋቹ ከአሰልጣኙ ጋር ግጭት ውስጥ የገባው ጉዳት ላይ እንደሆነ እየታወቀ ለቡድኑ በጊዜ ሪፖርት ባለማድረጉ ሲሆን ለልምምድ በመጣበት ሰአት ከዋናው ቡድን ውጪ ለብቻው ጂም እንዲሰራ ታዟል። ተጭዋቹ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ወደ ቼልሲ አልያም አርሰናል ሊዛወር እንደሚችል ተነግሯል።  (ArsenalNexus)
.

➣ ዛሬ እንደወጡ በርካታ ሪፖርቶች ከሆነ አርሰናሎች ፓትሪክ ሺክን በጥር ወር ላይ ለማዛወር እያደረጉት ያለው ሙከራ አሮን ራምሴይን የዝውውሩ አካል ሊያደርግ ይችላል። ያም ሆኖ ክለቡ በዳኒ ዌልቤክ ጉዳት ሳቢያ መድፈኞቹ የተጭዋቹን ፓትሪክ ሺክ ለማዛወር የሚያደርጉትን ጥረት ለግዜው በመግታት የሊሉን ኒኮላስ ፔፔን ለማዛወር የሚያደርጉትን ጥረት ቅድሚያ በመስጠት ይገፉበታል።

.

➣ ማንቸስተር ዩናይትዶች ማቲዮ ዳርሜይን በጥር ወር ለመሸጥ ከኢንተር ሚላን እና ሮማዎች ጋር ድርድር ማድረግ ጀምረዋል።   (Sun)

.

➣ የVAR ቴክኖሎጂ በዚህ አመቱ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ጫወታዎች ላይ ስራ ላይ ይውላሉ። UEFA በመስከረም ወር 2019 ላይ ይሄንን ቴክኖሎጂ እንደሚጠቀሙበት ገልፀው የነበረ ቢሆንም መልሰው የቫርን በጨዋታዎች ላይ በፍጥነት ተግባራዊ ስለማድረግ ለሳምንታት ያህል ሲወያዩበት ቆይተው ካሰቡበት ቀን ቀደም ብለው ሊጠቀሙበት አስበዋል።  [BBC Sport]

.

➣ አሌክሲስ ሳንቼዝ ማንቸስተር ዩናይትድን በመልቀቅ ወደ ፒ.ኤስ.ጂ መዛወር ይፈልጋል። ተጭዋቹ በደቡብ ምዕራቡ የእንግሊዝ ክለብ መላመድ የተሳነው ሲሆን ተጭዋቹ በካሪንግተን የልምምድ ማዕከል ላይ ደስተኛ አለመሆኑን በተደጋጋሚ የሚያሳያቸው በሃርያት ያመላክታሉ።  (Times)

.

➣ ፖል ፖግባ በበኩሉ ትላንትና በካሪንግተን የተደረገው ልምምድ ላይ አልተካፈለም። ተጭዋቹ ለብቻው በቤት ውስጥ ቀለል ያለ ልምምድ ያደረገ ሲሆን መጠነኛ የሆነ ጉዳት አስተናግዷል። እሁድ ለሚደረገው የደርቢው ጨዋታ መሰለፉም ያጠራጥራል።   (Mail)

.

➣ ፒር ኤምሬክ ኦበምያንግ ከ2015 ማርች ወር ኦሊቨር ዥሩድ ከተመረጠ በኃላ የወሩ የፕሪሚየር ሊጉ ኮከብ ተጭዋች በሚል ሲመረጥ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጭዋች ነው። ሌላኛው የቡድን አጋሩ አሮን ራምሴይ ደግሞ ፉልሃም ላይ ያገባት ጎል የወሩ ምርጥ ጎል ተብላ ተመርጣለታለች።

➣ በአርሰናል ክለብ በቅርብ አመታት የወሩ ምርጥ የሊጉ ተጭዋች በመባል የተመረጡ ተጭዋቾች ..

• October 2018: Pierre-Emerick Aubameyang
• March 2015: Olivier Giroud
• September 2013: Aaron Ramsey
• October 2011: Robin Van Persie
• December 2010: Samir Nasri
• October 2009: Robin Van Persie

.

➣ ፔፕ ጋርዲዮላ ከጆዜ ሞሪንዎ ጋር ስላለው ባላንጣነት:

"አሁን ባላንጣነታችን ተሻሽሏል። ሆኖም ልክ ከጫወታው መጠናቀቅ በኃላ ሁለታችንም መልካም ሰዎች እንሆናለን። እናንተ ከምታስቡት በላይ እኛ እንግባባለን"

.

➣ ኬርሎ አንቼሎቲ ጆዜ ሞሪንዎ በጁቬንቱሱ የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ፍፃሜ ላይ ስላደረጉት ነገር በጋዜጠኞች ሲጠየቁ እሳቸውም ጆሮአቸውን በመያዝ እንዲህ ሲሉ መልሰዋል:

“Sorry I didn’t hear you ይቅርታ አልሰማዋችሁም” -  ሁሉም ጋዜጠኞች ሳቁ።

.

➣ ሲሞን ሚኞሌት በቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ፓትሪስ ቪየራ ሁለተኛ እድል ሊሰጠው ይችላል። ተጭዋቹ በሊቨርፑል ፍፁም ደስተኛ ያልሆነ ሲሆን። አኒንሱ አለቃ የቀድሞው መድፈኛ ክለብ ኒስ ለዝውውር ተፈልጓል። ኒንስ በሊግ ዋን ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።    (mirror)

.

➣ ጄሚ ካራገር እንደሚያምነው ከሆነ ራሂም ስተርሊንግ ሊቨርፑልን በመልቀቅ ወደ ማንቸስተር ሲቲ ለመዛወር ያሳለፈው ውሳኔ ድንቅ ነው። "የለቀቀው በእግርኳሳዊ ምክንያቶች ነው። በወቅቱ ሊቨርፑሎች ጥሩ ቁመና ላይ አልነበሩም። በተቅቃራኒው ሲቲዎች እየሄዱበት ያለው አቅጣጫ ግን ጥሩ ነበር"    (liverpoolecho)

.

➣ ዤርዳን ሻቂሪ እንደ ሊቨርፑል ተጭዋችነት በክለቡ በፍጥነት መልመዱን እንደወደደው በይፋ ተናግሯል። "እኔ እዚህ በመሆኔ እጅግ በጣም ደስተኛ ነኝ። በጣም በፍጥነት ክለቡን መላመድ ችያለሁ። ሆኖም ከዚህም በላይ ገና በደንብ መሻሻል እችላለሁ። አሁን ባለሁበት ሁኔታ ግን ደስተኛ ነኝ"  (liverpoolfc)

.

➣ የሌስተር ሲቲ እግርኳስ ክለብ ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ በክለቡ ኪንግ ፓወር ስታዲየም የውጪኛው ክፍል ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸውን ላጡት የክለቡ ባለቤት Vichai Srivaddhanaprabha መታሰቢያ የሚሆን ሃውልት እንደሚገነቡ አሳውቀዋል።

.

➣ ቦሩሲያ ዶርትመንዶች ግብ ጠባቂያቸው ሮማን ቡርኪ ትላንትና ልምምድ ላይ ሳይካፈል ቀርቷል። መጠነኛ የጡንቻ ህመም የገጠመው ሲሆን ዛሬ ከባየር ሙኒክ ጋር በሚደረገው ተጠባቂ ጨዋታ ላይ ላይሰለፍ ይችላል።   (Bild)

.

➣ አምስት ተጨማሪ አመታት! ራሂም ስተርሊንግ በማንቸስተር ሲቲ እስከ 2023 የውድድር አመት ድረስ የሚያቆየውን አዲስ ኮንትራት ተፈራረመ።

➣ ራሂም ስተርሊንግ ፊርማውን ካኖረ በኃላ: “ውሌን በማራዘሜ ተደስቻለሁ። እዚህ ከመጣው ጀምሮ ያሳየውት እድገት የማይታመን ነው። ኢትሃድ ከደረስኩ ጊዜ ጀምሮ ትክክለኛ ምርጫ እንዳደረኩ ይሰማኛል። እጅግ በጣም ተደስቻለሁ።"

➣ ራሂም ስተርሊንግ ለማንቸስተር ሲቲ ከፈረመ በኃላ:
• በ2015/16 Played: 47 Goals: 11 Assists: 10
• በ2016/17 Played: 46 Goals: 10 Assists: 19
• በ2017/18 Played: 46 Goals: 23 Assists: 17
• በ2018/19 Played: 14 Goals: 7 Assists: 7
ባጠቃላይ ተጫወተ: 153 | አገባ 51 | ለጎል አቀበለ 53

.

➣ ሲቪያዎች የሊቨርፑሉን ግራ ተመላላሽ ተከላካይ አልቤርቶ ሞሬኖን ማዛወር ይፈልጋሉ። ተጭዋቹ በቀያዮቹ ቤት ያለው ኮንትራት በአመቱ መጨረሻ ላይ ኮንትራቱ ያበቃል።  (FTransferNews)

.

➣ ማውሪዚዮ ሳሪ ሮዝ ባርክሌይ በቼልሲ የነበረውን የእግርኳስ ህይወቱ በአዲስ መልክ እንዲያንሰራራ ማድረጉን አድንቀዋል። አሰልጣኙ ባርክሌይን ከሩበን ሉፍተስ ቼክ ይበልጥ ታክቲካዊ ጉዳዮችን መረዳትም ይችላል ብለዋል።  (AdamCrafton)

.

➣ አርሰናሎች ዳኒ ዌልቤክ ከስፖርቲንግ ሊዝበን በነበራቸው የዩሮፓ ሊግ ጨዋታ ላይ የደረሰበት የቁርችምጭሚት ጉዳት አጥንት ስብራት ከባድ በመሆኑ ሲዝኑን ሙሉ በጉዳት ከሜዳ ሊያርቀው ይችላል የሚል ስጋት አድሮባቸዋል። ሆኖም የጉዳቱ ጥልቀት እና መዳኛ የግዜ ገደብ እስካሁን ጥርት ያለ መረጃ አልወጣለትም።    (SamiMokbel81_DM)

.

➣ ቶርጋን ሃዛርድ እንዳለው ከሆነ በእርሱ እና በቼልሲው ኮከብ ወንድሙ ኤዲን ሃዛርድ መሃከል በያመቱ በየክለቦቻቸው 'እኔ ከፍተኛ ጎል በሲዝኑ አስቆጥራለሁ' የሙል የቤተሰባዊ ውርርድ እንደሚያደርጉ ተናግሯል። ሦስተኛው ወንድማቸውም ካይላን ይሄንኑ ፉክክር በቅርቡ እንደሚቀላቀል ተስፋ አለኝም ብሏል። "በእኔ እና በሃዛርድ መሃከል በየአመቱ ተመሳሳይ ፉክክር በመሃላችን አለ"   (dailymail)

Friday, November 9, 2018

ውለታ መላሹ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ (በመንሱር አብዱልቀኒ)



…የትልቁ ስፖርቲንግ ሊዝበን መልማዮች እንደሚመጡ ሲሰማ ለምልመላ የተዘጋጁት ታዳጊዎች ጓጉተው ጠበቁ። የልጅነት ህልማቸው እውን እንዲሆን አጋጣሚው ከእንቁ በላይ ውድ ነበር። ክሪስቲያኖ ሮናልዶ የተባለው ታዳጊም በቡድኑ ውስጥ እንዳለው እኩያው አልበርት ፋንትሮ ሁሉ ምኞቱ ከዚህ የተለየ አልነበረም።

መልማዮቹ እንደመጡ ታዳጊው ሁሉ ራሱን ለገበያ ሊያቀርብ ያቺን ቀን ያለ የሌለ ብቃቱን ሁሉ አውጥቶ ሊያሳይ ቆረጠ።

መልማዮቹ ማን የስፖርቲንግ ሊዝበንን አካዳሚ ነጻ የስልጠና ዕድል እንደሚያገኝ ለታዳጊዎቹ ማስገንዘቢያ ተናገሩ።

"የበለጠ ጎሎችን ያስቆጠረ ይመለመላል" ተባለ።

በጨዋታው ክሪስቲያኖ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጠረ። አልበርት በአስደናቂ ቴስታ ሁለተኛውን ጎል በስሙ አስመዘገበ።

ውጤት 2ለ0 ሆኖ ጨዋታው ቀጠለ።

ሶስተኛዋ ጎል ግን ተመልካቹን ሁሉ ያነጋገረች ሆነች። ከሁለቱ ተጫዋቾች አንድ ጎል የጨመረ በጨዋታው የሚፈለገውን የጎል የበላይነት ይይዛል። ፉክክሩ ልብ አንጠልጣይ በሆነበት ሰዓት አልበርት ከግብ ጠባቂው ጋር አንድ-ለ-አንድ ተገናኘ። ራሱ ጎሉን ማስቆጠርና ስኮላርሺፑን ለራሱ ማድረግ  ይችላል። ከበረኛው ፊት ሲደርስ ግን ዕድሉን አሳልፎ ሰጠ።

ራሱን ነፃ አድርጎ ወደ ጎል ለተጠጋው ክሪስቲያኖ አመቻችቶ አቀበለው። ሮናልዶም ከመረቡ ውስጥ ዶላት።

ጨዋታው 3ለ0 ሲያበቃ፣ ክሪስቲያኖ ለስፖርቲንግ አካዳሚ ስኮላርሺፕ ታጨ።

ከጨዋታው በኋላ ሮናልዶ ወደ አልበርት ሄዶ ጠየቀው።

"ከቶ እንዴት ዕድሉን አሳልፈህ ሰጠኸኝ?"

የአልበርት ምላሽ አጭርና ግልፅ ነበር።

"ምክንያቱም አንተ ከእኔ የበለጠ ተሰጥኦ ስላለህ፣ ዕድሉ ላንተ ስለሚገባ ነው" አለው።

ፈፅሞ የማይታመን ነበር። ከዓመታት በኋላ ሮናልዶ ይህን ታሪክ ሲናገር የሰማ ጋዜጠኛ የተባለው እውነት ለመሆኑ ማስረጃ ፍለጋ ወደ አልበርት ፋንትሮ ቤት ሄደ።

የጎለመሰው አልበርት ፕሮፌሽናል ተጫዋች አልሆነም። ይባስ ብሎ ከዚያ ጨዋታ በኋላ የእግር ኳስ ተጫዋችነት ህይወቱ እንዳበቃ ለጋዜጠኛው ነገረው። አሁን የረባ ስራ እንኳን እንደሌለውም አስረግጦ አጫወተው።

ጋዜጠኛው ግራ ገባው።

"እንዴ?… የረባ ስራ እንኳን የለህም። ግን ይህን በሚያክል የተንጣለለ ቪላ ውስጥ ትኖራለህ። የበርካታ መኪኖች ባለቤት ነህ። በተጨማሪ ቤተሰብህን አንደላቀህ ታኖራለህ። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ሃብቱ ከየት መጣ?"

አልበርት ለመልሱ አልተቸገረም።

"ይህን ሁሉ ያደረገልኝ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ነው።"

አርብ ምሽት የወጡ የዝውውር እና ሌሎችም በርካታ ዜናዎች



አሌክሲስ ሳንቼዝ በጁቬንቱሱ ጨዋታ ላይ መጠነኛ ጉዳት አስተናግዷል። በማንቸስተር ደርቢ ጨዋታ ላይ ላይሰለፍ ይችላል።   [Mail]

.

ቼልሲዎች በቀጣዩ ክረምት የዝውውር መስኮት ላይ ኤዲን ሃዛርድ ክለቡን በመልቀቅ ወደ ሪያል ማድሪድ የሚዛወር ከሆነ በምትኩ የሊዮኑን የፊት መስመር ተሰላፊ ናቢ ፊከርን በማስፈረም ሊተኩት አቅደዋል። ተጭዋቹ በበኩሉ ክለቡ እንዲለቀው በግልፅ ጠይቋል።   (Source: Daily Star)

.

አትሌቲኮ ቢልባዎዎች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ የቶተንሃሙን ስፔናዊ አጥቂ ፈርናንዶ ሎረንቴ ለማዛወር ጥያቄ ያቀርባሉ።  (Source: Independent)

.

አንቶኒ ማርሻል በማንቸስተር ዩናይትድ የሚያቆየውን አዲስ የአምስት አመት ኮንትራት ለመፈራረም ተቃርቧል።   [Mail]

.

ሮሚዮ ሉካኩ የፊታችን እሁድ ከሚደረገው የማንቸስተር ደርቢ ጨዋታ ላይ ወደ ሜዳ ሊመለስ ይችላል። ተጭዋቹ ቀለል ያለ ልምምድ መስራት ጀምሯል።   [Mail]

.

ዩሃን ማታ አሁንም ከማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ ኮንትራት ይቀርብልኛል ብሎ ያስባል። ተጭዋቹ በኦልትራፎርድ የሚያቆይ ቀሪ የስምንት ወር ኮንትራት ብቻ ይቀረዋል።   [Mail]

.

ኡናይ ኤምሬ ስለ ዳኒ ዌልቤክ ጉዳት ፦

"ይሄ በጣም መጥፎው ዜና ነው። ጉዳቱ ከባድ እንደሆነ ሰምቻለው። ሁሉም ጉዳት አንድ አይነት አይደለም ይለያያሉ። ቁርጭምጭሚቱ ላይ የሆነ አጥንት ሳይሰበር አልቀረም። ከሌሎች ጉዳቶች ይለያል ከባድ ነው። ጉዳቱ ሜዳ ላይ የነበሩ ሌሎች ተጭዋቾችን ሳይቀር መትፎ ተፅህኖ ፈጥፎባቸዋል"

.

ናቢ ኪየታ፣ ጆርዳን ሄንደርሰን እና ጆ ጎሜዝ ከደረሰባቸው ጉዳት ሙሉ ለሙሉ በማገገማቸው በፉልሃሙ ጨዋታ ላይ ወደ ሜዳ ለመመለስ ብቁ ናቸው።

.

ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ቶተንሃሞች የሮማውን የክንፍ መስመር ተጫዋች ለማስፈረም ከክለቡ ጋር ድርድር ማድረግ ጀምረዋል። ለተጭዋቹ ዝውውር በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ለጣሊያኑ ክለብ ሊያቀርቡ ያሰቡት ሂሳብ የክለቡ ሪከርድ የሆነ €60 ሚሊዮን ነው።  [TEAMtalk via RAI Sports]

.

ጁቬንቱሶች አንቶኒ ማርሻልን ከማንቸስተር ዩናይትድ ለማዛወር የነበራቸው እቅድ ላይ ተስፋ ቆርጠዋል። በዚህ ምክንያት ትኩረታቸውን በቦሩሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ጃዶ ሳንቾ አዙረዋል።   (Source: Daily Express)

.

የበርንማውዙ አጥቂ ካሉም ዊልሰን በ£35m የዝውውር ዋጋ የቼልሲ የዝውውር ኢላማ ሆኑአል። የ26 አመቱ አጥቂ ትላንትና ለመጀመሪያ ግዜ ወደ እንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ተጠርቷል።   (Source: Sun Sport)

.

ባየር ሙኒክ፣ ቦሩሲያ ዶርትመንድ እና አርሰናሎች የሊሉን የክንፍ መስመር የ23 አመቱን ተጫዋች ኒኮላስ ፔፔ ለማዛወር የ €50 ሚሊዮን ዩሮ ሂሳብ ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል። 8 አስቆጠረ 7 ለጎል አቀበለ in 13 ተጫወተ። (telefoot_TF1)

.

አንቶኔ ማርሻል ወደ ፈረንሳይ ብሄራቡ ቡድን በድጋሚ ተጠርቷል።   (l’equipe)

.

አርሰናሎች የጁቬንቱሱን መሃል ተከላካይ መሃዲ ቤናሺያን ለማዛወር በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ጥያቄአቸው ያቀርባሉ። መድፈኞቹ እንደሚያምኑት ከሆነ የጁሼንቱሱ መሃል ተከላካይ በቱሪን ህይወቱ ደስተኛ አይደለም።   (Source: Daily Star)

.

ኦዚል ስለ ኡናይ ኢምሬ: “አሁን በጥሩ መንገድ ላይ ነን። በዚሁ ሁኔታ መቀጠል እንፈልጋለን። በጣም ጥሩ አሰልጣኝ ነው። ተጭዋቾችን መረዳት ይፈልጋል ሁሌም ከጎናችን ይሆናል። ክለቡን በደንብ ተረድቶታል። ሜዳ ላይ ሁላችንም ያለንን ልናሳየው የምንጓጓለት አይነት አሰልጣኝ ነው"

.

ሙስታፊ ስለ ቶሬራ: “ለስኬቱ ደስተኛ ነኝ። የቀድሞ ክለቤ በሆነው ሳምፕዶሪያ ተጫውቷል። እንደዚህ በቀላሉ የሚለመድ ሊግ አይደለም። በእንግሊዝ እና በጣሊያን ያለው ፈፅሞ ይለያል። እኔ በደንብ እረዳለሁ ምክንያቱም በተለያዩ ሃገራት ሊጎች ተጫውቼ አሳልፌአለው። እንደርሱ በፍጥነት መላመድ ከባድ ቢሆንም እርሱ ግን በሚገባ ተላምዶ ጥሩ ነገር እያሳየን ነው።"

.

ሳሙኤል ኤቶ ተስፋ በቆረጠ ሰአት ለሊቨርፑሉ ኮከብ ሙሃመድ ሳላህ የእግርኳስ ህይወቱን የቀየረለትን ምክር ሰትቶት እንደነበር ተናግሯል።

"ነገሮች ባሰበው መልኩ ባለመሄዳቸው ተስፋ ቆርጦ ነበር እንዲታገስ መከርኩት። 'አንተ በጣም ጥሩ ተጭዋች ነህ ወደፊት ታላቅ ተጭዋችም ትሆናለህ' ስል ምክሬን ለግሼዋለሁ"

"ሁሉም ነገር የሚወሰነው በራሱ በሳላህ ነው። የማይታመኑ ክህሎቶች አሉት። እናም አሁን በትልቅ ደረጃ እየተጫወተ ይገኛል። የባለን ደ ኦር እጩም መሆን ችሏል"

.

ጆርዳን ሄንደርሰን፣ ትረንት አሌክሳንደር አርኖልድ እና ጆ ጎሜዝ በእንግሊዝ በሄራዊ ቡድን አለቃ ጋሬዝ ሳውዝጌት ቡድኑን እንዲቀላቀሉት ጥሪ ደርሷቸዋል።

.

ማትስ ሁምለስ: "ይሄኛው የቦሩሲያ ዶርትመንድ ቡድን በየርገን ክሎፕ ዘመን የነበረውን ድንቅ ቡድን ያስታውሰኛል"  (Bild)

.

ፑማ ተጨማሪ የማንቸስተር ሲቲ ተጭዋቾችን ስፖንሰር ለማድረግ እየጣረ ነው። ሎሪ ሳኔ፣ ቪሰንት ኮምፓኒ እና ራሂም ስተርሊንግ በራዳራቸው ውስጥ ገብተዋል። ከሲቲ ጋር ፑማዎች አመታዊ የ£50m ክፍያ ስፖንሰርሺፕ ተፈራርመዋል። ዴቪድ ሲልቫና ሰርጂዎ አጉዌሮም ቀደም ብለው ለፑማ ፊርማቸውን አኑረዋል።   (Daily Mail)

.

ፍሬድ ለFourFourTwo: "ሲቲዎች ጥያቄ አቅርበውልኝ እንደነበር ሚነገረው እውነት ነው። እናዛውርህ ብለውኝ ነበር። እንደውም በብሄራዊ ቡድን አጋሬ በኩል እንድቀላቀላቸው ሊያሳምኑኝ ሞክረው ነበር። ሆኖም በመጨረሻ ዝውውሩ ሊሳካ አልቻለም"

.

ዌስትሃም ዩናይትዶች የ31 አመቱን የቀድሞ የማንቸስተር ሲቲ አማካይ ሳሚር ናስሪ ለማዛወር እያጤኑበት ነው። የቀድሞው የፈረንሳይ ኮከብ በእፅ መውሰድ ክስ ከተጣለበት የ18 ወራት የጨዋታ ቅጣት በቅርብ ወደ ሜዳ ይመለሳል።  (Mirror)

.

ማንቸስተር ሲቲዎች ታዳጊውን ፈርናንዶ ኦቬላርን ለማዛወር እየተከታተሉት ይገኛሉ። ኦቨራባለፈው ሳምንት በፓራጓዩ ሱፐርክላሲኮ ጩዋታ ላይ ጎል ማስቆጠር ችሏል - ምንም እንኳን ገና 14 አመቱ ቢሆንም።  (Mirror)

.

ማንቸተር ዩናይትዶች የሳምፕዶሪያውን የ22 አመት ዴንማርካዊ ተከላካይ ኮአኪም አንዴርሰንን የማዛወር ፍላጎት አላቸው።   (Source: La Republica)

.

ኒኮላስ ፔፔ ሊልን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆኑን ገለፀ። ይሄንን ተከትሎ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ወደ አርሰናል ሊዛወር ይችላል በሚል በስፋት እየተወራ ይገኛል።   (Source: Sun Sport)

.

ጃቪ ጋርሺያ የዋትፎርድ ዋና አለቃ በመሆን አዲስ የቀረበላቸውን የሦስት አመት ኮንትራት ለመፈራረም ተስማምተዋል።   (Source: SkySports)

.

ኤቨርተኖች እድሜአቸው ከ10-18 የሆኑ ታዳጊ ተጭዋቾችን ለሁለት አመታት እንዳያዛውሩ እገዳ ተጭሎባቸዋል። ይሄ የሆነው ታዳጊዎችን ገና የትምህርት ገበታቸው በማማለል ለማዛወር ሲያደርጉ የነበረው ጥረት ተደርሶበት ጥፋተኝነታቸው ተረጋግጦ ነው።   (Source: SkySports)

.

ቼልሲዎች እና ባየር ሙኒኮች የሊዮኑን አማካይ አጥቂ ናቢ ፊከር ለማዛወር በድጋሚ ተፋጠዋል። ተጭዋቹ በቀጣዩ ክረምት ላይ ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግ በግልፅ ነግሮአቸዋል።   (Source: L'Equipe)

.

የPSVው ኮከብ አጥቂ ሄርቪንግ ሎዛኖ አሁን ያለበትን የሆላንዱን ክለብ የሚለቅ ከሆነ ከማንቸስተር ዩናይትድ አሊያም ባርሴሎና አንዳቸውን ብቻ እንደሚቀላቀል ተናግሯል።  (Source: Sun Sport)





የሳዎ ፖሎውን የ24 አመት ኮከብ ዳንኤል ኮሪያን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ ወንጀሉን አመነ



Football Crime -  መርማሪዎች እንዳረጋገጡት ከሆነ ግድያ የተፈፀመበት እግር ኳስ ተጫዋች ዳንኤል ኮሪያ በወቅቱ 'በጣም ጠጥቶ' ስለነበር 'ሴት ለመድፈር የሚያበቃ አቅም አልነበረውም' ሲሉ መርማሪዎች ተናግረዋል

የሳዎ ፖሎው ኮከብ ኮሪያ በብራዚሏ Sao Jose dos Pinhais ከተማ ባሰቃቂ ሁኔታ ኦክቶበር 27 ተገሎ የተገኘ ሲሆን አንገቱ እና ብልቱ ተቆርጠው ነበር በድን እሬሳውን ፓሊስ ያገኘው።

የቢዝነስ ሰው ናቸው የሚባሉት የ38 አመቱ ኢድሰን ጁኒየር ከሦስት ቀናት በኃላ ተይዘው የታሰሩ ሲሆን የ24 አመቱን ኮከብ እግር ኳስ ተጭዋች እብደት ባለው በዛች ሌሊት ባለቤቴን ክርስቲና ብሪቴስ ለመድፈር ሙከራ ሲያደርግ በመድረሴ ገድዬዋለሁ ሲል አምኖአል።

ኮሪያ ከክርስቲና ጋር አልጋ ላይ እያለ የተነሳውን ፎቶ ለሳዎ ፖሎው የቡድን አጋሩ ልኮለት ነበር። ከዛም ወደ አንድ ፓርቲ ድግስ ቤት ናይት ክለብ ለመዝናናት በድጋሚ አምርቶ ነበር።

ክርስቲና እና ኢድሰንን የሚወክሉት የህግ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ "በተጭዋቹ ያለፍቃዷ በተኛችበት ወሲብ እንድትፈፅም ሞክሮአል። ወሲብ ሊያደርጋትም ታግሏል"

"ዳንኤላም በወቅቱ ጠጥታ ነበር። እንቅልፍ ላይም ነበረች። ሁኔታው ህልምም መስሏት ነበር። ስትነቃ እርሱ መሆኑን ተመለከተች ከዛም በጩሃት የድረሱልኝ ጥሪዋን አሰማች"

ሆኖም መርማሪ አማኤዱ ትሪቪዛን ይሄንን መላምት ተችተዋል እናም ያሉት መረጃዎች የተሰጠው መግለጫ ጋር አይጣጣሙም ብለዋል።

እንደተባለው ከሆነ በምርመራው ወቅት እንደተገኘው የtoxicology ውጤት ሪፖርት ከሆነ ኮሪያም ጠጥቶ ነበር እናም ክሪስቲናን ለመድፈር የሚያበቃ ተፈጥሮአዊ አቅሙን አጥቷል።

በMail ሪፖርት እንደተደረገው, ትሪቪዛን ሲያክሉ: "
"ከሰማናቸው የአይን እማኞች እና በወቅቱ በቤቱ ውስጥ ከነበሩ ሰዎች እንደተረዳነው ከሆነ ክሪስቲና እንደተባለው ጥቃት እየደረሰባት በመሆኑ ስትጮህ ማንም ሰው አልሰማም ጩሃትም አላሰማችም።

"ማንም ሰው ደግሞ የኤድሰንን በሩን በጉልበት ሰብሮ ሲገባ ድምፅም አልተሰማም። ትልቅ ቤት አልነበረም ክፍሉ አነስተኛ ቤት ነበር። ብዙ ሰዎችም በዙሪያው እዛው ነበሩ"

"እኛ እንደምናምነው ከሆነ ኤዲሰን ኤዲሰን ወንጀሉን ከመፈፀሙ በፊት ባካባቢ የነበሩ ሰዎች ዝም እንዲሉ አግባብቷቸዋል።

"ስለዚህ የክርስቲና ሰዎች እየዋሹ እንደሆነ እናስባለን። ሆን ብለውም የራሳቸውን ታሪክ እየፈጠሩ ነው። ውንጀላው ሃሰት መሆኑን ለማረጋገጥ የፈጠሩት የታሪክ ፍሰት ነው።" ብለዋል።

ኤዲሰን እንዳለው ከሆነ ክፍሉን ሰብሮ ለመግባት የተገደደው ከውስጥ ተቆልፎ ስለነበር ነው። ከውስጥ ደግሞ የክርስቲና የድረሱልኝ ድምፅ ከውጪ ሆኖ ሰምቶታል።

"ከዛም ከሚስቴ ሰውነት ላይ አነሳሁት እና ወደ ወለሉ ወረወርኩት። ያንን ወንከለኛ በቻልኩት ሁሉ ሚስቴን ከመድፈር አዳንኩአት። ያደረኩት ያንን ነው።"

"በጣም ደጋግሜ መትቼዋለሁ። ቀጥቅጬዋለሁ። ከዛም ከቤት ውጪ ይዤው ሄድኩ በህይወት ይኑር ወይ እራሱን ስቶ ይሆን የማውቀው ነገር አልነበረም። ግን አይኖቹን ከድኖ ነበር።

"በወቅቱ ምንም የማስበው ነገር አልነበረም። በመኪናዬ ውስጥ ቢላዋ ነበር። አነስ ያለ ስለታማ ቢላዋ። ከዛም ምን ማድረግ እንዳለብኝ አይምሮዬ ሹክ አለኝ። የሆነውን ሁሉ አደረኩ"

Thursday, November 8, 2018

ሃሙስ ምሽት የወጡ የዝውውር እና ሌሎችም ዜናዎች



PAUL POGBA MISSED MAN UNITED TEAM FLIGHT AFTER WIN OVER JUVENTUS

ፖል ፖግባ ከትላንት ምሽቱ የማን.ዩናይትድ ቻምፒየንስ ሊግ ጁቬንቱስ ድል በኃላ ወደ ማንቸስተር ከተማ በተመለሰው የተጭዋቾቹ በረራ ፕሌን ውስጥ አልነበረም ተባለ።

ፈረንሳዊው ኮከብ ወደ ማንችስተር የተመለሰው ከተጭዋቾቹ ጋር ሳይሆን ከክለቡ ዋና አስተዳዳሪ እና ከደጋፊዎች ጋር ዋናው ቡድን የያዘው ፕሌን ማንቸስተር ከገባ ከአንድ ሰአት በኃላ ነው።

ይሄ የሆነበት ምክንያት ቡድኑ ታሪካውን ድል በቱሪን ካስመዘገበ በኃላ የአደንዛዥ እፅ መርማሪ ቡድኖች ፖግባ ላይ የሽንት እና መሰል ሳምፕሎችን በመውሰድ ምርመራ ለማድረግ ጠርተውት ከበረራው ስላዘገዩት ነበር ተብሏል።   (ምንጭ፦ Mirror)

ARSENAL SCOUT BRAZILIAN STAR SIX TIMES

አርሰናሎች የጥር የዝውውር መስኮቱ ተከፍቶ ወደ ዝውውሩ እንቅስቃሴ ውስጥ ከመግባታቸው በፊት የብራዚላዊውን ኮከብ እንቅስቃሴ ለ6ተኛ ግዜ ገምግመዋል ተባለ።

የ18 አመቱ ታዳጊ ተጭዋች ሙሉ ስም Eric dos Santos Rodrigues (በቅፅል ስሙ ራሚሬዝ ይሉታል) የሚባል የአማካይ ስፍራ ተጭዋች ሲሆን ለብራዚሉ ባሂአ የተሰኘ ክለብ በመጫወት ላይ ይገኛል። በአትሌቲኮ ማድሪድም ይፈለጋል።

ገና በለጋ እድሜው በብራዚሉ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ላይ በ9 ጨዋታዎች ላይ መሰለፍ ችሏል። ከደቡብ አሜሪ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ከሆነ ተጭዋቹ በጥር ላይ ወደ አርሰናል ሊያመራ ይችላል።
ክለቡ ባሂያ መጪው የብራዚል ባለተሰጥዎ ኮከብ እየተባለ የሚወደሰውን ኮከብ ለሃገር ውስጥ ክለቦች አሳልፈው ከመሸጥ ይልቅ ወደ አውሮፓ ትልልቅ ክለቦች ለመሸጥ ምርጫቸውን ማድረጋቸው ራሚሬዝ ቀጣይ ማረፊያው የለንደኑ ክለብ ነው እንዲባል አሰኝቷል።  (ምንጭ፦ The Sun)

PETER CROUCH CAR WAS STOLEN FOR SEX CAUSE

የዝነኛው እንግሊዛዊ አጥቂ ፒተር ክራውች ውድ መኪና በአንድ ሌባ ከተሰረቀች በኃላ - ዘራፊው የኃላውን መቀመጫ ቦታ ስፍራ ላይ ወሲብ እንደፈፀመበት ተጭዋቹ ተናገረ።

የቀድሞው የእንግሊዝ እና የሊቨርፑሉ አጥቂ በታዋቂው የBBC Podcast ሾው ፕሮግራም ላይ አንድ ደጋፊ በስልክ ደውሎ ከጠየቀው በኃላ ነው ጉዳዩን በቀጥታ ይፋ ያደረገው።

አድማጩ ጄይ የሚባል ሲሆን በቀጥታ የሬዲዮ ፕሮግራሙ ላይ ከደወለ በኃላ የተጭዋቹ መኪና ጠፍታ በነበረችበት ወቅት ከኃላ ወንበር መቀመጫ ስፍራው ላይ መኪናዋን ወደ ደቡብ ለንደን በመውሰድ ምን ያህል ጣፋጭ ጊዜ እንዳሳለፈበት ራሱ ነበር የተናገረው።

ክስተቱ የደረሰበት የአሁኑ የስቶክ ሲቲ ተጭዋች የሆነውን ከሰማ በኃላ በመገረም ስሜት ውስጥ ሆኖ ማመን እንዳልቻለ ገልፆአል።

"የሆነ ሰው መኪናዬን ከሰረቀ በኃላ የራሱን ሙዚቃ በመክፈት እና እዛው ፍቅረኛውን በመቅጠር ተዳርቶባታል።"

ሲል ሁኔታውን እያስታወሰ ተናግሯል ..
"የራሱን ሙዚቃ ማጫወቻ CD እንኳን እዛው ትቶት ነበር። ድምፁን ጨምሮ ቆንጆ ሙዚቃውን እንደከፈተ" መኪናዋን ትቷት ሄዷል" ሲል ሁኔታውን አብራርቷል።
(ምንጭ፦ BBC Podcast)

FA IS HAPPY WITH THEIR DECISION

የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳዳሪ ሰዎች አንቶኒ ቴይለር የመጀመሪያውን የማንቸስተር ደርቢ ጨዋታ እንዲዳኝ የወሰኑነት ውሳኔ ላይ ደስተኞች ናቸው።

አንዳንድ የሲቲ ደጋፊዎች ግን ግለሰቡ የተወለዱት ከኦልትራፎርድ ስቴዲየም ስድስት ማይልስ ብቻ ርቀት ላይ በምትገኘው የWythenshawe ስፍራ በመሆኑ ታይለር ለማን.ዩናይትድ እንዳያደሉ በሚል ስጋት ስለገባቸው የመሃል ዳኛውን መመደብ ከሰሙ በኃላ ተቃውሞአቸውን እያሰሙ ቢገኙም FAው ግን ውሳኔአችን ትክክለኛ እና ተገቢ ስለሆነ ምደባውን አንቀይርም የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።
(ምንጭ፦ Sky Sports News)

ሃሙስ ምሽት የወጡ ከ20 በላይ የዝውውር እና ሌሎችም ዜናዎች

ማንችስተር ዩናይትዶች ለአንቶኒ ማርሻል የጠየቀውን ሳምንታዊ የ£190,000 ደሞዝ የሚያገኝበትን ኮንትራት ቦነሱንም ጨምሮ ሊሰጡት ተዘጋጅተዋል።
(Source: Sun Sport)

.

ሪያል ማድሪዶች ኬይላን ምባፔን በ2017 ላይ በ€214m የዝውውር ሂሳብ ሊያስፈርሙት ከክለቡ ሞናኮ ጋር ከስምምነት ደርሰው ነበር። ሆኖም ተጭዋቹ በፓሪስ በመወለዱ ምክንያት ለፒ.ኤስ.ጂ መፈረምን መርጦ ወደዛው ተዛውሯል።   (Source: L'Equipe)

.

ሊዮን ቤይሊ በክረምቱ ከማንቸስተር ሲቲ እና ማንቸስተር ዩናይትዶች ቀርቦለት የነበረውን የእናዛውርህ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ በባየር ሌቨርኩሰን መቆየቱን ተናገረ።   (Source: MEN)

ሊዮን ቤይሊ ለFourFourTwo: "ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ማን.ሲቲ፣ ቼልሲ፣ ሊቨርፑል ሁሉም ትልልቅ ክለቦች ናቸው። ሁሉም ሊወስዱኝ ፈልገው ነበር። ሆኖም ወሳኙ ነገር አሁን መማር ባለብኝ ቦታ እና ስፍራ መቆየቴ ለኔ ጠቃሚ ውሳኔ ነው። በፍትነት ትልቅ ክለብ መቀየር ለእድገቴም መልካም አይደለም። ምክንያቱም ገና ካሁኑ ትልቅ ክለብ ከገባህ በቀጣይስ ለማደግ ወደየትኛው ክለብ ለመዛወር ትጥራለህ?"

.

ጆዜ ሞሪንዎ ስለ ጁቬንቱስ ደጋፊዎች: “እኔ እነሱን አላንቋሸሽኩም። ያደረኩት ትንሽ ነገር ነው። ተጭዋቾቻቸውን አከብራለሁ ሁሉንም አከብራለሁ። በልጆቼ እጅጉን በጣም ኮርቻለሁ"   [BT]

"እኔኮ ለ90 ደቂቃ ያህል በደጋፊው ስብጠለጠል ነበር። የኔን ቤተሰቦች ሲያንኬስሱ ነበር። እዚህ የመጣሁት ስራዬን ለመስራት ነው እንጂ ለስድድብ አይደለም። በመጨረሻው ደቂቃ ማንንም አልተተናኮልኩም። ድምፃቸውን ከፍ እንዲያደርጉ ጆሮዬን ይዤ ጠይቄያቸዋለሁ። ምናልባት ይህን ማድረግ ላይኖርብኝ ይችላል። ወይም ያደረኩበት መንገድ መጥፎ ሊሆን ይችላል"  [Sky Italia]

.

ጋሬዝ ቤል በክረምቱ ማንቸስተር ዩናይትድን ሊቀላቀሉ ይችላሉ ከተባሉት ተጭዋቾች መሃከል በክለቡ ቀዳሚው የግዢ እቅድ ውስጥ ተይዟል። ዩናይትዶች ተጭዋቹን በቅናሽ ዋጋ እንደሚያዛውሩት ተስፋ አድርገዋል።   (Don Balon)

.

ሽኮድራን ሙስታፊ ስለ ኡናይ ኤምሬ ተፅህኖ: “ለኔ በግሌ እርሱ ማለት ከእያንዳንዱ ተጭዋች ምን እንደሚጠብቅ ጠንቅቆ የሚያውቅ ድንቅ አሰልጣኝ ነው። ማድረግ ያለብህን በግልፅ ይነግርሃል። በተመሳሳይ መልኩም ሜዳ ውስጥ ነፃነቱን ይሰጥሃል"

.

አርሰናሎች የ18 አመቱን የባሂያ አማካይ ራሚሬዝን ለማዛወር ፍላጎት አሳድረዋል። ክለቡ ተጭዋቹን በመከታተል ላይ ይገኛል። በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በይፋ ጥያቄያቸውን ለክለቡ ለማቅረብም ዝግጁ ናቸው። [Football_LDN]

ባሂያ በሃገራቸው ብራዚል ሊግ ክለቦች የሚመጣላቸውን የእናዛውረው ጥያቄ በሙሉ ውድቅ ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ከወደ አውሮፓ ክለቦች የሚቀርብላቸው ጥያቄ ካለ ግን ሊያጤኑት ዝግጁ ናቸው። አርሰናሎችም የታዳጊው ብራዚላዊ ባለተሰጥዎ ማረፊያ ይሆናሉ በሚል የተሻለ እድል አግኝተዋል።  [Football_LDN]

.

ሊቨርፑሎች ታዳጊውን የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች ቪክቶር ክርስቶፈር ዲ ባውንበርግ ዝውውር ጋር ስማቸው ተያይዟል። የጭዋቹ የዋናውን የሪያል ማዮርካ ቡድን ሰብሮ ለመግባት እንደቻለ ተነግሮለታል። ሺክቶር በማዮርካ ታዳጊ ማዕከል ለ3ት አመታት ተጫውቷአል። በየአመቱም የቡድኑ ኮከብ ጎል አግቢ መሆን ችሏል።
(liverpoolecho)

.

አንዲ ሮበርትስ እንደሚያምነው ከሆነ ሊቨርፑሎች በፓሪሰን ዥርሜይን ጋር የሚያደርጉትን የቻምፒየንስ ሊጉን ጨዋታ የማሸነፍ እድል አላቸው። ወደ ቀጣዩ ዙርም እንደሚያልፉ ይተማመናል።

"እያንዳንዱን ጨዋታ እንደምናሸንፍ እናምናለን። እንደዛ ስለምናምንም ነው ለዚህ ውጤታማ ቡድን የበቃነው" -  (skysports)

"እንደ ቡድን መጫወት ይኖርብናል። ተቃራ ቡድን ፋታ በመንሳት ማጥቃት ይገባናል። ቀደም ብለን ጎሎችን በማስቆጠር ጨዋታን አስቀድሞ መግደል እና በራስ መተማመን ማሸነፍ ይኖርብናል"

.

ራሂም ስተርሊንግ ስለ ፔናሊቲው ክስተት: "የፈለኩት ኳሷን ቺፕ ማድረግ ነበር። ምን እንደተፈጠረ አላስታውስም። ተጭዋቹ የነካኝም አይመስለኝም። ዳኛውን መልሼ ይቅርታ ጠይቄዋለሁ"

.

አንቶኔ ጋሬዝማን ለKicker ጋዜጣ: "ለኔ ማንቸስተር ሲቲዎች የቻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ የማንሳት የተሻለ እድል አላቸው። ምክንያቱም እነርሱ ፔፕ ጋርዲዮላን ይዘዋል"

.

ሚሼል ባላክ እንደሚያምነው ከሆነ የቀድሞ ክለቡ ቼልሲዎች በዘንድሮው የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ ላይ የማንቸተር ሲቲ እና ሊቨርፑል ተፎካካሪዎች እንደሆኑ ያምናል።  ቡድኑ በሞሪዚዮ ሳሪ ስል እንደተሻሻለ ያስባል።  (90min)

.

አንቶኒዮ ኮንቴ ቼልሲዎች ስላባረሩአቸው በካሳ መልክ የ£8.7m ክፍያ እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል። እንዲሁም ሰውየው ኮንትራታቸውን ሳያጠናቅቁ ለተሰናበቱበት የአመቱን ሙሉ ክፍያ ሂሳብ £11m ጨምረው እንዲከፍሏቸው ጠይቀዋል።   (90min)

.

አልቫሮ ሞራታ በባለፈው የውድድር አመት ላይ ላሳየው መጥፎበቋም ደጋፊዎቹን ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን አሁን ግን በቼልሲና ለንደን ፍፁም ደስተኛ በመሆኔ ወደ ቀድሞ አቋሜ እመለሳለሁ ብሏል።
(90min)

.

የLA Galaxyው አጥቂ ዝላታን ኢቭራሞቪች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ወደ አውሮፓ ክለቦች ይዛወራል የሚለውን ዘገባ አጣጥሎታል።
(Source: SkySports)

.

ጁቬንቱሶች ተከላካያቸውን መሃዲ ቤናሺያን በመሸጥ በሚያገኙት ገንዘብ ላይ ጨምረው በ €60m ከፍተኛ ግምት የተሰጠውን የአያክስ መሃል ተከላካይ ማቲያስ ዲ ሊጅትን ማስፈረም ይፈልጋሉ።
(Source: Tuttosport)

.

ጁቬንቱሶች ፖል ፓግባን ስለሚያዛውሩበት ሁኔታ ከወኪሉ ሚኖ ራዮላ ጋር በተደጋጋሚ ግዜ ንግግር እያደረጉ እንደሚገኝ ተገለፀ። ፈረንሳዊውን ኢንተርናሽናል ወደ ቱሪን የመመለስ ከፍተኛ ፍላጎት አላቸው።  (Source: Tuttosport)

Wednesday, November 7, 2018

እረቡ ምሽት የወጡ የዝውውር እና ሌሎች ዜናዎች - Latest News Update



KYLIAN MBAPPE'S በፒ.ኤስ.ጂ ክለብ ለመቆየት የጠየቀው አስገራሚ ደሞዝና ጥቅማ ጥቅም ይፋ ሆነ። ተጭዋቹ የBallon d'Or ሽልማትን የሚያሸንፍ ከሆነ ከኔይማር ደሞዝ በላይ እንዲከፈለው ይፈልጋል።

ታዳጊው ባለተሰጥዎ ሞናኮን በመልቀቅ የፈረንሳዩን ሃብታም ክለብ ፒ.ኤስ.ጂን ባለፈው አመት በውሰት ከተቀላቀለ በኃላ በክረምቱ በቄሚ ዝውውር ለክለቡ ፊርማውን አኑሮአል።

እናም በፒ.ኤስ.ጂ የሚያቆየውን ውል ለመፈራረም የ19 አመቱ ኮከብ በአምስት አመታት የክለቡ ቆይታው አመታዊ የ£48 million ደሞዝ ከግብር በኃላ እንዲሰጠው ጠይቋል።

እንደ Football Leaks, ዘገባ ከሆነ የቀድሞው የሞናኮ ኮከብ ምባፔ በመላው አለም ያለ ደጋፊዎች ግርግርና ምንም መጨናነቅ፣ መጉላላት ሳይደርስበት ከደጋፊዎች ትኩረት በማምለጥ ከአንድ ሃገር ወደ ሌላ ሃገር እንደልቡ የሚጓዝበትን የግል ጀት ክለቡ እንዲመድብለትም ጠይቋል።

ሆኖም PSGዎች ይሄንን ሁሉ ጥያቄዎቹን ውድቅ በማድረግ ለተጭዋቹ የተለያዩ ወጪዎች መሸፈኛ ይሆን ዘንድ በወር £27,000 ቦነስ ክፍያ በመስጠት፣ ተንከባካቢ፣ ሹፌር እና ቦዲጋርድ መድበውለታል።

እንደ ሪፖርቱ ከሆነ ታዳጊው የባለንደኦር ሽልማትን የሚያነሳና የአለማችን ምርጡ የሚባል ከሆነ ከኔይማው ደሞዝ ሳምንታዊ £600,000 በላይ ደሞዝ እንዲከፈለው ጠይቆ ተስማምቷል።

________________________________________
●  ማንቸስተር ዩናይትዶች ጋሬዝ ቤልን ከሪያል ማድሪድ ለማዛወር የ£100 million ክፍያ ለማቅረብ አስበዋል። ምክንያቱ ደግሞ የሪያል ማድሪድ ተጭዋቾች ዌልሳዊው አጥቂ ከሳንቲያጎ በርናባው እንዲሰናበት በመፈለጋቸው ነው።

ዌልሳዊው ኮከብ ፕሪሚየር ሊጉን በ86 ሚሊዮን ውፓንድ ከለቀቀ ከ2013 ጀምሮ ወደ እንግሊዝ ይመለሳል በሚል ተደጋጋሚ ወሬ ሲናፈስ ነበር።

ታዋቂው ስፔናዊ ጋዜጠኛ Eduardo India ለTV show El Chiringuito እንዳለው ከሆነ የሪያል ማድሪድ ነባር ተጭዋቾች ሰርጂዎ ራሞስን ጨምሮ ለክለቡ ውጤት ማጣት ምክንያቱ ጋሬዝ ቤል መሆኑን ለቸርማኑ ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ነግረዋቸዋል።

ቤል በቅዳሜው የቫላዶሊድ ጨዋታ ላይ ቡድኑ 0-0 እያለ ደጋፊዎች ሲጮሁበት የተሰማ ሲሆን በርሱ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ብራዚላዊው ታዳጊ ከገባ በኃላ ቡድኑ መነቃቃትን አሳይቶ 2ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፎ እንዲወጣ ማድረግ ችሏል።

________________________________________
●  ALEXANDRE LACAZETTE'S ሜዳ ውስጥ እያሳየ ካለው ድንቅ እንቅስቃሴ እና ጎል ከማስቆጠር ሚናው ባሻገር ከሜዳ ውጪ ማቲዎ ጉንዶዚ እያሳየ ላለው ድንቅ ብቃት ምክንያት እንደሆነ ተሰምቷል። ላካዜቲ ተጭዋቹ በእንግሊዝ በፍትነት እንዲለመድ ከጎኑ በመሆን ድጋፍ እንደሚያደርግለት ተሰምቷል።

________________________________________
●  WENGER TO REAL MADRID?

ARSENE WENGER በሪያል ማድሪድ የሚፈለጉ ከሆነ የሚቀርብላቸውን ጥያቄ ላለመቀበል እንደሚቸገሩ ተገለፀ። ይሄንን ያለው የSunSport ፀሃፊ ማርቲን ሊፕቶን እንደሚለው ከሆነ አርሰን ዌንገር የሎስብላንኮዎቹ አለቃ ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ትልቁን መርከብ እንዲሾፍሩት ከሚፈልጎቸው ሰዎች መሃከል አንዱ ናቸው።

________________________________________
●  WEST HAM ዩናይትዶች የቼልሲውን ሩበን ሉፍተስ ቼክ ለማዛወር የነበራቸውን ህልም ማውሪዚዎ ሳሪ ተጨናፍጎባቸዋል።

መዶሻዎቹ ተጭዋቹን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ እንደሚያስፈርመት እርግጠኞች የነበሩ ቢሆንም በአለም ዋንጫው ላይ ለቡድኑ ድንቅ እንቅስቃሴ ያደረገውን ተጭዋች ሳሪ ለጉረቤት ተቀናቃኝ ክለብ አሳልፈው መስጠት አልፈለጉም።

እንደ Daily Mirror ዘገባ ከሆነ የዌስትሃሙ አለቃ ማኑኤል ፔሌግሬኒ ሌላኛውን የለንደን ክለብ በውሰት ውል በጥር እንዲሻገር ለማድረግ ቢጥሩም የ22 አመቱን ተጭዋች ሳሪ አለቅም በማለታቸው በስታምፎርድ ብሪጅ መቆየቱ እርግጥ ሆኑአል።

እረቡ የወጡ ያልሰማችኃቸው ዜናዎች - News You Missed Today



KYLIAN MBAPPE'S በፒ.ኤስ.ጂ ክለብ ለመቆየት የጠየቀው አስገራሚ ደሞዝና ጥቅማ ጥቅም ይፋ ሆነ። ተጭዋቹ የBallon d'Or ሽልማትን የሚያሸንፍ ከሆነ ከኔይማር ደሞዝ በላይ እንዲከፈለው ይፈልጋል።

ታዳጊው ባለተሰጥዎ ሞናኮን በመልቀቅ የፈረንሳዩን ሃብታም ክለብ ፒ.ኤስ.ጂን ባለፈው አመት በውሰት ከተቀላቀለ በኃላ በክረምቱ በቄሚ ዝውውር ለክለቡ ፊርማውን አኑሮአል።

እናም በፒ.ኤስ.ጂ የሚያቆየውን ውል ለመፈራረም የ19 አመቱ ኮከብ በአምስት አመታት የክለቡ ቆይታው አመታዊ የ£48 million ደሞዝ ከግብር በኃላ እንዲሰጠው ጠይቋል።

እንደ Football Leaks, ዘገባ ከሆነ የቀድሞው የሞናኮ ኮከብ ምባፔ በመላው አለም ያለ ደጋፊዎች ግርግርና ምንም መጨናነቅ፣ መጉላላት ሳይደርስበት ከደጋፊዎች ትኩረት በማምለጥ ከአንድ ሃገር ወደ ሌላ ሃገር እንደልቡ የሚጓዝበትን የግል ጀት ክለቡ እንዲመድብለትም ጠይቋል።

ሆኖም PSGዎች ይሄንን ሁሉ ጥያቄዎቹን ውድቅ በማድረግ ለተጭዋቹ የተለያዩ ወጪዎች መሸፈኛ ይሆን ዘንድ በወር £27,000 ቦነስ ክፍያ በመስጠት፣ ተንከባካቢ፣ ሹፌር እና ቦዲጋርድ መድበውለታል።

እንደ ሪፖርቱ ከሆነ ታዳጊው የባለንደኦር ሽልማትን የሚያነሳና የአለማችን ምርጡ የሚባል ከሆነ ከኔይማው ደሞዝ ሳምንታዊ £600,000 በላይ ደሞዝ እንዲከፈለው ጠይቆ ተስማምቷል።

________________________________________
●  ማንቸስተር ዩናይትዶች ጋሬዝ ቤልን ከሪያል ማድሪድ ለማዛወር የ£100 million ክፍያ ለማቅረብ አስበዋል። ምክንያቱ ደግሞ የሪያል ማድሪድ ተጭዋቾች ዌልሳዊው አጥቂ ከሳንቲያጎ በርናባው እንዲሰናበት በመፈለጋቸው ነው።

ዌልሳዊው ኮከብ ፕሪሚየር ሊጉን በ86 ሚሊዮን ውፓንድ ከለቀቀ ከ2013 ጀምሮ ወደ እንግሊዝ ይመለሳል በሚል ተደጋጋሚ ወሬ ሲናፈስ ነበር።

ታዋቂው ስፔናዊ ጋዜጠኛ Eduardo India ለTV show El Chiringuito እንዳለው ከሆነ የሪያል ማድሪድ ነባር ተጭዋቾች ሰርጂዎ ራሞስን ጨምሮ ለክለቡ ውጤት ማጣት ምክንያቱ ጋሬዝ ቤል መሆኑን ለቸርማኑ ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ነግረዋቸዋል።

ቤል በቅዳሜው የቫላዶሊድ ጨዋታ ላይ ቡድኑ 0-0 እያለ ደጋፊዎች ሲጮሁበት የተሰማ ሲሆን በርሱ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ብራዚላዊው ታዳጊ ከገባ በኃላ ቡድኑ መነቃቃትን አሳይቶ 2ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፎ እንዲወጣ ማድረግ ችሏል።

________________________________________
●  ALEXANDRE LACAZETTE'S ሜዳ ውስጥ እያሳየ ካለው ድንቅ እንቅስቃሴ እና ጎል ከማስቆጠር ሚናው ባሻገር ከሜዳ ውጪ ማቲዎ ጉንዶዚ እያሳየ ላለው ድንቅ ብቃት ምክንያት እንደሆነ ተሰምቷል። ላካዜቲ ተጭዋቹ በእንግሊዝ በፍትነት እንዲለመድ ከጎኑ በመሆን ድጋፍ እንደሚያደርግለት ተሰምቷል።

________________________________________
●  WENGER TO REAL MADRID?

ARSENE WENGER በሪያል ማድሪድ የሚፈለጉ ከሆነ የሚቀርብላቸውን ጥያቄ ላለመቀበል እንደሚቸገሩ ተገለፀ። ይሄንን ያለው የSunSport ፀሃፊ ማርቲን ሊፕቶን እንደሚለው ከሆነ አርሰን ዌንገር የሎስብላንኮዎቹ አለቃ ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ትልቁን መርከብ እንዲሾፍሩት ከሚፈልጎቸው ሰዎች መሃከል አንዱ ናቸው።

________________________________________
●  WEST HAM ዩናይትዶች የቼልሲውን ሩበን ሉፍተስ ቼክ ለማዛወር የነበራቸውን ህልም ማውሪዚዎ ሳሪ ተጨናፍጎባቸዋል።

መዶሻዎቹ ተጭዋቹን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ እንደሚያስፈርመት እርግጠኞች የነበሩ ቢሆንም በአለም ዋንጫው ላይ ለቡድኑ ድንቅ እንቅስቃሴ ያደረገውን ተጭዋች ሳሪ ለጉረቤት ተቀናቃኝ ክለብ አሳልፈው መስጠት አልፈለጉም።

እንደ Daily Mirror ዘገባ ከሆነ የዌስትሃሙ አለቃ ማኑኤል ፔሌግሬኒ ሌላኛውን የለንደን ክለብ በውሰት ውል በጥር እንዲሻገር ለማድረግ ቢጥሩም የ22 አመቱን ተጭዋች ሳሪ አለቅም በማለታቸው በስታምፎርድ ብሪጅ መቆየቱ እርግጥ ሆኑአል።

Tuesday, November 6, 2018

ማንቸስተር ዩናይትድ እና ባርሴሎና በሮናልዶ ዝውውር ተፋጠዋል



UNITED LAUNCH RONALDO BID

.

ማንቸስተር ዩናይትዶች የቤኔፊካ ታዳጊ ባለተሰጥዎ ሮናልዶ ካማራ ለማዛወር ከባርሴሎናዎች ጋር አንገት ላንገት ተናንቀዋል። የ15 አመቱ ባለተሰጥዎ ለቤኔፊካ ታዳጊ ቡድን በድንቅ አቋምና እንቅስቃሴ ላይ የሚገኝ ሲሆን ከአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች የእናዛውርህ ጥያቄ እየቀረበለት ይገኛል።

MANCHESTER UNITED ማንቸስተር ዩናይትዶችም ፖርቹጋላዊው ሌላኛው መጤ ታዳጊ ባለተሰጥዎ ተጭዋች ለማዛወር እንቅስቃሴ ላይ ናቸው ሲሉ በርካታ ሪፖርቶች ጠቁመዋል።

ከስፖርቲንግ ሊዝበን ትልቁን ክርስቲያኖ ሮናልዶ ካዛወሩት ከ15 አመታት በኃላ ቀያይ ሰይጣኖቹ ሌላኛውን ደግመው ለመውሰድ አልመዋል።

እንደ ፖርቹጋሉ ተነባቢ ጋዜጣ እትም Record , ገለፃ ከሆነ የቤኔፊካው ባለተሰጥዎ ሮናልዶ ካማራ ታዳጊ ቡድኑ ባደረጋቸው በUefa Youth League ጨዋታዎች በሙሉ አስደናቂ ሆኑአል።

በጃንዋሪ 2003 ላይ የተወለደው ታዳጊ ክርስቲያኖ ወደ ኦልትራፎርድ ከመዛወሩ ከሰባት ወራት በፊት ነው የተወለደው። እስከ ጁላይ ወር 2015 ድረስም የስፓርቲንግ ሊዝበን አካዳሚ ቡድን አባል ሆኖ ነበር። ከዛም ወደ ተቀናቃኛቸው ቤኔፊካ ተዛወረ።

የአማካይ አጥቂው ለፖርቹጋል ከ17 አመት በታች ቡድን አባል ቢሆንም የጊኒ ቢዛዋን ቡድን የመወከል መብትም ባለቤት ነው።

ተጭዋቹ ከእርሱ በ2 አመታት ከሚበልጡት ታዳጊዎችም ጋር ተጫውቶ ከኳስ ጋር ድንቅ እንቅስቃሴን በማድረግ የበርካቶችን ቀልብ የገዛ ሲሆን ማን.ዩናይትዶች ታዳጊውን ለማዛወር ከበርካታ ታላላቅ ክለቦች ጋር ፉክክር ማድረግ ይኖርባቸዋል።

ካማራ በቤኔፊካ እስከ 2020 ድረስ የሚያቆየው ውል ያለው ሲሆን ወሰ 16 አመት የልደት በአሉን ከማክበሩ በፊት ግን በርካታ ክለቦች ትኩረት አድርገው እየተከታተሉት ይገኛሉ። 16 አመት ከሞላው በኃላ ለፈለገው የአውሮፓ ክለብ የመፈረም ሙሉ መብት ይኖረዋል።

ባርሴሎናዎችም ከፈላጊ ክለቦቹ መሃከል አንዱ ሲሆኑ ከነርሱ በተጨማሪም ቼልሲዎች እና ማንቸስተር ሲቲዎች ባለፈው አመት ከተጭዋቹ ዝውውር ጋር ስማቸው የተነሱ ክለቦች ነበሩ።

Featured Post/ቀጣይ ልጥፍ

የዝውውር ዜናዎች

  ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር...