Tuesday, October 31, 2017

ከዛሬና ነገው የቻምፒየንስ ሊጉ ጨዋታዎች በፊት የተሰሙ ዓበይት ጉዳዮች


ማስታወቂያ ...

እምር ፅድት ያሉ ፎቶዎችን የሚፈጥሩባቸው በ5ት የኤዲቲንግ አማራጮች በአይቴል S11 ስልክ ላይ ያገኙአቸዋል!


ጆዜ ሞሪንዎ በ4ት ቀናት ውስጥ ብቻ ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜ የማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎችን ተችተዋል: "በቶተንሃሙ ጨዋታ ያልተዝናናችሁ አንዳንድ ደጋፊዎች፤ በዛሬው ጨዋታ ላይ 'ዘና' ትላላችሁ"





በአራት ቀናት ውስጥ አሰልጣኙ የዩናይትድ ደጋፊዎችን ሲተቹ ለሦስተኛ ግዜአቸው ነው። ይሄንን አዲስ ትችቶች ጆዜ ሞሪንዎ በደጋፊዎቹ ላይ ያዘነቡት ደግሞ አንዳንድ ደጋፊዎች በቶተንሃሙ የ1ለ0 ድል ጨዋታ ወቅት በቡድኑ እንቅስቃሴ ደስተኞች አልነበሩም መባሉን ተከትሎ ነው።


ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ከዛሬው የኦልትራፎርድ የ4:45 ቤኔፊካ ሻምፒየንስ ሊጉ ጨዋታ በፊት በክለቡ በሚታተም የUnited Review መፅሄት ላይ በሰጡት አስተያየት ደጋፊው ላይ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል። ሞሪንዎ እንዳሉት ከሆነ...


"በቶተንሃሙ ጭዋታ ላይ ደስተኛ ያልነበራችሁ በሙሉ በዛሬው ጨዋታ ትደሰታላችሁ" በሚል በክለቡ እውቅ ከጨዋታ በፊት መፅሄት United Review ላይ የፃፉት ሞሪንዎ ደጋፊዎቹ በቶተንሃሙ ጨዋታ ላይ ለቡድኑ ሙሉ ድጋፍ አልሰጡም ሲሉም ወቅሰዋቸዋል።


"ዳጋፊዎቹ ለምን ሮሚዮ ሉካኩ ሙሉ ለሙሉ ጨዋታዎች ላይ ያለውን እየሰጠ እየተጫወተ ሳለ ድጋፋቸውን እንዳልሰጡት ቢያብራሩልኝ ደስ ይለኝ ነበር"  ሲሉ ሞሪንዎ ከጨዋታው በፊት አስተያየታቸውን በመፅሄቱ ማስፈራቸውን ቀጥለው..


"እንደማስበው በጨዋታው ላይ ጎልም አስቆጠረ ወይም አላስቆጠረ ይሄን ያህል እሚያስተች ነገር ያለ አይመስለኝም። ስላላገባ ብቻ ድጋፍ መንፈግ ተገቢ አይመስለኝም። ስለዚህ በመጠኑም ቢሆን በደጋፊው ተከፍቻለሁ። በእርሱ ግን አልተከፋሁም ደስተኛ ነኝ"


"ለኔ ሉካኩ በቡድኔ ውስጥ የሚነካ ተጭዋች አይደለም። እናም ድጋፍ ሊለየው አይገባም። ከደጋፊዎች ከበሬታ ሊቸረው ይገባል"   ሲሉ በአምስት የተለያዩ ውድድሮች ላይ ያለምንም ጎል የጨረሰውን ቤልጂየማዊ አጥቂ ትችት ተከላክለዋል።


የሮማ ደጋፊዎች በፐብ ብራውል ስፍራ ተሰባስበው በነበሩ የቼልሲ ደጋፊዎች ላይ ጥቃት አደረሱ



የቼልሲ እና ሮማ ደጋፊዎች በፐብ ብራውል በሮሙ እውቅ ኮሊሲየም አካባቢ ትላንትና ምሽት ተጋጭተዋል ሲል የዘገበው Corriere dello Sport ነው።


የጣሊያኑ ጋዜጣ አክሎ እንደዘገበው ከሆነ 40 የሚጠጉ የሮማ ደጋፊዎች ፊታቸውን በመሸፈን ጭምብል አድርገው በጣሊያኖ ዋና ከተማ ማዕከላዊ ክፍል በሚገኝ ፐብ ውስጥ በመግባት በያዙት የብረት ቁራጭ (Metal Bars) በቼልሲ ደጋፊዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ ቢያደርጉም ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ ፖሊስ ወደ ስፍራው በመድረሱ ግርግሩ በርዷል። ሁለት የሮማ ደጋፊዎችም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።


እንደ ዘገባው ከሆነ በግጭቱ ሳቢያ ከቼልሲም ሆነ ከሮማ ደጋፊዎች ከባድ የሚባል አይነት ጉዳት ያልደረሰባቸው ሲሆን የጣሊያን እና የእንግሊዝ ኢምባሲዎች በጋራ በመሆን ተጨማሪ ግጭቶች በቻምፒየንስ ሊጉ ጨዋታው ላይ እንዳይፈጠሩ በትብብር እየሰሩ እንደሆነም ተገልፆአል።


ለምሽቱ ጨዋታ ወደ 1,750 የሚደርሱ ትኬቶች ለተቃራኒ ቡድን ቼልሲ ደጋፊዎች የተሸጡ ሲሆን እነኛ የተሸጡት ትኬቶች ዛሬ በሮሙ የPalatino Hotel ውስጥ ለፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒየኖች ቼልሲ ደጋፊዎች ይሰጣሉ ተብሏል።



የማንቸስተር ሲቲ ደጋፊዎች በናፖሊው የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ላይ የቡድናቸውን አርማ ቤልት ይዘው ስቴዲየም እንዳይገቡ ታግደዋል!





የሲቲ ደጋፊዎች በናፖሊው የስታዲዎ ሳን ፓዎሎ የነገ ምሽት የሻምፒየንስ ሊግ ወሳኝ ጨዋታ ላይ የቡድናቸውን አርማ ቤልት ይዘው በስቴዲየም እንዳይገቡ በናፖሊ ተከልክለዋል።


ደጋፊዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የቡድኑ አባላት ስታፎችና የሚዲያ ሰዎችም ይሄንን ቤልት በቻምፒየንስ ሊጉ ጨዋታ ምሽት ወደ ሜዳው ይዘው እንዳይመጡ ከወዲሁ ታግደዋል። ያም ሆኖ እገዳው በማንቸስተር ሲቲ ተጭዋቾች እና አሰልጣኙ ፔፕ ጋርዲዮላ ላይም ጭምር ይስራ አይስራ የታወቀ ነገር የለም።


ለእገዳው መንስኤ የሆነው ድርጊት የተፈጠረው የናፖሊ ደጋፊዎች በባለፈው ኦክቶበር 17ቱ ጨዋታ ላይ ወደ ኢትሃድ ስቴዲየም በመጡ ሰአት አንዳንዶቹ በያዙት የክለቡ አርማ ቤልት የሲቲ ደጋፊዎችን ሳያስቡት 'ከኃላ በማነቅ' በፈጠሩት ግርግር እና ጥቃት ሳቢያ ነው።


በወቅቱ በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ቢያስ በሦስት ደጋፊዎች ላይ ጉዳት የተከሰተ ሲሆን አንድ የናፖሊ ደጋፊ በበኩሉ ወደ እስር ቤት ካመራ በኃላ ለአምስት ወራት ያህል ምንም አይነት እግርኲስ ጨዋታዎችን እንዳይመለከት እገዳ ተጥሎበታል። ያም ሆኖ የማንቸስተር ክለብ ደጋፊዎች ጀነራል ሴክሬተሪያት Kevin Parker እንዳሉት ከሆነ ከGroup F የነገው ምሽት ምድብ ጭዋታ በፊት የተጣለውን የናፖሊዎች የቤልት እገዳ እርባና ቢስ "ridiculous" ሲሉ በማጣጣል ገልፀውታል።


ፓርከር እንደተናገሩት ከሆነ: "በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊጉ ጨዋታዎች ላይ በሲቲ ላይ ሁሌም እገዳዎች አሉ። በመጀመሪያ በጨዋታዎች ላይ ተቃውሟችንን እንዳንገልፅ (booing) ታገድን። በሁለተኛው ከስቴዲየም ታገድን። አሁን ደግሞ የክለባችንን አርማ ቤልቶች እንዳናደርግ ታግደናል" ሲሉ ሁኔታውን በምሬት ገልፀውታል።

 ዛሬ ምሽት በሻምፒዮንስ ሊግ የሚደረጉ ጨዋታዎች፦



⬛ ምሽት 3:45 ላይ ወደ ጣሊያን በመጓዝ የአንቶኒዮ ኮንቴ ስብስብ የሆነው ቸልሲ ከ ሮማ ጋር ይፋለማሉ።

⬛ ፒኤስጂ በሜዳው አንደርሌክትን ምሽት 4:45
ላይ ይገጥማል።

⬛ ባርሴሎና ከሜዳው ውጪ ምሽት 4:45 ላይ
ኦሎምፒያኮስን ይገጥማል።

⬛ ማንችስተር ዩናይትድ በኦልትራፎርድ ምሽት 4:45 ላይ ቤነፊካን ይገጥማል።

⬛ የብሬንዳን ሮጀርስ ስብስብ ሴልቲክ በሜዳው
የጀርመኑን ክለብ ባየርሙኒክን 4:45 ላይ ይገጥማል።

⬛ ባዜል በሜዳው የሩስያውን ክለብ ሲኤስኬ ሞስኮን ምሽት 4:45 ላይ ይገጥማል።

⬛ አትሌቲኮ ማድሪድ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ካራባግን 4:45 ላይ ይገጥማል።

⬛ የጣሊያኑ ክለብ ጁቬንትስ ወደ ፖርቹጋል በማቅናት ስፖርቲንግ ሊዝበንን ምሽት 4:45 ላይ ይገጥማል።

Monday, October 30, 2017

ሰኞ ምሽት ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



PSG SET SIGHTS ON COUTINHO

ፒኤሲጂ ለኮንቲኒሆ €200 million ሊያቀርብ ነዉ።

ፊሊፕ ኮንቲኒሆ ወደ ፒኤሲጂ መሄድ አልፈልግም ቢልም እንኮን ፒኤሲጅወች ተስፋ በለመቁረጥ በድጋሜ የእናስፈርም ጥያቄ ሊያቀርቡለት ነዉ።

የሊቨርፑሉ የጨዋታ አቀጣጣይ የሆነዉ ብራዚላዊዉ ፊሊፕ ኮንቲኒሆን በቀጣዩ ክረምት የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤሲጂ ለማስፈረም ከሊቨርፑል ባለስልጣናት ጋር ንግግር ሊያደርጉ ነዉ።

ፒኤሲጂ ብራዚላዊዉን ኮከብ ከሀገሩ ልጅ ኔይማር ጁኔር ጋር ለማጣመር ሲል ሁለተኛ ጥያቄ ለኮንቲኒሆ ሊያቀርቡ ተዘጋጅተዋል። ኮንቲኒሆ ግን በጥር የካታሎኑን ክለብ ባርሴሎና መቀላቀል እንደሚፈልግ ተናግሮል።     (the sun)


ARSENAL MISS OUT ON LEMAR

አርሰናል ፈረንሳዩን የሞናኮዉን አማካኝ ቶማስ ሌማርን በጥር ከሚያዛዉራቸዉ ተጫዋቾች መካከል ዉጭ ሊያደርገዉ እንደሆነ እየተዘገበ ነዉ።

ምክንያቱ ደግሞ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በክረምቱ የዝውውር መስኮት ተጫዋቹን ለማስፈረም ቢጥሩም እንኮን ሳያስፈርሙት ቀርተዋል። በዚህም አርሰናሎች ፊታቸዉን ወደ ሌላ ተጫዋች ሊያዞሩ እንደሆነ በመታወቁ አርሰናሎች ሌማርን ከእቅዳቸዉ ዉጭ ማድረጋቸዉ አይቀርም ተብሎል።   (daily mirror)


THREE CLUBS EYE CARRICK

የ36 አመቱ የማንችስተር ዩናይትድ አማካኝ እንዲሁም አንበል(capitan) ማይክል ካሪክ በተለያዩ የእንግሊዝ ክለቦች አይን ዉስጥ ገብቶል።

ካሪክ በአሁኑ 2017 አመት የእንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ እስካሁን ለክለቡ ተሰልፍ አልተጫወተም።

በክለቡ ማን ዩናይትድ የመሰለፍ እድል ማጣቱን ተከትሎ በጥር ተጫዋቹን ለማስፈረም ዌስትብሮሚች አልቤን፣ ሌስተር ሲቲ እና የሻምፒዩን ሽፑ ክለብ አስቶንቪላ ካሪክን ለማስፈረም ተፋጠዋል ሲል evening standard ዘግቧል።

Advertisement
ፅድት ጥርት ያሉ ምስሎችን በitel S11 ስልክ በመነሳት ከቤተሰብዎ ጋር ያሳለፉትን ትውስታዎን ያስቀሩአቸው!


LIVERPOOL WANT CASILAS

ሊቨርፑል አንጋፋዉን ግብ ጠባቂ ስፔናዊዉን አይከር ካስሊያስን የማስፈረም ሰፊ እድል አለዉ ተባለ።
ካስሊያስ በአሁኑ ሰአት ለፖርችጋሉ ክለብ ለሆነዉ ለፖርቶ በመጫወት ላይ ይገኛል።

በዚህም ሊቨርፑል በጥር ለማዛወር በቂ እድል አለዉ ተብሎል። ሊቨርፑል ካስሊያስን በነፃ ዝውውር ሊያመጣዉ ይችላል በማለት bbc ዘግቧል።

ትናንት ምሽት በላሊጋዉ ወደ ካታሎን ግዛት አቅንቶ ጌሮናን የገጠመ ሪያል ማድሪድ 2፣1 ሲሸነፍ አጥቂ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በጊሮናዉ ተጫዋች ላይ ያልተገባ በሀሪ አሳይቶል። በዚህም በላሊጋዉ ለሁለተኛ ጊዜ ቅጣት ሊጣልበት ይችላል ተብሎል።

በሮናልዶ ጉዳይ ላይ የላሊጋዉ ምላሽ ዛሬ ምሽት ይታወቃል ተብሎል።    (sky sport)



MANGALA TO MILAN?

የማንችስተር ሲቲዉ ተከላካይ ኢልኩሚ ማንጋላ በሴሪያዉ ክለብ ኢንተር ሚላን ይፈለጋል።

ማንጋላ በማንችስተር ሲቲ የመሰለፍ እድል እያገኘ አለመሆኑ ተከተሎ ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግ ይታዉቆል።

ኢንተር ሚላንም ልጁን በጥር የዝውውር ጊዜ ለማስፈረም እንደሚፈልጉ ለሲቲወች ነግሮቸዋል።   (done deal)



GUNNERS TARGET JORGINHO

ምሽቱን በወጣ ዜና መድፈኞቹ ከ ብራዚላዊዉ አማካኝ  ጆርጊንሆ ላይ አነጣጥረዉበታል።

የሴሪያዉ ክለብ ናፖሊ አማካኝ የሆነዉ ጆርጊንሆ አርሰናል ባለስልጣናትን እንደሳባቸዉ እየተነገረ ነዉ።

አማካኙን ወደ ኢሜሬትስ በማስኮብለል ለማስፈረም አርሰናል የጥር የዝውውር ጊዜን ወይንም ቀጣዬ ክረምት እየተጠባበቁ ነዉ ሲል marca ዘግቧል።


OTHER SHORT STORIES

አስቶን ቪላ፣ ዌስት ብሮም እና ሌስተር ሲቲዎች የማንቸስተር ዩናይትዱን አምበል ማይክል ካሪክ ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው።   (Source: Daily Mirror)


ኢዲ ኒኪታህ በአርሰናል የሚያቆየውን አዲስ የአምስት አመት ኮንትራት ሲፈራረም ሳምንታዊ ደሞዙን ወደ 650% ጭማሪ ይደረግለታል። (Source: Sun on Sunday)


DEAL DONE: ፌዴሪኮ ፋዚዎ አዲስ የሦስት አመት ኮንትራት በሮማ ፈርሟል። (Source: ASRomaEN)



የማንቸስተር ሲቲው ቤልጂየማዊ አማካይ ኬቨር ዲ ብሪየን አዲሱን ሳምንታዊ £250,000 የሚያስገኝለትን ደሞዝ ሲፈራረም የክለቡ የምንግዜም ከፍተኛው ተከፋይ ተጫዋች ይሆናል።
(Source: Daily Star)


ባርሴሎናዎች ለአትሌቲኮ ማድሪዱ አጥቂ አንቶኔ ጋሬዝማን ዝውውር በክረምቱ የ£89m ሂሳብ ለማቅረብ ዝግጁ ናቸው።   (Source: Mundo Deportivo)



ማንቸስተር ዩናይትዶች ማርከስ ራሽፎርድን ለሪያል ማድሪድ በመሸጥ በምትኩ ማርከስ አሴንሶን ከሎስ ብላንኮዎቹ መውሰድ ይፈልጋል።  (Source: Daily Express)

Sunday, October 29, 2017

እሁድ ከሰአት በኃላ ላይ የወጡ ሰፋ-ያሉ በርካታ ተጭዋቾችንና ክለቦችን የተመለከቱ የዝውውር ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎች አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ ወሬዎች! Latest News Updates



MOURINHO'S FELLAINI CONCERN

ጆዜ ሞሪኖ ስለ ማሩዋን ፌላኒ ኩንትራት ተጠይቀዉ አሁን ኩንትራቱ አልጨረሰም ኩንትራቱ በክረምቱ ነዉ የሚያበቃዉ፣ እስከዛ ባለዉ ከሱ ጋር አዲስ ኩንትራት ለማስፈረም ንግግር አደርጋለን።

ጨምረዉም ጆዜ ስለ ሉክሸዉ ሲጠየቁ እኔ ስለሱ ምንም ማዉቀዉ ነገር የለም ብለዋል።   (sky sport)


በዘመናዊው አይቴል S11 ስልክ ህይወትዎን አኗኗርዎን ቀለል ያድርጉ!

PASTORE ON THE MOVE?

ጃቪየር ፓስትሮይ በጥሩ የዝውውር መስኮት ክለቡን ፓርሴን ጀርሜን በመልቀቅ ወደ ሌላ ክለብ ማምራት ይፈልጋል ተብሎል።

የመልቀቁ ምክንያት ደግሞ በፒኤሲጂ በቂቦታ መግኝ አለመቻሉ ነዉ። በክረምቱ የዝውውር ጊዜ ፒኤሲጂ ኔይማር ጁኔርን ከባርሴሎና ኬሊያን ሞፓፔን ከሞናኮ በማስፈረሙ ቦታዉ በሁለቱ ኮክብት በመያዙ የመሰለፍ እድሉ አንሶል።

አርጀንቲናዊዉ አጥቂ በዚህም ምክንያት ክለብ መልቀቅ እንደሚፈልግ ታዉቆል።   (bbc)


'SPURS WANT  GOMES'

ቶተንሃም ከባርሴሎናዉ አማካኝ አንድሬ ጎሜዝ ላይ አነጣጥሮል።

ፖርቹጋላዊዉ አማካኝ ጎሜዝ በባርሴሎና ከመቀመጫ ወንበር ተነስቶ ወደ ሜዳ መግባትን አልመዉደዱ ክለቡን የመልቀቁ ጉዳይ እዉን እንደሚሆንላቸዉ ለቶተንሃሞች ልጁን ለማስፈረም ጥሩ እድል ነዉ እየተባለላቸዉ ይገኛል።

በዚህም ጎሜዝ በሴሪያዉ ክለብ ጁቬንትስም ይፈለጋል። ሁኖም ቶተንሃም ከጁቬንትስ ልጁን ለማስፈረም ትልቅ ፈተና ይገጥመዋል ተብሎል።    (mundov deportivo)

MASCHERANO TO LEAVE?



የቀድሞዉ የቀዩቹ ሊቨርፑሎች የተከላካይ አማካኝ የአሁኑ የባርሴሎና ተጫዋች የሆነዉ አርጀንቲናዊዉ ጃቪየር ማሻራኖ ስለወደፊት ነገር ከአሁኑ ልናገር አልችልም ምክንያቱም አለ እኔ በባርሴሎና ደስተኛ ነኝ፣ በባርሴሎና ከተማ በዙ ግዜ ቆይቻለሁኝ፣ እስካሁን ከክለብ አጋሮቸ ጎደኞቸ ጋር በጣም በፍቅር ቆይተናል።

የአሁኑን አመት ሲዝን  በድል ለማሳለፍ ከአሁኑ ጠንክረን እየሰራን ነዉ። በተለይ ከሀገሬ ልጅ ሊዩነል ሜሲ ጋር በመጫወቴ ከህይወቴ ስኬቶች መካከል አንዱ ነዉ ብሎል።

ማሻራኖም በመጨረሻም እኔ ስለ ወደፊቱ ጊዜ ግድ የለኝም በማለት ሳቅ በሞላዉ ንግግሩ ተናግሮል። ማሻራኖም የአስተያየት መቆጫዉ ላይ ላደረጉለት አስተያየት ራዲዩ 5 አመስግኖል።   (marca)


COUTINHO UPDATE


ኮንቲኒሆ ወደ ባርሴሎና ዝውውሩን ጨርሶል እየተባለ ነዉ። ፊሊፕ ኮንቲንሆ ሊቨርፑል በ€150 million ለባርሴሎና ሽጦታል የሚሉ ዜናወች ተበራክተዋል። ጉዳዩ በግልፅ ባይታወቅም ባርሴሎና ኮንቲኒሆን አዘዋዉሮል ተብሎል።

ጉዳዩም በግልፅ በቅርቡ ይፋ ይሆናል ተብሎል ሲል AS ዘግቧል።


MAN UTD EYE MEUNIER



ማንቸስተር ዩናይትዶች £30 million ሂሳብ ወጪ በማድረግ የፓሪሰን ዥርሜዩን ተመላላሽ ተከላካይ ቶማስ ሚውነርን ለማዛወር አቅደዋል ብሏል Sunday Express ጋዜጣ።

ሙኒየር ባፓርክ ደ ፍራንስ ዳኒ አልቬስ ክለቡን ከተቀላቀለ በኃላ በቋሚነት የመሰለፍ እድል ተነፍጎታል።

እናም ጆዜ ሞሪንዎ የቤልጂየሙ ኢንተርናሽናል የረጅም ጊዜ አድናቂ በመሆናቸው በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ወደ ኦልትራፎርድ ሊያዛውሩት ፈልገዋል።


NO MAN CITY MOVE FOR ALEXIS IN JANUARY



ማንቸስተር ሲቲዎች አሌክሲስ ሳንቼዝን ለማዛወር በጥሩ የዝውውር መስኮት ላይ ምንም አይነት ጥያቄ አያቀርቡም ፤ ይልቁንም በነፃ የዝውውር ሂሳብ በቀጣዩ ክረምት ሊያመጡት ጥረት ያረጋሉ ያለው የDaily Mirror ዘገባ ነው።

ሲቲዎች የ28 አመቱን አጥቂ ባለፈው ክረምት ሊያዛውሩት ሙከራ አድርገው ያቀረቡት የ£60 million ሂሳብ በመድፈኞቹ ውድቅ ተደርጎባቸዋል።

በቅርቡ በተሰሙ ሪፖርቶች መሰረት የፔፕ ጋርዲዮላው ቡድን ቺሊያዊውን አጥቂ ለማስፈረም በጥሩ የዝውውርች መስኮት ላይ ጥያቄ ያቀርባል ተብሎ ቢጠበቅም ሲቲዎች በክረምቱ ዝውውር ድርድር ወቅት አርሰናሎች ባሳዮአቸው ድርቅ ያለ አቋም ደስተኛ አልነበሩም ሲል ሚረር ዘግቧል።


ARSENAL & MAN UTD CHASE BARCA WINGER



ማንቸስተር ዩናይትድ እና አርሰናሎች የባርሴሎናውን የክንፍ መስመር ተጫዋች ጆዜ አርናይዝን ማዛወር ይፈልጋሉ ሲል Mundo Deportivo ዘግቧል።

አርናይዝ ባርሴሎናን በክረምቱ የተቀላቀለው ከሪያል ቫላዶሊድ ሲሆን እስካሁን እየተጫወተ ያለው በባርሴሎና ቢ ቡድን ውስጥ ነው። ያም ሆኖ በኢርኔስቶ ቫልቫርዴ ባሰለፉት የመጀመሪያ ጨዋታው ላይ ሪያል ሙርሲያ ላይ በኮፓ ዲ ላሬይ ጎል አስቆጥሮአል።

ተጭዋቹ ባሁን ሰአት የ€20 million ውል ማፍረሻ ሂሳብ አንቀፅ ኮንትራቱ ላይ ያለው ሲሆን አርሰናል እና ማንቸስተር ዩናይትዶች ከባየር ሙኒክ ጋር በመሆን የአርናይዝን እድገት በቅርበት እየተከታተሉት ይገኛሉ።


LIVERPOOL PLAN €25M LEFT-BACK BID



ሊቨርፑሎች በ€25 million ሂሳብ የሮማውን ግራ ተመላላሽ ኤመርሰን ፓልሜሪን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለማዛወር ጥያቄ ሊያቀርቡለት ተዘጋጅተዋል ብሏል GazzaMercato.

ፓልሜሪ አሁን ከደረሰበት የጉልበት ጉዳት እያገገመ ሲሆን ሊቨርፑሎች በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ጥያቄ ያላቀረቡለት ምን ያህል እንደሚያገግም ለማየት ነበር። ምንም እንኳን ሙሉ ለሙሉ ባይሻለውም አሁንም ብራዚላዊው የየርገን ክሎፕ የዝውውር ኢላማ ነው።

Friday, October 27, 2017

ማንቸስተር ዩናይትዶች ቶተንሃምን በኦልትራፎርድ አጥቅተው ይጫወቱ ይሆን ወይንስ ላለመሸነፍ ብቻ ይገባሉ?

✔  ማንቸስተር ዩናይትዶች ቶተንሃምን በኦልትራፎርድ አጥቅተው ይጫወቱ ይሆን ወይንስ ላለመሸነፍ ብቻ ይገባሉ?


ቶተንሃሞች ባለፈው ዲሴምበር ወር ላይ ወደ ኦልትራፎርድ መጥተው ሲሸነፉ ሽንፈታቸው በሜዳው ካደረጔቸው ስምንት ተከታታይ ጨዋታዎች የመጀመሪያው ነበር። ይሄ ሪከር



ታሪክ ባለፈው የአንፊልዱ ጨዋታ ላይም ሊቨርፑሎች የዩናይትዶችን ተከታታይ 6ት ጨዋታዎችን የማሸነፍ ሪከርድ አቻ በመውጣት ሲያቋርጡት ታይቷል። በእለቱ ቡድኑ አሰልቺ እና ሳቢ እግርኳስን አለመጫወቱን ተከትሎ የቡድኑ ተጭዋቾች ሳይቀሩ የጠሉት ቢሆንም የአሰልጣኙን ታክቲክ የመተግበር ግዴታ ስላለባቸው ብቻ ግን እየጠሉትም ቢሆን ተጫውተዋል።



ከዛ ቀን አቻ ውጤት በኃላ ቡድኑ በሊዝበን 1ለ0 አሸንፎ በትንሹ ሃድስፊልድ 2ለ1 ከተረታ በኃላ የጆዜ ሞሪንዎ የቁጣ ጩሃት በተጭዋቾቹ መልበሻ ክፍል ውስጥ እንዲሰማ አድርጔል። ደጋፊዎቹም ቢሆኑ በፖርቹጋላዊው አለቃ አጨዋወት ላይ ለመጀመሪያ ግዜ ጥያቄ ማንሳት ጀምረዋል።



ምንም እንኳን ቡድኑ ፖል ፖግባ፣ ኤሪክ ቤይሊ እና ማርዋን ፌላይኒ የመሳሰሉ ቁልፍ ተጭዋቾቹን በጉዳት ሳቢያ ቢያጣም በሊጉ ካደረጔቸው ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች አንድ ጎል ብቻ ብልስቆጠሩት ሃድስፊልዶች ሁለት ጎል አስተናግደው መሸነፋቸው ድንጋጤን መፍጠሩ ግልፅ ነው።



በማክሰኞው የ Carabao Cup ድል ላይ ቡድኑ ማሽነፍ መቻሉ መልካም ሲሆን ጄሲ ሊንጋር ያስቆጠራቸው ግሩም ጎሎች፣ ታዳጊዎቹ አሌክስ ትዋንዜቤ እና ስኮት ማክቶሚናይ ያሳዩት ጥሩ እንቅስቃሴ ቡድኑ ላይ ተስፋ የሚዘራ ቢሆንም ቶተንሃሞች ግን ከባድ ተጋጣሚዎች እንደሚሆኑባቸው እርግጥ ነው።

እንደ ዩናይትዶች ሁሉ 20 ነጥቦችን በመሰብሰብ በሊጉ አንድ ደረጃ አንሰው የተቀመጡት ቶተንሃሞች በማጥቃት እንቅስቃሴ የሚጫወቱ ቡድን መሆናቸው በሊቨርፑሉ ጨዋታ ታይቷል። ሁለቱ ቡድኖች ባለፈው አመት ላይ በማንቸስተር ሲገናኙ ጆዜ ሞሪንዎ ፖቼቲንዎ ከኔ በተሻለ ቡድኑ ውስጥ በመቆየቱ የሚፈልገውን ቡድን ሰርቶ የመጣ አሰልጣኝ ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረው ነበር።



✔ ተጠባቂው ነገር: ማን.ዩናይትዶች በሜዳቸው እንደሚጠበቀው አጥቅተው ይጫወቱ ይሆን? ወይስ ጆዜ ሞሪንዎ አምና በሊጉ በ17 ነጥቦች በልጦአቸው የጨረሰው ቡድንን ተከላክለው ነጥብ ይዘው ለመውጣት ይገባሉ?




ፖቼቲንዎ በኦልትራፎርድ ያሉ በርካታ አድናቂዎች አሏቸው። ከነዛ መሃከልም አንዱ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ናቸው። አርጀንቲናዊው አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ(ምንም እንኳን ቢያስተባብሉትም) ዩናይትድን በመልቀቅ ወደ ፈረንሳዩ ሃብታም ክለብ ፒ.ኤስ.ጂ ካቀኑ ፖርቹጋላዊውን በመተካት የዩናይትድን  አሰልጣኝነት መንበር ለመረከብ ቀጣዩ ግለሰብ ናቸው በሚል ስማቸው በድጋሚ ከዩናይትድ ጋር ተያይዟል።



በኃላ ላይ ሞሪንዎ በFrench television ጣቢያ ላይ ቀርበው ቀልጣፋ በተባለ ንፁህ ፈረንሳይኛ ቋንቋ አቀላጥፈው እየተናገሩ ቃለ መጠየቃቸው ላይ ወሬው ሃሰት መሆኑን አጣጥለውታል። ሆኖም ይሄ የጆዜ ሞሪንዎ መለያ በሃሪ ነው። ያም ቢሆን የዩናይትድ ደጋፊዎች ቡድናቸው ነገ በሜዳው ልክ ይ8ሊቨርፑሉ አይነት አሉታዊ የመከላከል ታክቲክ ይዘው ቢገቡ ጆዜ ሞሪኖዎ ክለባቸውን ለቀው እንዲሄዱ ተቃውሞ የሚያሰሙበት በቂ ምክንያት ያላቸው አይመስልም። ሰውዬው የኦልትራፎርዱን መርከብ አነዳድ በሚገባ አጥንተውታል፤ አምና ዋንጫዎችን አሸንፏል እንዲሁም በዝውውር ገበያው ላይ ጥሩ ግዢዎችን ለክለቡ ፈፅመዋል። ከሊቨርፑሉ በተሻለ በነገው ወሳኝ ጨዋታ ላይ ጥንቃቄ የተሞላበት አልፎ አልፎ የማጥቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ጨዋታ እንደሚሆን ይጠበቃል።


ሞሪንዎ የቡድኑ ቁልፍ ተጭዋቾች ባሌሉበት ጨዋታዎች ላይ ይታደጉኛል ያሏቸውና ወጥ የሆነ አቋም ማሳየት የተሳናቸውን ተጨዋቾቻቸውን መተቸታቸው አግባብ ይመስላል። አሰልጣኙ ማን.ዩናይትድን ለሚያክል ትልቅ ክለብ ስትጫወት በወር አንድ ግዜ ምርጥ አቋምህን አሳይተህ መዝናናት ሳይሆን በየጨዋታዎቹ ላይ ከ10/8 ነጥቦች የሚያሰጥህ እንቅስቃሴ የምታሳይ፤ ቢያንስ በየ10 ጨዋታዎች 8ንቱ ላይ አቋምህ ሳይወርድ መጫወት ያለብህ ተጭዋች መሆን እንዳለባቸው እንደሚያምኑ በግልፅ ተናግረዋል። ለዛም ይመስላል እንደነ ሄነሪክ ሚኪተሪያን፣ ሁዋን ማታ እና አንደር ሄሬራ የመሳሰሉ ተጭዋቾቻቸውን የተቹት። አሁንም የግራ ተመላላሽ ቦታቸው ችግር እንዳለ ነው።



ማን.ሲቲዎች ያሉበት ድንቅ አቋም የዩናይትዶችን ትንሽ ችግር ጎልቶ እንዲወጣ በማድረግ በኩል አጋልጧቸው ይሆናል። ሆኖም በክለቡ ጥሩ ነገር እንዳለ ይታያል።



ዩናይትዶች የዛሬ አመት አምና በዚህ ሰአት ካሳዩት አቋም እጅግ የተሻለ ቡድን መገንባታቸው መልካም ነገር ነው። ይሄም አሁን በያዙት ደረጃ፣ በሰበሰቡት የነጥቦች ብዛት፣ ባስቆጠሩት ጎሎች ብዛት እና በተቆጠረባቸው አነስተኛ ጎሎች የሚገለፅና የሚታይ ሆኖአል። በቻምፒየንስ ሊጉ ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎችን ማሸነፋቸውም ሌላው ሊጠቀስ የሚገባው ጥሩ ነገር ነው። ሆኖም የነገውን ጨዋታ ጨምሮ ከባባድ ጨዋታዎችን ጥሩ በመጫወት ማሸነፍ የማይችሉ ከሆነ የቡድኑ በራስ መተማመን ሊወርድ ይችላል። ዩናይትዶች ባለፈው ሲዝን ላይ ስፐርስን በሜዳቸው ከጥሩ ጨዋታ ጋር 1ለ0 አሸንፈው ነበር። ነገም ይሄንን መድገም ይጠበቅባቸዋል።


✔   ሃሪ ኬን በደረሰበት መጠነኛ የሃምስተሪንግ ጉዳት ሳቢያ ከጨዋታው ውጪ ሆኑአል



ሃሪ ኬን ክለቡ ባለፈው ሳምንት ላይ ከሊቨርፑል ጋር ባደረገው ጨዋታ ላይ በደረሰበት የሃምስተሪንግ ጉዳት ሳቢያ ለነገው የምሳ ሰአት ጨዋታ እንደማይደርስ ተረጋግጧል።



ኬን ክለቡ በዌምብሌይ 4ለ1 ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ በመጨረሻዎቹ ሁለት ደቂቃዎች ላይ ተቀይሮ እንዲወጣ የተደረገ ሲሆን ከጨዋታው መጠናቀቅ በኃላ ሞሪሲዮ ፖቼቲንዎ ሲጠየቁ ግን 'ስለደከመው ነው የቀየርነው' በሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር።



ሆኖም ኬን ክለቡ ያደረገውን የካራቦን ካፕ ዌስትሃም ዩናይትድ 3ለ2 ሽንፈት ጨዋታ ላይ ሳይሰለፍ ቀርቶአል። አሁን ደግሞ ለኦልትራፎርዱ ወሳኝ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ላይ የመሰለፉ ተስፋ ሙሉ ለሙሉ ያከተመ መስሏል።



ፖቼቲንዎ ስለ ጨዋታው ተጠይቀው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዲህ ብለዋል:

"ለነገው ጨዋታ ሃሪ ኬንን በማሰለፍ ሪስኩን መውሰድ አንፈልግም። ጉዳቱ የሚካበድ አይደለም። ኬንን ለሪያል ማድሪዱ የመልስ ጨዋታ ከደረሰልን የምናየው ይሆናል። ለነገው ጨዋታ ግን አይታሰብም። የነገውን ጨዋታ አያደርግም"  ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።


ቶተንሃሞች ከሁለተኛው ማንቸስተር ዩናይትዶች በእኩል 20 ነጥብ በጎል ክፍያ ተቀድመው ሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።


ፖቼቲንዎ አክለውም የሃሪ ኬን አለመኖር በቡድናቸው እንቅስቃሴ ላይ ተፅህኖ እንደማይኖረውና ቡድናቸው በአንድ ግለሰብ ላይ ጥገኛ ሳይሆን በቡድን እንቅስቃሴ ላይ መሰረት ያረገ ስለመሆኑ ተናግረዋል።

"እምናምነው በቡድን ስራ ነው። እስከ ሲዝኑ መጠናቀቂያ ድረስ ቡድንህ የተለያዩ ችግሮች ይገጥሙታል። በቡድን ያሉ ሁሉንም ተጫቾች ማመን ይጠበቅብኛል። እነርሱ ማሽን እንዳልሆኑም ነግሬአቸዋለሁ"


"ዩናይትዶች ወደ ጨዋታው የሚገቡት ከኛ በተሻለ አንድ ቀን እረፍት አድርገው ነው። ለዝግጅትና ልተጨማሪ ጉልበት ይረዳቸዋል። እኛም ከዩናይትዱ ጨዋታ በኃላ ሪያል ማድሪድ እና ክሪስታል ፓላስን ስለምንገጥም ከባድ ጨዋታዎች ከፊታችን ይጠብቁናል"   ሲሉ ምናልባትም በኦልትራፎርድ ጥንቃቄ የተሞላበት ጨዋታ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

Thursday, October 26, 2017

ሃሙስ ምሽት ላይ የወጡ ሠፊ የዝውውር ዜናዎች፣ አስተያየቶች እና ሌሎችም አጫጭር ትኩስ የእግር ኳስ መረጃዎች



¤   የቼሊሲዉ አሰልጣኝ አንቶኒዩ ኮንቴ ታዳጊዉ ተጫዋች ብራዚላዊዉ ቻሪሊን ሞሶንዳን በጥር የዝዉዉር መስኮት ላይ ለሌላ ክለብ አሳልፈዉ ለመስጠት ለሽያጭ አቅርበዉታል ሲል London Evening Standard ዘግቧታል።




¤   ማንችስተር ዩናይትድ የቦርሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ማርኮ ሬዩስን በክለቡ ዶርትመንድ እስከ ፈረንጆች 2019 ያለዉን የኩንትራት ጊዜ በማቆረጥ በጥር የዝውውር መስከት ማስፈረም ይፈልጋሉ ተባለ። ማርኮ ሬዩስ በአሁኑ ሰአት በጉዳት ምክንያት ክለቡን ቦርሲያ ዶርትመንድ እያገለገለ አይደለም።   (star)



¤   VALVERDE TERGETS NEW DEFENDERS


የባርሴሎናዉ አሰልጣኝ ኤርኔስቶ ቫልቬርዴ አዲስ ተከላካይ ማስፈረም ይፈልጋሉ ተብሎል።

ምክንያቱም የባርሴሎና የተከላካይ ክፍል መዳከሙ እና በተከላካይ ክፍሉ ያሉ ተጫዋቾች አቆም መቀነስ ነዉ ተብሎል።

ቫልቬርዴሜ በአሰልጣኝ ጆሲ ኤኒሬኬ ከተተኩ በሆላ በክረምቱ የዝውውር ጊዜ ሁነኛ ተከላካይ ማስፈረም አልቻሉም። ሁኖም በጥር የዝዉዉር ጊዜ የተከላካይ ክፍላቸዉ ለማጠናከር ብለዉ የግራ መስመር ተመላላሽ የሆነዉን ኢንጎ ማርቲኔዝን  ቀዳሚ የክለባቸዉ ተመራጭ ተጫዋች አድርገዉታል።

ሁኖም ቫልቬርዴ የጥር የተጫዋቾች የዝዉዉር መስኮት ላይ ልጁ ለማስፈረም ከአሁኑ ስራቸዉን ጀምረዋል በማለት፣metro. ጋዜጣ ዘግቧታል።

በተያያዘ ዜና ባርሴሎና በመጪዉ ክረምት ኮሎንቢያዊዉን ተከላካይ ዬርይ ሚናን ለማስፈረም ከልጁ ጋር ንግግር እያደረጉ ነዉ ተባለ።   (metro)


¤   BUFFON'S RETIREMENT PLANS


አንጋፋዉ ጣሊያዊዉ የጁቬንትሱ ግብ ጠባቂ ጁሊጂያን ቡፎን ስለወደፊቱ እቅዱ ተናግሮል።

ቡፎን በአስተያየቱም እንዲህ አለ፦ እኔ በአሁኑ አመት ከክለቤ ጁቬንትስ ጋር ታላቁን ዋንጫ የአዉሮፓ ሻምፒዩንስሊግን የማላነሳ ከሆነ በአሁኑ የ2018 የሩሲያ የአለም ዋንጫ በሆላ እራሴን ከእግር ኮስ አከላለዉ በማለት በባሎንዶር ሽልማት ዝግጅት ላይ በተደረገለት የአጭር ቀለ መጠየቅ አስተያየቱን ሰጦል።

አጋፋዉ ግብ ጠባቂ ቡፎን የተለያዩ ዋንጫወችን ከክለቡ ጁቬንትስ ጋር ቢያነሳም እንኮን ታላቁን ዋንጫ የአዉሮፓ ሻንምፒዩን ስሊግ እስካሁን ማንሳ አልቻለም።

ቡፎን ጨምሮም አምና ከክለቤ ጁቬንትስ ጋር የሴሪያዉን እና የኮፓ ኤታሊያን ዋንጫ በማንሳት ጥሩ ጊዜን አሳልፌለዉ ነገር ግን የሴሪያዉን ዋንጫ ማንሳት ብቻ ለእኔ በቂ አይደለም በማለት ተናግሮል።    (done deal)


¤   REUS: FOUR OR FIVE CLUBS WANT ME


የቦርሲያ ዶርትመንዱ አጥቂ ጀርመናዊዉ ኢንተርናሽናል ማርኮ ሬዩስ በተለያዩ አምስት ክለቦች ይፈለጋል ሲል፣ mirror ዘግቧል።

ከክለቦቹ መካከል አርሰናል፣ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ሪያል ማድሪድ እና በባየር ሙኒክ ይገኙበታል ተብሎል።     (mirror)


¤   LIVERPOOL WILL SELL COUTINHO FOR €150M


ብራዚላዊዉ የሊቨርፑሉ ኮከብ ፊሊፕ ኩቲንዎ ወደ ስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና በጥር መሄዱ እርግጥ መስሎል እየተባለ ነዉ።

የጀርገን ክሎፑ ሊቨርፑል በተጨዋቹ ላይ ያለዉ እምነት መቀነሱ ታዉቆል። ምክንያቱም በክረምቱ የዝዉዉር ጊዜ ኮንቲኒሆ ወደ ባርሴሎና መሄድ
እንሚፈልግ በግልፅ መናገሩ እና ብራዚል በአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ላይ ጎል ካገባ በሆላ ማልቀሱ ወደ ባርሴሎና የመሄድ ፍላጎቱ ከፍተኛ እንደሆነ መታወቁ ልጁ ባርሳን በጥር መቀላቀሉ አይቀርም ሲባል መቆየቱ ይታወቃል።

ሁኖም ባርሴሎና አሁን ኮንቲኒሆን በ150 million እናስፈርም ሊሉት ተዘጋጅተዋል በማለት የስፔኑ ታማኝ ጋዜጣ mundov deportivo ዘግቧል።

በመሆኑም ሌላኛዉ የማስፈረም ፍላጎት ያለዉ ፒኤሲጂ ኮንቲኒሆን ልቀቁልን በማለት ለባርሴሎና ነግሮቸዋል ሲል mundov deportivo አክሎ ዘግቧል።


¤   ማንችስተር ዩናይትድ ተዘጋጅተዋል በ£30 million የቫሌንሴዉን ካርሎስ ሶሌርን ለማስፈረም ሲል the Sun ዘገበ። ካርሎስ በእንግሊዙ ሀያል ክለብ መፈለጉ ቫሌንሴወች ልጁ ማጣታቸዉ አይቀርም ተብሎል። ምክንያቱም ካርሎስ ወደ እንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ መጦ የመጫወት ፍላጎት ስላለዉ ነው።


¤   ARSENAL WANT TO KEEP OZIL AND ALEXIS




የሰሜን የለንደኑ ክለብ አርሰናል ሁለቱን ኮከቦች ሜሴት ኦዚል እና አሌክሲ ሳንቸዝን በኢምረተስ ለማቆየት ከአሁኑ ድርድር ሊያደርግ ነዉ።

ሁለቱ ተጫዋቾች ባሳለፍነዉ ሳምንት አርሰናል ኤቨርተንን በሜዳዉ ጉዲሰን ፓርክ አስተናግዶ 5፣2 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለቱም በጨዋታዉ ላይ አንዳንድ ጎል አስቆጥረዋል።

በመሆኑም ሁለቱ ኮከቦቹ ለክለባቸዉ ያላቸዉን ወሳኝነት በጨዋታዉ ላይ አሳይተዋል።
አርሰናሎችም ሁለቱን ተጫዋቾች ለማቆየት የማይፈነቅሉት ዲንጋይ የለም ተብሎል።
(daily mirror)


¤   DRAXLER TO LIVERPOOL?



ሊቨርፑል በጥር ፊሌፔን ኮንቲኒሆን የሚያጣ ከሆነ በምትኩ ጀርመናዊዉን ኢንተርናሽናል የፒኤሲጂዉን አማካኝ ጁሊያን ድራስለርን ያስፈርማሉ ተብሎል።
የመሀል ሞተሩ ድራክስለር በፒኤስጂ በቂ ቦታ እያገኘ አለመሆኑ ክለቡን ሊለቅ ይችላል ተብሎል።

ጀርመናዊዉ ኮከብ በሀገሩ ሰዉ በሆነዉ አሰልጣኝ ጀርገን ክሎፕ መሰልጠን እንደሚፈልግ ከዚህ በፊት ተናግሮ። ክሎፕ ልጁን በጥር የዝዉዉር ጊዜ
ለማምጣት ከአሁኑ በቅርበት ሁነዉ እየተከታተሉት እንደሆነ የዜናዉ አዉታሩ daily star ዘግቧል።


¤   COUTINHO WANTS JANUARY MOVE




አሁን አመሻሽ በወጣ ሌላ ዜና ደግሞ የካታሎኑ ክለብ ባርሴሎና ከሊቨርፑል ጋር በብራዚላዊዉ ኮከብ ፊሊፕ ኮንቲኒሆ የዝዉዉር ጉዳይ ላይ ስምምነት ሊያደርግ ነዉ ተባለ።

ጨዋታ አቀጣጣዩ ፊሊፕ ኮንቲኒሆ በጥር ወደ ሚፈልግበት ክለብ እንዲሄድ አሰልጣኝ ጀርገ ክሎፕ ነግረዉታል ተብሎል። ኮከቡ በስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና የእናስፈርምህ ጥያቄ ከተጠየቀ ሰነባብቶል። በዚህም ባርሴሎና አሁን ልጁ ለማግኘት በሊቨርፑል የተጠየቁትን አዲስ የዝውውር ሂሳብ በማቅረብ ሊስማሙ ይችላሉ ሲል bbc ዘግቧል።

ፀሃፊ፦ ሙሴ አማረ
አዘጋጅ እና አርታኢ፦ መንግስቱ ደሳለኝ

አይቴል ሞባይል ኢትዮጵያ ጥቅምት 14 2010 ዓ.ም የሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበርን በመጎብኘት የተለያዩ ስጦታዎችን አበረከተ

አይቴል ሞባይል ኢትዮጵያ ጥቅምት 14 2010 ዓ.ም የሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበርን ጎበኘ፡፡




በጉብኝቱ ወቅትም አይቴል ሞባይል ለሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር መስራች ለሆኑት ለወ/ሮ ሙዳይ 20,000 ( ሀያ ሺህ ) ብር በጥሬ እና 30,000 ( ሰላሳ ሺህ ) ብር የሚያወጣ የትምህርት መሳርያ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡




በቦታዉ የአይቴል ሞባይል ብራንድ ማናጀር፣ የመገናኛ አካባቢ የአይቴል ነጋዴዎች እንዲሁም ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡





የትምህርት መሳርያ ቁሳቁስ ለ305 ተማሪዎችና መምህራን ድጋፍ ያደረገ ሲሆን አይቴል ሞባይል በያዝነዉ ወር 10ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ በጎንደር፣ ባህር ዳር እና ኮምቦልቻ ከተሞች ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ስራዎችን መስራቱ
የሚታወስ ነዉ።


 ይህን መሰሉ ሰናይ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በዕለቱ የአይቴል ሞባይል ብራንድ ማናጀር ገልፀዋል፡፡

Wednesday, October 25, 2017

Dghxddd







Report - አይቴል ሞባይል 10ኛ አመት በደማቅ ሥነ ስረዓት በኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል ተከበረ

አይቴል ሞባይል የምስረታ 10ኛ አመት ክብረ በአሏን ያለፈው እሁድ ጥቅምት 5 ላይ በደማቅ ስነስረአት በኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል አክብራለች።



እ.አ.አ በ2007 ከተመሰረተችበት ቻይና ሆንግ ኮንግ ጀምራ በመላው አለም ተቀባይነትን እያተረፈ ያለው የአይቴል ስልክ ምርቶች ድርጅት አስረኛ አመቷን በሃገራችን ኢትዮጵያ ላይም ከስኬታማ አስር አመታት በኃላ Anniversary Of Itel 2007-2017 በሚል ደማቅ ስነስረአት ተከብሮአል።

በፕሮግራሙ ላይ ቁጥራቸው ከ150 በላይ የሆኑ ባለ ድርሻ አካላት ፣ የምርት አከፋፋይ ኤጀንቶች ፣ የስታፍ አባላት ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት ባለስልጣናት ፣ የሚዲያ አካላት እና ተጋባዥ እንግዶች የተገኙበት ሲሆን ፤ ተጋባዥ የባህላዊ እና ዘመናዊ ዳንስ ተወዛዋዦች በእለቱ ታዳሚውን በውዝዋዜ ዘና ሲያደርጉት ተስተውሏል።



በፕሮግራሙ ላይ በድርጅቱ ምርቶች አከፋፋይነት በአ.አ እና በክልል የሚሰሩ ኤጀንቶች መሃከል በስራቸው ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ወኪሎች ከድርጅቱ ባለ 32" ፍላት ቴሌቭዥን በሽልማትነት ተበርክቶላቸዋል። እንዲሁም በስራቸው ምስጉን ተግባር የከወኑ የድርጅቱ አባላት የአይቴል S31 ስማርት ስልኮችን ተሸልመዋል።

በመድረኩ ላይ ከሽልማት እና ኬክ መቁረስ ስነስረአቱ በፊት አይቴል ሞባይል ከየት ወዴት እንደተጓዘች ፣ የድርጅቱ አጠቃላይ አለማቀፋዊ ስኬት ስታቶች እና ቀጣይ የተያዙ እቅዶች ለታዳሚው በግልፅ ቀርበዋል። እንዲሁም ድርጅቱ በቀጣይ የሚያወጣው አዲስ ሲሪየስ ስልክም ተዋውቋል።

Anniversary Of Itel 2007-2017 በሚል ከተከበረው ደማቅ ዝግጅት ላይ የአይቴል ኢትዮጵያ ብቸኛው ወኪል እና አከፋፋይ የሆኑት አቶ አለማየው ሃይሌ በቦታው በመገኘት ለፕሮግራሙ የተዘጋጀውን ልዩ ኬክ ቆርሰው ታዳሚዎች ወደ ፎቶ ፕሮግራም እና እራት ግብዧ እንዲያመሩ ጋብዘዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የአይቴል ቢዝነስ ዩኒት ማርኬቲንግ ዳይሬክተር የሆኑት ቺ ሊ የድርጅቱ አነሳስና አስር ስኬታማ አመታት ጉዞ ምን እንደሚመስል በፕሮጀክተር በተደገፈ ገለፃ ለታዳሚው አቅርበዋል። አቶ ሊ እንዳብራሩት ከሆነ አይቴል ሞባይል በአፍሪካ ስራውን የጀመረው በ10 ሃገራት ላይ ቢሆንም አሁን ግን ከ2012 ጀምሮ ባሉ አመታት ከ30 በላይ በሆኑ የአህጉሪቷ ሃገሮች ውስጥ ቅርንጫፎችን በመክፈት ገበያውን በስፋት ስለመቀላቀሉ ገልፀዋል። ሊ ጨምረው እንደጉለፁት ከሆነ ከአስር ስኬታማ አመታት በኃላ ድርጅቱ በመላው አለም ከ50 በላይ ሃገራት ውስጥ ገበያውን ሰብሮ በመግባት ከግዜ ወደ ግዜ ተፈላጊነቱና ተጠቃሚዎችን በብዛት እያፈራ ያለ መሆኑንም ገልፆ ፤ በቅርቡ ደግሞ ድርጅቱ በሌሎች ተጨማሪ የአለም ሃገራት ላይ ገበያውን በስፋት ለመቀላቀል እና ተደራሽነቱን ለመጨመር አቅዶ መንቀሳሰቀስ መጀመሩን አብራርተዋል።



አይቴል በአፍሪካ ካሉ እውቅ ብራንዶች መካከል(Most-Admired Brand In Africa) በሚል በአጭር ግዜ ውስጥ 25ኛ ደረጃን መያዝ የቻለ ተቋም ሆኑአል። እንዲሁም በአፍሪካ ከሚገኙ ቶፕ-3 የሞባይል ብራንዶች (Top-3 Social Media Mobile Brand in Africa) ውስጥ አንዱ መሆን ችሏል። ድርጅቱ በ2017 ላይ ወደ ኔፓል፣ ሲሪ ላንካ፣ ኢራን እና ኢንዶኔዢያ ገበያዎች ውስጥ በመግባት ምርቶቹን በመላው አለም ከጃፍ እስከ ጫፍ የማዳረስ እቅድ እንዳለው ተገልፆአል። ቡተጨማሪም በቀጣዮቹ ግማሽ አመታት ውስጥ ወደ ሩሲያ፣ ደቡብ አሜሪካ እና ሜክሲኮ ገበያዎችም ይገባል ተብሎ ታቅዷል።

ሊ ሰፋ ባለው ማብሪያራቸው ላይ ጨምረው እንደገለፁት ከሆነ ድርጅቱ ለዚህ ስኬት የበቃው ከላይ እስከ ታች ባሉ ትጉህ ሰራተኞቹ ጥረት መሆኑን ገልፀው ምስጋናቸውን በማቅረብ "If you want to go fast, go alone. If you want to go far, go together" የሚል ዕውቅ የአፍሪካውያንን አባባል በመጥቀስ ድርጅቱ ወደፊትም ከሰራተኞቹ ጋር በመሆን በጋራ ጠንክሮ በመስራትና ከትርፋማነቱ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን "Win Win" ስትራቴጂውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ ማብራሪያቸውን አጠናቀዋል።

ኬቭን ዙ የአይቴል ሽያጭ ማናጀር በኢትዮጵያ አዲስ ስልክ ምርት ሲሪየስን (itel S32) ያስተዋወቁ ሲሆን ስልኩ ሁለት የኃላ ካሜራዎችን የተገጠመለት እጅግ ማራኪ ስልክ ነው። የቀድሞው ሲሪየስ አይቴል S31 ስልክ በጁላይ 2017 ከ1,016,638 ጊዜ በመሸጥ ከፍተኛ የሽያጭ ቁጥር መመዝገቡን አያይዘው ገልፀውታል።

አዲሱ አይቴል S32 ሲሪየስ ስልክ የተገጠሙለት ባለሁለት ካሜራ ሌንሶች ራስን በራስ በተናጥል እንዲሁም በግሩፕ ፎቶዎችን በጥራት ለማንሳት የሚያስችሉ አማራጮች ያሉት ቀፎ ነው። ስልኩ ከመንትያ ካሜራዎቹ በተጨማሪም በ120° አንግል ድረስ ያሉ ቦታዎችን መሸፈን የሚችል በመሆኑ ብዙ ሰዎችን በፎቶ ፍሬሙ የማካተት ሰፊ ዕድል አለው።

ስልኩ ከጀርባው በተገጠመለት የጣት አሻራ ሴንሰር ብቻ በ0.1 ሴኮንድ ጊዜ ውስጥ ብቻ የራስ-በራስ ፎቶዎችን ያስቀራል። የ5.5 HD ስክሪን ስፋትም ተገጥሞለታል። ስልኩ በሦስት የተለያ አማራጭ ቀለሞች ጥቁር፣ ግራጫ እና ሰማያዊ እንደቀረበም ዙ ገልፀዋል። ስልኩን ለየት እሚያደርገው አዲስ ተጨማሪ ፊውቸሩ Blue-Ray eye Protection የሚል አማራጭ የያዘ የተመጠነ ሰማያዊ ጨረር መቀየሪያ አማራጭ ያለውም ነው ብለዋል።


Featured Post/ቀጣይ ልጥፍ

የዝውውር ዜናዎች

  ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር...