Saturday, December 9, 2017

የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ ሠፊ ቅድመ ዳሰሳና ትንታኔ ማን.ዩናይትድ Vs ማን.ሲቲ - Match Preview



TEAM NEWS - የሁለቱ ቡድኖች ዜናዎች፦



▪  የማንቸስተር ዩናይትዱ ኮከብ ፖል ፖግባ በእሁዱ ጨዋታ ላይ በቅጣት ምክንያት አይሳተፍም።

▪  የቡድን አጋሮቹ ኒማንያ ማቲች ምንም እንኳን ሙሉ ለሙሉ ጤነኛ ባይሆንም የደርቢው ጨዋታ ላይ ይሰለፋል። ዝላታን ኢቭራሞቪችና ፊል ጆንስ ወደ ሜዳ ይመለሳሉ።

▪  ማርዋን ፌላይኒ በበኩሉ የመጨረሻ የጤንነት ምርመራውን ከጨዋታው በፊት ያደርጋል።

▪  የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በበኩላቸው በቪሰንት ኮንፓኒ አካል ብቃት ላይ በመጨረሻ ውሳኔ ያሳልፋሉ። ተጭዋቹ ከሻክታር ዶኔትስኩ ጨዋታ ውጪ ተደርጎም ነበር።

▪  ዴቪድ ሲልቫ ለደርቢው ጨዋታ እንደሚመለስ እርግጥ ሆኑአል። ፋቢያን ዴላፕ ግን የሚሰለፍ አይሆንም።


MANCHESTER DERBY - የቡድኖቹ ወቅታዊ ብቃት


★  የEPL መሪወች የሆኑት የማንችስተሮቹ ሀያላን ክለቦች ዩናይትድና ሲቲ እሁድ ከምሽቱ 1፡30 በግዙፉና በማራኪው ኦልትራፎርድ ስታዲየም ይፋለማሉ፡፡ የ ሞሪኒሆው ዩናይትድ ባሳለፍነው ሳምንት አስደናቂ የመከላከል ስትራቴጂ ተጠቅሞ ያገኛቸውን አጋጣሚ በአግባቡ ተጠቅመው የሰሜን ለንደኑን አርሰናልን በሜዳውና በደጋፊው ፊት 3ለ1 አሸንፈዋል፡፡ ምስጋና ለ ዴቪድ ዴህያ ይሁንና
በዚያ ጨዋታ ላይ የመሀል ሜዳው ሞተር ፖግባ በፈፀመው አላስፈላጊ ፋወል ቀይ ካርድ በማየቱ የሲቲውን ጨምሮ 3 ጨዋታዎች ያልፉታል፡፡ ዩናይትድ በ 15 ጨዋታዎች 35 ነጥብ በመሰብሰብ ከሲቲ በ 8 ነጥብ ርቆ 2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡


★  በተመሳሳይ ማን ሲቲ ባሳለፍነው ሳምንት ዌስትሀምን ጋብዞ በ83ኛው ደቂቃ ሲልቫ ባስቆጠራት ጎል ሙሉ 3ነጥብ ይዞ መውጣት ችላል፡፡ የጋረዲወላው ማን ሲቲ በ 15ጨዋታዎች 43 ነጥብ በመሰብሰብ ሊጉን በ 1ኛ ደረጃ እየመራ ሲገኝ
ነገ ካሸነፈ 14 የEPL ጨዋታዎችን በማሸነፍ በአርሰናል እና በቸልሲ ተይዞ የነበረውን ያለመሸነፍ ጉዞ ከፍ ያረጋል፡፡


★  ሁለቱም የማንቸስተር ክለቦች በሳምንቱ አጋማሽ በተካሄደው የ UCL ውድድር ምድባቸውን በበላይነት ማጠናቀቃቸው የሚታወስ ነው፡፡




Your Questions - ስለ ደርቢው ተጠይቀው የተመለሱ 3ቱ ጥያቄዎች!

1. እሁድ በሁለቱ ማንችስተሮች መካከል የሚደረገው ጨዋታ በታሪካቸው ውስጥ ለስንተኛ ጊዜ ነው የሚገናኙት?

መልስ ፦ የእሁዱን ጨዋታ ሳይጨምር እስካሁን በሁሉም ውድድሮች ለ174 ጊዜ መገናኘት ችለዋል, እሁድ የሚደረገው ጨዋታ 175ተኛ የደርቢ ጨዋታቸው ነው።


2.  በማንችስተር ደርቢ ላይ ብዙ ጨዋታዋችን በመሰለፍ ቀዳሚው ተጫዋች ማን ይባላል? ስንት ጨዋታዋችን ማድረግግ ችሏል?

መልስ ፦ ሪያን ጊግስ ነው, 36 ጨዋታዋችን ማድረግ ችሏል።


3.  በማንችስተር ደርቢ ላይ ብዙ ጎል በማስቆጠር ቀዳሚው ተጫዋች ማን ይባላል? ስንት ጎል ማግባት ችሏል?

መልስ ፦ ዋይን ማርክ ሩኒ 11 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።





Who Said What? - ተጭዋቾችና አሰልጣኞች ምን አሉ?


▪  ስፖንያርዱ ኮከብ ዴቪድ ዴህያ ከቀድሞ የአርሴናል ተጨዋች ሄነሪ ጋር በስካይ ስፖርት ባደረገው ቆይታ ስለ ደርቢው ጠይቆት የሰጠው ምላሽ ፦


" የምንጫወተው በሜዳችን ነው። በደጋፊያችን ፊት የምናደርገው ልዩ ጨዋታ ነው። ደርቢ ነው እኛ በራሳችን እንተማመናለን። ጥንካሬ ይሰማናል ማሸነፍ
እንፈልጋለን"

"ቡድኑ አሁን በጣም ጥሩ ነው። ከሜዳችን ውጭ ሁለት አስቸጋሪ ጨዋታዋችን ማሸነፍ ችለና። ጠንካሮች ነን ማሸነፍ እንፈልጋለን"


▪  ማታ ስለ ፖግባ ተጠይቆ የመለሰው ፦

"ማክሰኞ እለት ቆንጆ የሆነ ኳስ አሲስት ማድረግ ችሎ ነበር። እሱ ሙሉ የሆነ ተጨዋች ነው። ሁሉንም ነገር ማድረግ የሚችል ተጨዋች ነው። የእሱ አለመኖር ክፍተት ይፈጥራል። ነገር ግን በቦታው ላይ ሌላ ተጨዋቾች መጫዋትና መሸፈን ይችላል"


▪  የማንቸስተር ሲቲው አለቃ ፔፕ ጋርዲዮላ ስለ ጨዋታው፦

 "ወደ ኦልትራፎርድ ተጉዞ መጫወት ደስታ ነው። ለዛም ነው እዚህ የተገኘነው። በጨዋታው ያለጥርጥር እዝናናለሁ።

"ወደዛው አምርቼ ለመጫወት ዝግጁ ነኝ። እዛ መሆንን በጣም እወደዋለሁ። ከነርሱ ጋር ገጥመን ምን እንደሚፈጠር ለማየት እፈልጋለሁ።

"ከዛ በኃላ ከሞሪንዎ ጋር እንደምንጨባበጥ ተስፋ አደርጋለሁ።"


MATCH Facts - የጨዋታው እውነታዎች እና ታሪካዊ ኩነቶች


▪  ሞሪንሆ በኦልትራፎርድ የተሸነፉት ከ42 ጫወታ 1 ብቻ ነው።

▪  ጋርዲዮላ በሞሪንሆን የተሸነፈው ከ19 ጫወታ 4 ግዜ ብቻ ነው።

▪  ዋይኒ ሮኒ በዚህ ደርቢ 11 ጎል በማስቆጠር ቀዳሚ ነው።

▪  ሲቲ በፕ.ሊጉ በርካታ ጎል ያስቆጠረው ኦልትራፎርድ ላይ ነው።

▪  የማንችስተር ደርቢን የጊግስን ያህል 36 ግዜ የተጫወተ የለም።

▪  ሞሪንሆ ለ51 ዓመታት በዩናይትድ ያልታየ ሪከርድ አምጥተዋል።

136 ዓመታት በፊት በኖቬምበር ወር ማንችስተር ዩናይትድ St. Mark's የሚባል ቡድንን በሜዳው ገጥሞ 3ለ0 አሸንፎ ተመለሰ ይህ ቡድን ባሁኑ
መጠሪያ ማንችስተር ሲቲ ነው። ይህ ጫወታም በሁለቱ ቡድኖች ለመጀመሪያ ግዜ የተደረገ በመባል በታሪክ መዝገብ ሰፍሯል።

ከዛ በኋላ በሁሉም ውድድሮች ለ174 ግዜ ተፋልመዋል። ዩናይትድ 72 ግዜ በማሸነፍ የበላይ ሲሆን ሲቲ 50 ግዜ ማሸነፍ ችሏል ቀሪውን 52 ጫወታ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል።

በ1947 በሊግ ውድድር በሲቲ ሜዳ 0ለ0 ሲለያዩ ጫወታውን የታደሙት 78,000 ተመልካቾች ነበሩ። ይህም በማንችስተር ደርቢ በርካታ ተመልካች
የተከታተለው ጫወታ በመሆን እስካሁን ድረስ ለ70 ዓመታት በሪከርድነት ዘልቋል።

 በተጫዋችነት እና በአሰልጣኝነት ሁለቱንም ክለቦች ያገለገሉ ባለታሪኮች ሁለት ናቸው። አሌክስ ፈርጉሰን ኦልትራፎርድ ከመድረሳቸው በፊት ዩናይትዶችን ያጀገነው የምንግዜም ምርጡ አሰልጣኝ Matt Busby ነበር። በ1920ዎቹ እና 30ዎቹ
ግን ከ200 በላይ ጫወታዎችን ለሲቲ መጫወት ችሏል በ1934 የFA CUP ማዳሊያንም ከሲቲ ጋር አጥልቋል። ከሁለተኛው አለም ጦርነት በኋላ ግን ማት ቤስቢ የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ በቆይታውም 5 የሊግ ዋንጫ ፣ 2 FA CUP ፣ እና የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግን በማሸነፍ ወርቃማ
ታሪክን መፃፍ ችሏል።

Steve Coppell በ1970ዎቹ በዩናይትድ ማልያ በቀኝ ክንፍ በኩል 300 ጫወታዎችን ማድረግ ችሏል በ1977 FA CUP ዋንጫንም መሳም ችሏል።
በ1996 ግን የሲቲ አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ ሆኖም ስልጣን ላይ መቆየት የቻለው ለ32 ቀናት ብቻ በመሆኑ በሲቲ ቤት አጭር የአሰልጣኝነት ቆይታ ያደረገ በሚል በሪከርድነት ሰፍሯል።




በፕሪምየር ሊጉ የእርስ በእርስ ግንኙነት

▪  በተወዳጁ ሊግ ለ40 ግዜያት የተገናኙ ሲሆን 20 ግዜ በማሸነፍ ዩናይትድ የበላይ ነው። ሲቲ ደግሞ 12 ግዜ ማሸነፍ ችሏል 8 ግዜ አቻ ተለያይተዋል።

▪  ዩናይትድ 59 ጎል ያስቆጠረ ሲሆን ሲቲ 51። መረባቸውን ከጎል በመታደግ ዩናይትዶች አሁንም የተሻለ ሪከርድ አላቸው 15 ሲቲ 8 በዲሲፕሊን በኩል ዩናይትድ ደካማ ሪከርድ ነው ያለው 66 ቢጫና 7 ቀይ ካርድ የተመዘዘበት ሲሆን ሲቲ 87 ቢጫና 1 ቀይ ካርድ ተመልክቷል።

▪  ዩናይትድ ከሲቲ ጋር ባደረጋቸው ያለፉት 12 የሊግ ጫወታ በ7ቱ ተሸንፏል። ይህም ከዚያ በፊት ካደረጋቸው 45 ግንኙነቶች ይልቃል ሲቲ በፕ.ሊጉ ታሪክ ከሜዳው ውጪ በርካታ ጎል ያስቆጠረው ኦልትራፎርድ ላይ ነው። (27)

▪  ዩናይትድ በጆሴ ሞሪንሆ ስር በሜዳው ባደረጋቸው 42 ጫወታዎች የተሸነፈው 1 ግዜ ብቻ ነው። (30 አሸንፎ 11 አቻ)

▪  ሞሪንሆ በሜዳቸው ባደረጉት ያለፉት 40 ጫወታዎች ሽንፈትን ባለማስተናገድ በ1966 በማት ቤስቤይ የተያዘውን ሪከርድ ተጋርተዋል።

▪  ዩናይትድ በዚህ ሲዝን አስገራሚ የመከላከል ሪከርድ አለው ከተቆጠሩበት 9 ጎሎች ውስጥ በሜዳው ያስተናገደውም 1 ጎል ብቻ ነው።

▪  ሞሪንሆ ከጋርዲዮላ ጋር ባደረጋቸው 19 ጫወታዎች ማሸነፍ የቻለው 4 ግዜ ብቻ ነው። (8 ተሸንፎ 7 አቻ) ጄሲ ሊንጋርድ ባለፉት 2 የፕ.ሊግ ጫወታ 3 ጎሎችን ማስቆጠር ሲችል ከዛ በፊት በ51 ጫወታ ካስቆጠረው ይልቃል።

▪  አጉዌሮ ከሜዳው ውጪ ባደረጋቸው ያለፉት 9 የፕ.ሊግ ጫወታዎች ጎል ማስቆጠር ችሏል። እሁድስ?

▪  በዚህ ሲዝን በፕ.ሊጉ በርካታ ኳስን ለጎል በማቀበል የሲቲ ተጫዋች የሆኑት ዴብሬይን እና ሲልቫ በእኩል 8 ይመራሉ።

▪  ሲቲ ዩናይትድ ላይ በታሪክ አጋጣሚ ሁለት ግዜ 6 ጎሎች ያስቆጠረበት ሲሆን ዩናይትድ ግን አንድም ግዜ 6 ጎል አስቆጥሮ አያውቅም።

ዩናይትድ 1–6 ሲቲ (1926)
ዩናይትድ 0–5 ሲቲ (1955)
ዩናይትድ 5–0 ሲቲ (1994)
ዩናይትድ 1–6 ሲቲ (2011)




ግምታዊ አሰላለፎች How they could line up፦


ማን.ዩናይትድ XI: De Gea; Lindelof,
Smalling, Rojo; Valencia, Matic, Herrera,
Young; Lingard, Martial, Lukaku

ማንቸስተር ሲቲ XI: Ederson; Walker,
Otamendi, Kompany, Delph; De Bruyne,
Fernandinho, Silva, Sterling, Aguero, Sane


የቢቢሲው ገማች - LAWRO'S PREDICTION


የቪሰንት ኮምፓኒ ጨዋታው ላይ መሰለፍ አለመሰለፍ አጠራጣሪ መሆን የሲቲን የሲዝኑ የመጀመሪያ ጨዋታ ድል እንድገምት አድርጎኛል።

እንደማስበው ማንቸስተር ዩናይትዶች አራት ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ የብቃታቸው ጫፍ ላይ ይገኛሉ። አርሰናልን ተከላክለው ያሸነፍበት መንገድ ድንቅና አሳማኝ ነበር።

ግምቴ Prediction: 2-0


የሱፐር ኮምፒተሩ ግምት - SAM's verdict


ሊቆጠር የሚችለው የጎል ብዛት: 1-1
አቻ የመውጣት እድላቸው: 27%
የባለሜዳው የማሸነፍ እድል: 29%
ከሜዳ ውጪ የማሸነፍ እድል: 44%

SAM ሱፐር ኮምፑይተር ሲሆን (Sports Analytics Machine) በመባል ይታወቃል። ማሽኑን የፈጠረው የሊቨርፑል ዩንቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆነው ProfIan Mc Hale ነው።


ዘንድሮስ ማን የበላይ ይሆን ይሆን በሜዳው አይበገሬ የሆነው የሞሪንሆው ዩናይትድ ወይስ ያለፉትን 13 የፕ.ሊግ ጫወታን ያሸነፈው የጋርዲዮላው ሲቲ እሁድ ምሽት የምናየው ይሆናል!

Friday, December 8, 2017

አርብ ምሽት ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update



የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ዚኔዲን ዚዳን በጥር  የዝውውሩ መስኮት ላይ አዲስ ግብ ጠባቂዉን ወደ ክለባቸዉ ማዘዋወር እንደሚፈልጉ ተነግሮል።
(Source: Daily Express)


በተያያዘ ዜና ሪያል ማድሪድ ዳቪድ ደያን ከማንንችስተር ዩናይትድ ለማስፈረም የማይፈነቅሉት ዲንጋይ የለም ተብሎል። ዛዳንም በጥር ሁለት ግብ ጠባቂወችን ማስፈረም መፈለጋቸዉ ተከትሎ ዋነኛዉ እና አንደኛዉ ኢላማቸዉ ደግሞ ዳቪድ ዴያ ነዉ ተብሎል።   (Source: MEN)


የእንግሊዙ ክለብ ወልብርሃምተን የቤኔፊካዉን አማካኝ ጆኦ ካርቫልሆን በ€15 million ለማስፈረም እየተመለከቱት ነዉ ተባለ። (Source: Birmingham Mail)


የባርሴሎናዉ ኮከብ አርጀንቲናዊዉ  ምትሀተኛ ሊዩነል ሜሲ እግር ኮስን በልጅነት ክለቤ ኒዌልስ ኦልድ ቦይ መጨረስ እንደሚፈልግ ተናግሮል።  (Source: Daily Express)


የፕሪሜር ሊጉ ክለብ ብራይተን በ£20m
 የዝውውር ሂሳብ በጥር የሴልቲኩን አጥቂ ሙሳ ዴምቤሌን ማስፈረም ይፈልጋሉ ሲል፣ (Source: Daily Mail) አስነብቧል።


አርሰናሎች ኮከባቸዉን ሜሲት ኦዚልን በክለቡ ለማቆየት ሲሉ አዲስ እና የተሻሻለ ኩንትራት ሊያቀርቡለት እንደሆነ እየተዘገበ ነዉ። በዚህም በተያያዘ እንዲሁም አሌክሲ ሳንቸዝን  በጥሩ ክለቡን ከመልቀቁ በፊት አዲስ ኩንትራት በማስፈረም በክለባቸዉ ማቆየት ይፈልጋሉ ተብሎል። (Source: Sun Sport)


ጀርገን ክለፕ ብራዚላዊዉን ኮከባቸዉን ፊሊፕ ኮንቲኒሆን በጥር ወር ለመሸጥ ሊገደዱ ይችላሉ ተብሎ። ምክንያቱ ደግሞ ኮንቲኒሆ በክለቡ መቆየት አለመፈለጉ እና በስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና በጥብቅ መፈለጉ ነዉ ተብሎል። (Source: Daily Star)


የሻልክ 04ቱ አማካይ ሊዮን ጎረትዝከ ስሙ በተደጋጋሚ ግዜ ከአርሰናል እና ማንቸስተር ዩናይትድ  ዝውውር ጋር ሲነሳ ቢቆይም በጥር የዝውውርችመስኮት ላይ ወዴትኛው ክለብ እንደሚያመራ ውሳኔ አሳልፋለሁ ሲል ተናግሮአል።
(Mail)


የሳምንቱን ታላቅ ጨዋታ ማን.ዩናይትድ Vs ማን.ሲቲ  ሠፋ ያለ ቅድመ ዳሰሳ ነገ ይጠብቁን!


የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ፖርቹጋላዊዉ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የ2017 የባላንዶር ሽልማት ለ5ኛ ጊዜ አሸነፈ። ሮናልዶም በባሎንዶር ሽልማት ታሪክ 946 ድምፅ አግኝቶ በማሸነፍ አዲስ ታሪክ አፅፎል። ሮናልዶ የባላንዶር ሽልማቱን 5 ጊዜ በማሸነፍ ከተቀናቀኙ ሊዩነል ሜሲ ጋር እኩል ሆኖል። (bbc). ሙሉ 30ውም የባለንደዎር ተጭዋቾች ዝርዝር የሚከተለው ነው። ደረጃው የተሰጣቸውን ነጥብ መሰረት ያደረገ ነው። = ምልክት ያለበት በሁለት ተጭዋቾች በጋራ የተያዘ ደረጃ ነው። (Ballon d'Or top 30 voting) ...


29= Philippe Coutinho
29= Dries Mertens
28. Edin Dzeko
27. Mats Hummels
26. Jan Oblak
25. Karim Benzema
24. Radamel Falcao
23. Sadio Mane
21= Leonardo Bonucci
21= Pierre-Emerick Aubameyang
20. David de Gea
19. Eden Hazard
18. Antonio Griezmann
17. Toni Kroos
16. Marcelo
15. Paulo Dybala
14. Kevin de Bruyne
13. Luis Suarez
12. Isco
11. Cavani
10. Harry Kane
9. Robert Lewandowski
8. N'Golo Kante
7. Kylian Mbappe
6. Sergio Ramos
5. Luka Modric
4. Guanluigi Buffon
3. Neymar
2. Lionel Messi
1. Cristiano Ronaldo

Thursday, December 7, 2017

ሃሙስ ምሽት ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update



ARSENAL CLOSE ON GORETZKA


አርሰናሎች የሻልካውን አማካይ ሊዮን ጎረትዝክን ዝውውር ለማጠናቀቅ ተቃርበዋል። ተጭዋቹን በክረምት ነፃ ዝውውር ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል ያለው The Sun ነው።

ጀርመናዊው ኢንተርናሽናል በአመቱ መጨረሻ ላይ በክለቡ ያለው ቀሪ ኮንትራት ሙሉ ለሙሉ የሚጠናቀቅ ሲሆን ከወዲሁ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ከፈለገው ክለብ ጋር በዝውውሩ ዙሪያ መደራደር ይችላል። ፉክክሩንም መድፈኞቹ እየመሩት ነው ተብሏል።


BARCA PRIORITISE £127M COUTINHO


ባርሴሎናዎች በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ የሊቨርፑሉን ብራዚላዊ ኮከብ ፍሊፕ ኩቲንዎ በ£127 million ሂሳብ ለማጠናቀቅ ቆርጠዋል ሲል Mundo Deportivo ዘገበ።

የላሊጋው ክለብ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ዝውውሩን ያጠናቅቀዋል በሚል ሲጠበቅ ቢቆይም ሳይጠናቀቅ ቀርቷል። ያም ቢሆን ብራዚላዊው አሁንም የባርሴሎናዎች ቀዳሚ የዝውውር ኢላማ በመሆኑ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ በድጋሚ ለዝውውሩ የሊቨርፑልን በር ያንኲኲሉ ተብሏል።

የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ዚኔዲን ያዚን ዚዳን እና ፕሬዝዳንቱ ፍሌሬንቲኖ ፔሬዝ የቼልሲዉን ኮከብ ቤልጄማዊዉን ተጫዋች ኤደን ሀዛርድን ለማስፈረም እየተመካከሩ ነዉ ተባለ። (Diario Gol via Daily Mail)




ዌስትብሮሚች አልቤን ተከላካያቸዉ ጆኒ ኢቫን በፕሪሜር ሊጉ ክለቦች እየተፈለገ ነዉ። ከፈላጊ ክለቦች መካከል ማንችስተር ሲቲ እና ዌስታሃም ዩናይትድ ይገኙበታል።  (Daily Mirror)



የጣሊያኑ ክለብ ኢንተር ሚላን የማንችስተር ዩናይትድ ጨዋታ አቀጣጣይ ስፔናዊዉ የ29 አመቱ ዩሃን ማታን ለማስፈረም አነጣጥረዉበታል። በአንፃሩ ማንችስተር ዩናይትድ ማታን የሚያጣ ከሆነ የኢንተሮችን አማካኝ ጆአኦ ማሪኦን ማስፈረም ይፈልጋሉ ተብሎል። (Corriere dello Sport - in Italian)



የእንግሊዞቹ ክለቦች የሆኑት ማንችስተር ሲቲ እና ሊቨርፑል የኒሱን አማካኝ ጄን ሴሪን የማዘዋወር ፍላጎት አላቸዉ ተባለ። ተጫዋቹ ከዚህ በፊት በስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና ሲፈለግ መቆየቱ ይታወሳል። (Daily Mail)



እስኮትላንዳዊዉ የዌስታሃሙ አሰልጣኝ ዳቪድ ሞይስ ግብ ጠባቂያቸዉን ጆኦ ሀርትን ለቅዳሜዉ የቼልሲ ጨዋታ በቆሚ አሰላለፍ ዉስጥ አካተዉታል ተብሎል።  (Guardian)



የቦልተኑ አጥቂ ጋሪ ሜዲን በሰንደርላንድ እራዳር ዉስጥ ገብቶል በዚህም ተጫዋቹ በጥር ክለቡን ሊለቅ ይችላል ተብሎ ይታሰባል። (Sunderland Echo)


የማንችስተር ሲቲዉ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዌላ የአርሰናሉን አጥቂ አሌክሲ ሳንቼዝን በእጁ ለማስገባት በድጋሜ በጥር ለማዘዋወር ከአሁኑ ከተጫዋቹ ጋር ንግግር ሊያደርጉ ነዉ ተባለ። (Independent)


ኤቨርተን የአርሰናሉን አጥቂ እንግሊዛዊዉን ቲዮወ ዋልኮትን የማስፈረም ተቀዳሚ አማራጭ አድርገዉታል ተብሎል። (Daily Mail)


የምእራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የጁቬንትሱን ተከላካይ አሌክስ ሳንድሮን የማስፈረም እቅዱን ከአሁኑ ጀምሮል፤ ቼልሲ ተጫዋቹን በክረምቱ ለማስፈረም ቢጥርም ሳይሳካለት መቅረቱ ይታወሳል ሲል፣ (Telegraph) ዘግቧል።


ቼልሲዎች በክለባቸው ከፍተኛ ተከፋይ በማድረግ ኤደን ሀዛርድን ለማቆየት እና ከሪያል ማድሪድ አይን ዉስጥ ለመጠበቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን  bbc የዘገበ ሲሆን በሳምንትን £300.000 ሊከፍሉት እንዳሰቡ ጋዜጣዉ አያይዞ ዘግቧታል።


ቀያይ ሰይጣኖቹ ማንችስተር ዩናይትዶች የላዚዮ ተጫዋች የሆነውን ሰርጂ ሚሊንኮቪችን በሚቀጥለው ክረምት የዝውውር መስኮት ለማስፈረም ማሰባቸው የተዘገበ ሲሆን ለዝውውሩም እስከ €40 millon ድረስ ያወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።   (daily star)

Wednesday, December 6, 2017

ዕረቡ አመሻሽ ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update



MAN CITY READY BIG ALEXIS BID


ማንቸስተር ሲቲዎች ለአርሰናሉ አጥቂ አሌክሲስ ሳንቼዝ በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ትልቅ ሂሳብ ለማቅረብ ተሰናድተዋል ሲል የእንግሊዙ ጋዜጣ Independent ዘገበ።

ቺሊያዊው አጥቂ የፔፕ ጋርዲዮላውን ቡድን ለመቀላቀል ተቃርቦ የነበረ ሲሆን በ2018 ላይ ከኮንትራቱ ነፃ ይሆናል። ማን.ሲቲዎች ለዝውውሩ በ£50 million ሂሳብ ሊያዛውሩት ቆርጠዋል።


WALCOTT EYED AS LUKAKU REPLACEMENT


ኤቨርተኖች ቲዎ ዋልኮትን በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ቲዎ ዋልኮትን ለማዛወር እና ሮሚዮ ሉካኩን ቦታ ለመሸፈን ንግግር ማድረግ መጀመራቸው ታውቋል። ከወዲሁ በዝውውሩ ላይ ከክለቡ አርሰናል ጋር ንግግር ማድረግ እንደጀመሩ የእንግሊዙ Daily Mail ዘገበ።

ሉካኩ ጉዲሰን ፓርክን በመልቀቅ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ በክረምቱ የ£75 million ሂሳብ የተዛወረ ሲሆነ እስካሁን ድረስ ምትኩን አላዛወሩም።

ዋልኮት በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ለሽያጭ የቀረበ ሲሆን በዚህ የውድድር መስኮት ላይ በክለቡ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን አንድም የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማድረግ አልቻለም። በኤቨርተኑ አዲስ አለቃ ሳም አላርዳይስ ለዝውውር በጥብቅ ይፈለጋል።


MAN CITY'S INCREDIBLE MESSI BID


ማንቸስተር ሲቲዎች ለሊዮኔል ሜሲ የ€100 million የዝውውር ሂሳብ እና አመታዊ የ€50m አመታዊ ደሞዝ ሊያቀርቡለት አስበዋል ሲል የስፔኑ ጋዜጣ Marca ዘገባ ጠቁሟል።

የተጭዋቹ የካምፕ ኑ ቆይታ አዲሱን ኮንትራት በቅርቡ ከመፈረሙ በፊት ጥርጣሬ ውስጥ ገብቶ የነበረ ሲሆን ከዛ በፊት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ክለብ ኢትሃድ ይዛወራል በሚል ስሙ በተደጋጋሚ ግዜ ሲነሳ ቆይቶአል።

ያም ሆኖ ሜሲ ኑ ካምፕን ለቆ የመጔዝ ምንም አይነት ፍላጎት የሌለው ሲሆን አሁንም ምንም እንኳን አዲስ ኮንትራት ቢፈርምም ሲቲዎች ካቀረቡለት ደሞዝ በእጅጉን ያነሰ ሂሳብ ነው። ሲቲዎች ያቀረቡለት ደሞዝ ደግሞ ከአለን እግርኳስ ተከፋዮች ሁሉ ሪከርድ የሚሆን የክፍያ ሂሳብ ነው። ከኔይማር ክፍያም የሚበልጥ ነው።


MAN UTD WATCH €80M-RATED LAZIO STAR



የማንቸስተር ዩናይትዶች ዋና መልማዮች ሰርጂ ሚሊንኮቪች ሳቪችን በአካል ተገኝተው እንቅስቃሴውን ተከታትለውታል። ቡድኑ ላዚዮ በሴሪአው ጨዋታ ላይ ሳምፕዶሪያን 2-1 በሳምንቱ መጨረሻ ሲያሸንፉ ለቡድኑ ውጤት ማማር ትልቅ አስተዋፅዎ ተወጥተዋል Calciomercato ዘገበ።

አማካዩ በጨዋታው ላይ አንድ ጎል ያስቆጠረ ሲሆን ለሌላኛው ጎል መቆጠርም አመቻችቶ ማቀበል ችሏል። ተጭዋቹን ላዚዎዎች በክረምቱ የዝውውር መኮት ላይ ሰርቢያውን ተጭዋች የሚለቁት ከሆነ ለዝውውሩ ከማን.ዩናይትድ የ €80 million ሂሳብ ይፈልጋሉ ተብሏል።


BARCELONA MAKE AOUAR CONTACT


ባርሴሎናዎች የሊዮኑን ታዳጊ ኮከብ ሆሴም አውራስ ወኪል ጋር የተነጋገሩ ሲሆን የማዛወር ፍላጎት ፍላጎት እንዳላቸው በመግለፅ ለወኪሉ ነግረውታል ሲል የፈረንሳዩ ጋዜጣ L'Equipe ዘግቧል።

አውራ በዚህ የውድድር አመት ላይ በሊግ 1 ውድድር ላይ ምርጥ ብቃቱን እያሳየ ያለ ተጭዋች ሲሆን ባርሴሎናዎች የ19 አመቱን ተጫዋች እንደ መጠባበቂያ የዝውውር ኢላማ ያልሆነ ሲሆን በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ተጣድፈው እንደማያዛውሩት ተሰምቷል።


ARSENAL IN N'ZONZI TALKS




ሲቪያዎች ስቲቭ ንዞንዜ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ወደፈለገበት ክለብ እንዲዛወር በሚል ወደ ለንደን ተጎዞ ከአርሰናል ጋር ንግግር እንዲያደርጉ ፈቅደውለታል። ተጭዋቹ ከአሰልጣኝ ኢድዋርዶ ቤሪዞ ጋር ሜዳ ላይ መጋጨቱ የሚታወስ ነው ሲል COPE ዘግቧል።

ንዞንዜ ክለቡ ሲቪያ ባለፈው ወር ላይ በቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ላይ ሊቨርፑል ጋር 3-3 ከተለያዩ በኃላ ለክለቡ ተጫውቶ አያውቅም ሲል ዘገባው አክሎ ገልፆአል። ሊቨርፑሎች የቀድሞውን የብላክበርን ተጭዋች ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ከአርሰናሎች ጋር ፉክክር የሚያደርጉ ሲሆን ኤቨርተኖችም ሌላኞቹ ፈላጊ የሆኑ የሊጉ ክለብ ናቸው።

Tuesday, December 5, 2017

ማክሰኞ አመሻሽ ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update



MAN UTD CONFIDENT OF £50M ROSE
DEAL


የማንቸስተር ዩናይትዱ አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ የቶተንሃሙን ግራ ተመላላሽ ዳኒ ሮዝ በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በ£50 million ሂሳብ እንደሚያዘዋውሩት እርግጠኞች ሆነዋል ሲል Daily Mail ዘገበ።

ሞሪንዎ አዲስ ግራ ተመላላሽ ለማስፈረም ወደ ገበያው የሚወጡ ሲሆን ቦታው አሁንም ክፍት እንደሆነና ተጭዋቹ ሁነኛ የረጅም ግዜ የቦታው ትክክለኛ ሰው እንደሆነ ያምናሉ ሲል ዘሰን ዘግቧል። ተከላካዩ በቶተንሃም እንደማይቆይ ፍንጮች ታይተዋል።

አሁን ማን ዩናይትዶች ምንም እንኳን ቶተንሃሞች ተጫቹን ላለመልቀቅ ከፍተኛ ትግል ላይ የነበሩ ቢሆንም በጥር ላይ ካልሆነም በክረምቱ የዝውውር መኮት ላይ ከጃቸው እንደሚያስገቡት እርግጠኞች ሆነዋል።


የዜናዎቹ ስፖንሰር ጆርካ ኢቭንትስ ነው!



★★★★★★⚡(ማስታወቂያ)⚡★★★★★★

👏👌ጆርካ ፌስት 📅ቅዳሜ_ሚያዝያ_06_2010  ⌚ ከቀኑ 6:00 ጀምሮ በጊዮን ሆቴል 

🍻🍹🍺 በርካታ የከተማችን ታዋቂ ምግብ ቤቶች የሚሳተፉበት በአይነቱ ልዩ የሆነ የምግብ እና የመጠጥ ፌስቲቫል። እንዲሁም በዕለቱ ...

🎤 አበበ ከፈኒ(ጀኒና) 
🎤 ሰለሞን ሀይለ 
🎤 እሱባለው ይታይህ 
🎤 ያሬድ ነጉ 
🎤 ጌትሽ ማሞ እና 
🎤 ሮፍናን ስራቸውን ያቀርባሉ። 

💰 መግቢያ 200ብር 

📞 ለበለጠ መረጃ: 0975 06 06 06 / 0911 15 00 13 / 0974 07 07 07


HAZARD HOLDING OUT FOR MADRID OFFER


ቤልጂየማዊው ኮከብ ኤዲን ሃዛርድ የሪያል ማድሪድን የዝውውር ጥያቄ እየጠበቀ በመሆኑ ከክለቡ ቼልሲ ጋር ሲያደርግ የቆየውን የአዲስ ኮንትራት ንግግር ድርድር ለግዜውም ቢሆን አቁሞታል ሲል The Times ገለፀ።

የሰማያዊዎቹ ቦርድ ሃላፊዎች ኤዲን ሃዛርድን የክለቡ የምንግዜውም ከፍተኛ ተከፋይ ሊያደርጉት ያቀዱ ሲሆን ሳምንታዊ የ£300,000 ደሞዝ ሊያቀርቡለት ይፈልጋሉ።

ያም ሆኖ ኢደን ሃዛርድ በቼልሲ የሚያቆይ ቀሪ የሁለት አመት እና ስድስት ወራት ኮንትራት ያለው ቢሆንም ክለቡ ያቀረበለትን አዲስ ውል ለመፈራረም እያመነታ ይገኛል። የሎስ ብላንኮዎቹን የእናዛውርህ ጥያቄም በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።


ARSENAL TO SELL WALCOTT


አርሰናሎች በመጨረሻም ቲዎ ዋልኮትን በጥር የዝውውር መኮት ላይ ለመሸጥ ወስነዋል ሲል ዘ ሰን ጋዜጣ ዘገበ።

ዋልኮትን ለማዛወር የቀድሞ ቡድኑ ሳውዛምፕተን እና ዌስትሃም ዩናይትዶች እንግሊዛዊውን ኢንተርናሽናል ጥር ላይ ለማዛወር ይፎካከራሉ ሲል ጋዜጣው አክሏል። ከተጫዋቹ ሽያጭ በሚያገኙት ገንዘብ በምትኩ የሊዮኑን አጥቂ ናቢ ፊከርን ለማዛወር ይሞክራሉ።


MOURINHO TO BE GIVEN £80M IN JANUARY


እንደ እንግሊዙ ተነባቢ ጋዜጣ The Sun ሃተታ ከሆነ ጆዜ ሞሪንዎ ለጥሩ የዝውውር መስኮት የሚሆን የ£80 million የዝውውር ሂሳብ ክለቡ የሚሰጣቸው ሲሆን ገንዘቡን ከሉክ ሾው እና ማቲዎ ዳርሜይን ሽያጭ የሚያገኙት ይሆናል።

ማንቸስተር ዩናይትዶች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ ከማን.ሲቲዎች እኩል እግራቸውን በመያዝ ለመከታተል እያሰቡ ሲሆን ጆዜ ሞሪንዎም በመጪው ጥር የዝውውር መስኮት ላይ ግራ ተመላላሽ፣ ቀኝ ክንፍ መስመር እና የ10ቁ ተጭዋች በማዛወር ቡድናቸውን ማጠናከር ይፈልጋሉ።


EVERTON JOIN RACE FOR EVANS


አዲሱ የኤቨርተን አሰልጣኝ ሳም አላርዳይስ የዌስት ብሮሙን መሃል ተለላካይ ጆን ኢቫንስን ለማዛወር የሚደረገውን ፉክክር ተቀላቅለውታል ሲል ESPN FC ዘገበ።

የቶፌሶቹ ተከላካይ ክፍል በዚህ የውድድር አመት ላይ በመጥፎ ብቃት ላይ የሚገኙ ሲሆን የ29 አመቱን የሰሜን አየርላንድ ኢንተርናሽናል ለማዛወር ከአርሰናል ፣ ማንቸስተር ሲቲ እና ሌሎች ክለቦች ጋር ፉክክር ለማድረግ ተሰናድተዋል።

Saturday, December 2, 2017

እሁድ ከሰአት በኃላ ላይ የተሰሙ በርካታ አጫጭር እና ሠፋ ያሉ የዝውውር ጭምጭምታዎች፣ ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም ትኩስ ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎችን ያንብቡ



CHELSEA WANT AUBAMEYANG



የቼልሲዎች አሰልጣኝ አንቶኒዮ ኮንቴ በቦሩሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ፒር ኢምሬክ ኦበምያንግን ለማዛወር ከሊቨርፑል ጋር ለማዛወር ፉክክር ላይ ናቸው ሲል Sunday Express ዘግቧል።

ከጀርመን የወጡ ሪፖርቶች እንዳሉት ከሆነ
BVBዎች አጥቂውን ለመሸጥ ዝግጁ ሲሆኑ በዚህ የውድድር አመት ላይ ተጭዋቹ በጥሩ ብቃት ላይ ይገኛል።

ምንም እንኳን የርገን ክሎፕ ከዚህ በፊት ያሰለጠነው ጋቦናዊው አጥቂ ጋር አብሮ መስራት ቢፈልግም በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ እሱን ለማዛወር ከቼልሲ ጋር መፎካከር አለባቸው ተብሏል።


NEYMAR HAS REAL MADRID DEAL



ኔይማር ከሪያል ማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ጋር በ2019 የዝውውር መስኮት ወደ ክለቡ ለመዛወር ከወዲሁ ቅድመ ስምምነት ማድረጉን የስፔኑ ጋዜጣ Don Balon ዘገበ።

ብራዚላዊው ባርሴሎናን በክረምቱ በመልቀቅ በአለም ሪከርድ የዝውውር ሂሳብ €222 million ወደ ፒ.ኤስ.ጂዎች ማምራቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከወዲሁ ወደ ስፔን ለመመለስ እያቀደ ነው።


SANDRO OPENS CHELSEA DOOR



አሌክስ ሳንድሮ አሁንም ከ2018ቱ የአለም ዋንጫ በኃላ ወደ ቼልሲ የመዛወር ፍላጎት እንዳለው በመግለፅ ለቼልሲዎች ተስፋ ሰጥቶአል ሲል የጣሊያኑ TMW ዘግቧል።

ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ተመላላሽ ተከላካይ በባለፈው ክረምት ላይ ወደ ሰማያዊዎቹ ይዛወራል በሚል ሲወራበት ቢቆይም ከሩሲያው የአለም ዋንጫ በኃላ ግን ወደ ለንደን መምጣቱ የማይቀር እንደሆነ ዘገባው አትቷል።

ቀያይ ሰይጣኖቹ ማንችስተር ዩናይትዶች የቶተንሃሙን የግራ መስመር ተጫዋች የሆነዉን ዳኒ ሮዜን በ45 million  ለማስፈረም የጥር ወር የዝውውር መስኮትን እየተጠባበቁ ነዉ። የ27 አመቱ እንግሊዛዊዉ ተከላካይ ሮዝ በክለቡ ቶተንሃም ባለዉ ሁኔታ ደስተኛ አይደለም ሲል (Daily Star Sunday) ዘግቧል።


በአይቴል ሞባይል ኢትዮጵያ ስፖንሰር የተደረገ
ፅድት ጥርት ያሉ ምስሎች የአይቴል S11 እና S31 ስልኮች መለያዎች ናቸው



ሊቨርፑል ተዘጋጅተዋል ዳኒኤል ስቶሪጅን በመሸጥ በምትኩ የቦርሲያ ዶርትመንዱን አጥቂ ጋቦናዊዉን ፒኤሬ ኤምሪክ ኦባሜያንግ መግዛት። ከዚህ በፊት በዶርትመንድ ቤት ከአሰልጣኝ ጀርገን ክሎፕ ጋር አብረዉ መስራታቸዉ ይታወሳል። ተጫዋቹ ዳግመኛ በክሎፕ ስር ለመሰልጠን ወደ አንፊልድ ሊመጣ ይችላል ተብሎል። (Sunday Express)


አዲሱ የኤቨርተን አሰልጣኝ ሳማላርዳይስ የጥር የዝውውር መስኮት ላይ የሲቪያዉን አማካኝ ሲቴቬን ኒዞንዚን በ25 million ለማስፈረም እቅዳቸዉ ዉስጥ አካተዉታል ተባለ። (Mail on Sunday)


ማንችስተር ዩናይትድ የሪያል ማድሪዱን ዌልሳዊዉን አጥቂ ጋሬዝ ቤልን ለማስፈረም የዝውውሩን ሂሳቡን ዝቅ አድርገዉታል። ዩናይትዶች 100 million የነበረዉን ሂሳቡን ዝቅ ያደረጉበት ምክንያት ደግሞ እድሜዉ መግፋቱን ተከትሎ ቤል ለብዙ ጊዜ ሊያገለግላቸዉ ስለማይችል ነዉ ተብሎል። ማንችስተር ዩናይትድ 28 አመት ላይ የሚገኘዉን ቤልን በ£50m ወይንም በ£60m ሊያስፈርሙት ይችላሉ ሲል፣ (Sunday Mirror) አስነብቧል።


ማንችስተር ሲቲ የዌስትብሮሚች አሌቤኑን ተከላካይ የሆነዉ ጆንስ ኢቫንስን በጥር ለማስፈረም ቢጥሩም የሚሳካላቸዉ አይመስልም በዚህም ተጫዋቹን በክረምት ለማስፈረም ማሰባቸዉ ተነገረ። (Sunday Express)


ሪያል ማድሪድ የሊቨርፑሉን ኮከብ ግብፃዊዉን መሀመድ ሳላህን ለማስፈረም ፍላጎት እንዳለዉ ታወቀ። (ON Sport TV - Egypt, via Evening Standard)

Friday, December 1, 2017

Arsenal vs Manchester United: የጨዋታው ሰፊ ቅድመ ዳሰሳ




የማን ጨዋታ ነው What is it?

ጨዋታው በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ 4ተኛ የሆኑን አርሰናሉች 2ተኛ ከሆኑት ማንቸስተር ዩናይትዶች ጋር የሚያደርጉት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከባዱ ጨዋታ ነው።


ጨዋታው መቼ ይደረጋል When is it?

ጨቃታው ነገ ማለትም ቅዳሜ በኤምሬትስ ስታዲየም ከምሽቱ 2:30 ላይ የሚደርሀግ ይሆናል።


አርሰናሎች የፕሪሚየር ሊጉን ትልቁ ተቀናቃኛቸው ማን ዩናይትዶች በኢምሬትስ ስቴዲየም ሲያስተናግዱ የሳምንቱ ከባድ ጨዋታ የሚደረግ ይሆናል።

ማንቸስተር ዩናይትዶች ባለፈው ማክሰኞ ከሜዳቸው ውጪ ዋትፎርድን ገጥመው 4-2 በሆነ ውጤት ሲያሸንፉ ምስጋና ለአሽሊ ያንግ ብቃት ውና ለአንቶኔ ማርሻል ጎል ይሁንና እረፍቱን 3ለ0 እየመሩ ነበር ያጠናቀቁት። ከረፍት መልስ ትሮይ ዲኔይ እና አብዱላዬ ባስቆጠሩአቸው ጎሎች ዩናይትዶችን ጭንቀት ውስጥ ከቶአቸው የነበረ ቢሆንም ጄሲ ሊንጋርድ ባስቆጠረው ድንቅ የግል ጥረት ጎል 4ለ2 ሆነው እፎይ ብለዋል።


አርሰናሎች የጎል ናዳ አውርደዋል Rampant Arsenal


አርሰናሎች በበኩላቸው በእረቡው የ5-0 ሃድስፊልድ ድል የጎል ናዳ አውርደውባቸዋል። አሌክሳንደር ላካዜቲ የመጀመሪያውን ጎል ሲያስቆጥር ከዛ በኃላ የነበረው ሰአት ለመድፈኞቹ የጭንቅ ሰአት ነበር።

ቡድኑ በሜሱት ኦዚል በአምስት ደቂቃዎች ውስጥ ሁለት አሲስት እና አንድ ጎል ምስጋና ይግባና ውጤቱን ወደ 5ለ0 ቀይረውታል። ኦሊቨር ዝሩድ ሁለት ጎሎችን ሲያስቆጥር አሌክሲስ ሳንቼዝ በበኩሉ አንድ ጎል ከመረብ አዋህዷል።

አርሰናሎች የቅዳሜውን ጨዋታ ሜዳቸው ላይ የሚያደርጉ በመሆናቸው የተሻለ የማሸነፍ እድል ይኖራቸዋል።
አርሰናሎች በዚህ አመት ላይ በኤምሬትስ ድንቅ ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛሉ።

መድፈኞቹ በዚህ አመት በኤምሬትስ ያደረጓቸውን ሰባቱንም ጨዋታዎች ማሸነፍ ችለዋል። (ማንቸስተር ዩናይትዶችም እንደዛው)

ማን.ዩናይትዶች በበኩላቸው በሁሉም ውድድሮች ላይ ከሜዳቸው ውጪ ያደረጔቸውን ያለፉት 5ት ጨዋታዎች ላይ 3ቱን ተሸንፈዋል።

ጆዜ ሞሪንዎ ይሄንን በመሳሰሉ ትላልቅ የሊጉ ጨዋታዎች ላይ ይዘው የሚገቡት የመከላከል አጨዋወት ስልት ቡድኑን እንዲተች ያደረጉት ነገሮች ናቸው። ልክ ሊቨርፑል እና ቼልሲ ላይ ይዘው የገቡት አይነት ታክቲክ ይዘው እንደሚገቡ ይጠበቃል።

አርሰናሎች ሦስቱ ተከላካዮቻቸው ማለትም ሎረንት ኮሽሌይኒ ፤ ሽኮድራን ሙስታፊ እና ናቾ ሞንሪያል አንድ ላይ በተሰለፉባቸው ስድስት ጨዋታዎች ላይ ምንም ጎል ሳይቆጠርባቸው ጨርሰዋል።


የአርሰናል የቡድን ዜናዎች Arsenal team news


አሌክሳንደር ላካዜቲ በእሮቡ ጨዋታ ላይ በእረፍት ጊዜ ተቀይሮ የወጣ ሲሆን የGroin ጉዳት ደርቦበታል። አርሰን ዌንገር ከጨዋታው በኃላ ስለ ተጭዋቹ እንዲህ ብለዋል..

“ጥቂት ጨዋታዎች ያመልጡታል”

ኦሊቨር ዥሩድ ቦታውን በመተካት ቋሚ ተሰላፊ እንደሚሆን ይጠበቃል።

አልምክስ ኢዎቢ ከደረሰበት የDead leg ህመም በማገገሙ በድጋሚ ወደ ጨዋታ ለመመለስ ዝግጁ ሆኖአል።

ዳኒ ዌልቤክም የቀድሞ ክለቡን ለመግጠም ዝግጁ ነው። እንግሊዛዊው ኢንተርናሽናል አጥቂ ከቀድሞ ክለቡ ጋር ባደረጋቸው ጨዋታዎች ላይ ለ3ት ተከታታይ ጊዜ ጎሎችን አስቆጥሮአል።

የሳንቲ ካዞርላ ጉዳት ግን አሁንም አላገገመም። ተጫቹ ከደረሰበት የቁርጭምጭሚት ጉዳት ለመዳን ሌላ ቀዶ ጥገና ማድረጉን ከቀናት በፊት ይፋ አድርጔል።


የማንቸስተር ዩናይትድ የቡድን ዜናዎች Manchester United team news

ማርዋን ፌላይኒ በደረሰበት የጉልበት ጉዳት ሳቢያ ከጨዋታው ውጪ ሆኑአል። ቤልጂየማዊው ስለማይኖር የዩናይትዶች የመሃል ሜዳ ክፍል አማራጭ ይጠባል።

ኒማንያ ማቲች በደረሰበት የጡንቻ ችግር ሳቢያ ተቀይሮ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም ለነገው ጨዋታ ግን እንደሚመለስ ይጠበቃል።

ማይክል ካሪክ ግን ከጨዋታው ውጪ መሆኑ ታውቋል።
ፖል ፖግባ በበኩሉ ከጉዳት ከተመለሰ በኃላ በሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሙሉ 90 ደቂቃዎችን መሰለፍና መጫወት ችሏል።

ሞሪንዎ እንደሰጡት ፍንጭ ከሆነ ደግሞ አንቶኔ ማርሻል የጨዋታ መደራረብ ስላለበት ድካም ሳይሰማው አይቀርም በሚል ለጨዋታው ቄሚ ተሰላፊ ላያደርጉት እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

ምንም እንኳን ፊል ጆንስ ከጨዋታው ውጪ ቢሆንም ኤሪክ ቤይሊ ግን ከደረሰበት የ thigh injury አገግሞ እንደሚሰለፍ ይጠበቃል።



Wenger ስለ ጨዋታው: "ማን.ዩናይትዶች ጠንካራ ቡድን ናቸው። ከሚያደርሱብን ችግር ለመውጣት እንደምዘጋጅ አምናለው። ለመከላከል ብቻ ሳይሆን ለማጥቃትም ጭምር ይመጣሉ።

“አደገኛ ቡድን ናቸው። በባለፉት ጨዋታዎቻቸው ላይ ድንቅ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል። ስለዚህ እነርሱን ለማሸነፍ በድንቅ አቋማችን ላይ መገኘት ይገባናል። ማተኮር የምፈልገው ማሸነፍ ላይ ብቻ ነው።


“ሳንቼዝ መጠነኛ የhamstring ችግር ነበረበት
 – ሆኖም ለክፉ ሚሰጠው አይደለም”



ግምታዊ አሰላለፎት Predicted Line-Ups ..

አርሰናል...

ግብ ጠባቂ ፦ ፒተር ቼክ
ተከላካዮች ፦ ሞንሪያል ፣ ሙስታፊ ፣ ኮሽሌይኒ
አማካዮች ፦ ኮላሲኒች ፣ ራምሴይ ፣ ዥካ ፣ ቤለሪን
አጥቂዎች ፦ ዥሩድ ፣ ኦዚል ፣ አሌክሲስ
(ፎርሜሽን፦ 3-4-2-1)

ማንቸስተር ዩናይትድ ..

ግብ ጠባቂ ፦ ደ ሂያ
ተከላካዮች ፦ ሮሆ ፣ ስሞሊንግ ፣ ሊንደሎፍ ፣ ያንግ ፣ ቫሌንሺያ
አማካዮች ፦ ሄሬራ ፣ ማቲች ፣ ፖግባ
አጥቂዎች ፦ ሉካኩ ፣ ራሽፎርድ
(ፎርሜሽን፦ 5-3-2)

የቀቋማሪ ድርጅቶች ግምት What are the odds?

አርሰናል ያሸንፋል - 6/4
ማን.ዩናይትድ ያሸንፋል - 9/5
አቻ - 23/10

Featured Post/ቀጣይ ልጥፍ

የዝውውር ዜናዎች

  ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር...