Monday, September 28, 2020

የዝውውር ዜናዎች

 



ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር ዩናይትድን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል።  [mufcMPB]


እንዲሁም ማንቸስተር ዩናይትዶች ለእንግሊዛዊው የቦሩሲያ ዶርትመንድ ክንፍ ጃደን ሳንቾ ዝውውር የመጨረሻ ያሉትን የ90 ሚሊዮን ፓውንድ ሂሳብ እሚያቀርቡት በዚህ ሳምንት ነው።  [Liam Bradford84]


አርሰናሎች ለሁሴም አዋር ያቀረቡት የ €36m ሂሳብ ውድቅ ከተደረገባቸው በኃላ አዲስ በድጋሚ ያቀረቡት የ€38m, ሂሳብም በሊዮኖች ወዲያው ውድቅ ተደርጓል። ሊዮኖች ተጭዋቹን ለመልቀቅ እስከ €50m ድረስ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል።  [mohamedbouhafsi]


ሆኖም ሁለቱ ክለቦች በተጭዋቹ ዝውውር ዙሪያ አሁንም ድርድር ላይ ናቸው። ሁሴም አዋር አርሰናልን መቀላቀል ይፈልጋል።  [DiMarzio]


አሁን መድፈኞቹ የመጨረሻ ያሉትን የ€40m +  €10m በጉርሻ መልክ አዲስ ሂሳብ ለፈረንሳዩ ክለብ ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል።  [jamesbeng)


ማንቸስተር ዩናይትዶች ከፈረንሳዊው የቻልሲ አማካይ ንጎሎ ካንቴ ወኪሎች ጋር በዝውውሩ ዙሪያ ንግግር አድርገዋል። ሆኖም ዝውውሩ እንዲሳካ ንጎሎ ካንቴ በቼልሲ ቤት ይከፈለው የነበረውን ሳንታዊ የ£300,000 ደሞዝ ከቀነሰ ብቻ ነው። (Mirror)


ፒኤስዤዎች የ28 አመቱን ጣሊያናዊ አማካይ ጀርጊንዎ በአመት ውሰት ውል ከቼልሲ ስለሚያስፈርሙበት ሁኔታ ንግግር ላይ ናቸው። 

 (Telefoot, via Mail)


ላዚዎዎች ለስፔናዊው የ32 አመት አማካይ ዩሃን ማታ እና ለ24 አመቱ ብራዚላዊ አማካይ እንድርያስ ፔሬራ የዝውውር ለእንግሊዙ ክለብ ጥያቄ ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል።  (Sun)


ቶተንሃሞች የቤኔፊካውን ሲውዘርላንዳዊ አጥቂ ሃሪስ ሴፍሮቢችን በውሰት ውል ለማስፈረም ጥያቄ አቅርበዋል። (Football Insider)


ሲቲዎች አንዴ የቤኔፊካውን የ23 አመት ተከላካይ ሩበን ዲያዝን ዝውውር ካጠናቀቁ በኃላ የ19 አመቱ ስፔናዊ ተከላካይ ሉዊስ ጋርሺያ ወደ የሚፈልገው ባርሴሎና እንዲዛወር ፍቃዳቸውን የሚሰጡት ይሆናል።  (Sport - in Spanish)


ሌዝስተር ሲቲዎች የቶሪኖውን ብራዚላዊ የ23 አመት መሃል ተከላካይ ግሊሰን ብሬመርን ለማዛወር ጥያቄ ያቀርባሉ። ተጭዋቹ የኤቨርተን የዝውውር ኢላማም ነው።  (Football Insider)


ባርሴሎናዎች የኢንተር ሚላኑን የ23 አመት አርጀንቲናዊ አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ ለማስፈረም ሲያደርጉት የነበረውን ጥረት አቋርጠዋል። 

(Calciomercato - in Italian)


ማንቸስተር ሲቲዎች በግራ ተመላላሽ ወይም በግራ ክንፍ ቦታ መጫወት የሚችለውን የ23 አመቱን ዩክሬናዊ ተከላካይ አሌክሳንደር ዚቼንኮን ባርሴሎናዎች እንዲያስፈርሙት አቅርበውላቸዋል። 

 (Mundo Deportivo - in Spanish)


ባርሴሎናዎች የ 19 አመቱን ሆላንዳዊ የአያክስ ቀኝ ተመላላሽ ተከላካይ ሰርጂኖ ደስትን ለማስፈረም ተቃርበዋል። ተጭዋቹ ዛሬ የህክምና ምርመራውን በስፔን እንደሚያደርግ ይጠበቃል።  (Mundo Deportivo - in Spanish)


ሆኖም ባየር ሙኒኮች በቅድስት ዝውውር ላይ በአያክስ እንደተከዱ ያምናሉ። ለዝውውሩ ከተጭዋቹ ጋር ከስምንት በፊት ከስምምነት ቢደርሱም ከሆላንዱ ክለብ ጋር ግን በሌሎች ጉዳዮች ላይ መስማማት አቅቷቸው ቆይቷል። 

 (Sport - in Spanish)

Sunday, September 27, 2020

እሁድ ምሽት የወጡ የዝውውር ዜናዎችና መረጃዎችን ያንብቡ - Latest Transfer News Update!

 



ሊዮን ለአማካዩ ሆሳም ኦዋር የቀረበውን የ32.8 ሚ. ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ውድቅ በማድረግ 46 ሚ. ፓውንድ እንደሚፈልግ አስታወቀ፡፡ አርሰናል በድጋሜ

ለተጫዋቹ 36.5 ሚ. ፓውንድ እና 9 ሚ. ፓውንድ በተጨማሪ የሚከፈል ሂሳብ ለማቅረብ ተዘጋጅቷል፡፡( Football London)



ቸልሲ ለዌስትሃሙ አማካይ ዴክላን ራይስ ከ40 ሚ. ፓውንድ ከፍ ያለ የዝውውር ሂሳብ ለማቅረብ ተዘጋጅቷል፡፡ ዌስትሃም ገንዘብ ስለሚፈልግ ተጫዋቹን ሊሸጠው ይችላል፡፡  (Sun)



ዌስትሃሞች የቸልሲውን ተከላካይ አንተኒዮ ሩዲገር በውሰት ማስፈረም ይፈልጋሉ፡፡  (Sun)



ባርሴሎና ለ17 አመቱ አጥቂ አንሱ ፋቲ የቀረበውን የ125 ሚ ዩሮ የዝውውር ሂሳብ እና ብቃቱ እየታየ የሚጨመረ 25 ሚ. ዩሮ ተጨማሪ ገንዘብ ቀርቦለት ውድቅ ማድረጉ ተዘገበ፡፡ ይሁንና የክለቡ ስም አልተገለፀም፡፡ በርካታ ጋዜጦችም

ማንችስተር ዩናይትድ አጥቂውን በጣም ሲፈልገው እንደነበር አስነብበዋል፡፡ (Marca)



ቶሪኖ የአርሰናሉን አማካይ ሉካስ ቶሬራ እንደማይፈልግ አስታወቀ፡፡ ቶሪኖ ተጫዋቹን በውሰት ነው የሚፈልገው አርሰናል ግን በቋሚነት መሸጥ ነው እቅዱ፡፡ አትሌቲኮ ማድሪድ የተጫዋቹ ፈላጊ ሲሆን እሱም በውሰት ነው

ለመውሰድ ያቀደው፡፡  (Football London)



የቸልሲው አማካይ ንጎሎ ካንቴ ለዝውውር ራሱን አዘጋጅቷል፡፡ ካንቴ በቸልሲ ጨዋታዎች ላይ በቋሚነት እየተሰለፈ ቢሆንም የዌስትሃሙ ዴክላን ራይስ መምጣት ቦታውን ሊያሳጣው ይችላል፡፡ በቀጣይ አመት ለሚደረገው የአውሮፓ አህጉር ውድድር ለመመረጥ በቂ የመሰለፍ ጊዜ ስለሚያስፈልግ ወደ ሌላ ክለብ ለመሄድ ተዘጋጅቷል፡፡  (express)



ኢንተር ሚላን የቸልሲውን አማካይ ንጎሎ ካንቴ ለማስፈረም፣ ስሎቫኪያዊውን ተከላካይ ሚላን ስክሪኒር፣ እንዲሁም ክሮዒሺያዊውን አማካይ ማርሴሎ ብሮዞቪች ለቸልስ ለመስጠት ተዘጋጅቷል፡፡(90 min)



የሊቨርፑሉ ወጣት አጥቂ ርያን ብሪውስተር ከክሪስታል ፓላስ ጋር ንግግር ሊጀምር ነው፡፡ ሼፈልድ ዩናይትድ እና አስቶንቪላም ተጫዋቹን ይፈልጉታል፡፡ (Mail)



ዩድኒዜ ከሊድስ ዩናይትድ ለአማካዩ ርድሪጎ ዴ ፓውል የሚቀርበው ሂሳብ 40 ሚ. ፓውንድ መሆን እንዳልበት አስታውቋል፡፡ ሊድሶች 25 ሚ. ፓውንድ ነበር ያቀረቡት፡፡ (90 min)



ማንችስተር ሲቲ የእንግሊዛዊውን የ20 አመት አማካይ ፊል ፎደን ኮንትራት ለማራዘም ተዘጋጅቷል፡፡ ሳምንታዊ ደሞዙንም ከ30 ሺ ፓውንድ ወደ 150 ፓውንድ ሊያሳድግለት ነው፡፡  (90 min)



ሊቨርፑል፣ ሊድስ እና ብራይተን ለ16 አመቱ የማዘርዌል ተከላካይ ያቀረቡት የዝውውር ሂሳብ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ሶስቱ ክለቦች አሁን ለተጫዋቹ የሚያቀርቡት ጥቅማ ጥቅም ነው የሚጠበቀው፡፡ ሊቨርፑል ከተከላካዩ ወኪል

ጋር ለመነጋገር ቀጠሮ ይዟል፡፡ (Football Insider)



በ17 አመቱ ለፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን ተሰልፎ የተጫወተው እና በሪያል ማድሪድ የሚፈለገው የሬኔው አማካይ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ በሬኔ እስከ 2021 ለመቆየት ፍላጎት አለው፡፡  (Marca)



ሪያል ማድሪድ ሰርቢያዊውን አጥቂ ሉካ ዮቪች በውሰት መልቀቅ ይፈልጋል፡፡የቀድሞ ክለቡ ኢንትራክት ፍራንክፈርት ግን ተጫዋቹን መውሰድ አይፈልግም፡፡  (AS)



ሀርታ በርሊን በቦሩሺያ ዶርትንድ የተለቀቀውን ማርዮ ጎትዜ ማስፈረም ይፈልጋል፡፡ (Bild)



የአያክሱ ተከላካይ ሰርጂኖ ዴስት ወደ ባርሴሎና ለመዘዋወር ተቃርቧል፡፡ የ19 አመቱ የቀኝ ተመላላሽ ሰኞ ባርሴሎና እንደሚደርስ እና ክለቡም ከ21 ሚ. ፓውንድ በላይ እንደሚክፈል ይጠበቃል፡፡ (De Telegraaf)



ማንችስተር ዩናይትድ የፖርቶውን ተከላካይ አሌክስ ቴሌስ እንደሚያስፈረመው ተስፋ አድርጓል፡፡ ነገር ግን ሁኔታዎች ቀስ ብለው እየሄዱ ይገኛሉ፡፡ (Fabrizio)



የዋትፎርዱ አማካይ ኢቴን ካፖ ወደ ቫሌንሺያ ለማምራት ተዘጋጅቷል፡፡  (Mirror)



ቅዳሜ የተደረጉ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ውጤት 


FT| ብራይተን 2-3 ማንችስተር ዩናይትድ

FT| ክሪስታል ፓላስ 1-2 ኤቨርተን

FT| ዌስትብሮሚች 3-3 ቸልሲ

FT| በርንሌ 0-1 ሳውዝሀምፕተን


እሁድ| ሼፊልድ ዩናይትድ 8:00 ሊድስ ዩናይትድ 

እሁድ| ቶተንሀም ሆስፐር 10:00 ኒውካስል ዩናይትድ 

እሁድ| ማንችስተር ሲቲ 12:30 ሌስተር ሲቲ

እሁድ| ዌስትሀም 3:00 ወልቭስ


ሰኞ| ፉልሀም 1:45 አስቶንቪላ

ሰኞ| ሊቨርፑል 4:00 አርሰናል



የስፔን ላሊጋ ጨዋታዎች ውጤት..


FT | ዲፖርቲቮ አላቬስ 0-0 ጌታፌ

FT | ቫሌንሺያ 1-1 ሁሴክ

FT | ኢልቼ 0-3 ሬያል ሶሲዳድ

FT | ሬያል ሴቲስ 2-3 ሬያል ማድሪድ


እሁድ| ኦሳሶና 7:00 ሌቫንቴ

እሁድ| ኢባር 9:00 አትሌቲኮ ቢልባኦ

እሁድ| አትሌቲኮ ማድሪድ 11:00 ግራናዳ

እሁድ| ካዲዝ 1:30 ሴቪያ

እሁድ| ሬያል ቫላዶሊድ 1:30 ሴልታ ቪጎ

እሁድ| ባርሴሎና 4:00 ቪያርያል



የፈረንሳይ ሊግ 1 ጨዋታ ውጤቶች..


FT| ሴንቲቴን 0-3 ሬምስ

FT| ማርሴ 1-1 ሜትዝ


እሁድ| ቦርዶ 8:00 ኒስ

እሁድ| አንገር 10:00 ብሬስት

እሁድ| ዲዦ 10:00 ሞንፔሌ

እሁድ| ሞናኮ 10:00 ስትራስቡርግ

እሁድ| ኒምስ 10:00 ሌንስ

እሁድ| ሎረንት 12:00 ሊዮን

እሁድ| ሬምስ 4:00 ፒኤስጂ



የጀርመን ቡንደስ ሊጋ ጨዋታዎች ውጤቶች..


አርብ| ኸርታ በርሊን 3 : 30 ኢንትራንክ ፍራንክፈርት


FT| ቦርሲያሞቸግላድባክ 1-1 ኡኔን በርሊን

FT| ባየርሊቨርኩሰን 1-1 አርቢላይፕዚክ 

FT| ሜንዝ 1-4 ስቱት ጋርት

FT| ኦግስበርግ 2-0 ቦርሲያዶርትመንድ 

FT| አርሜንቤስፊልድ 1-0 ኮሎኝ

FT| ሻልካ 1-3 ወርደር ብሬመን


እሁድ| ሆፈንሄም 10:30 ባየርሙኒክ

እሁድ| ፍራይቡርግ 1:00 ወልፍስበርግ


የጣልያን ሴሪያ ጨዋታዎች ውጤት..


FT| ቶሪኖ 2-4 አትላንታ

FT| ካግላሪ 0-2 ላዚዮ 

FT| ሳምፒዶሪያ 2-3 ቤኔቬንቶ

FT| ኢንተር ሚላን 4-3 ፊዮረንቲና


እሁድ| ስፔዝያ 7:30 ሳሱሎ

እሁድ| ናፖሊ 10:00 ጄኖዋ

እሁድ| ሄላስ ቬሮና 10:00 ኡዱኑዜ

እሁድ| ክሮቶኔ 1:00 ኤስሚላን

እሁድ| ሮማ 3:45 ዩቬንቱስ


ሰኞ| ቦሎኛ 3:45 ፓርማ

Monday, December 24, 2018

ማን.ዩናይትዶች ከጆዜ ስንብት በኃላ ያደረጉት ፈጣኑ አስገራሚ ነገር ይፋ ሆነ



ሊቨርፑል እና ቼልሲዎች ክርስቲያን ፖሊሲችን ለማዛወር የነበራቸው እድል ጨምሯል።

ይሄ የሆነው የጀርመኑ ግዙፍ ክለብ ባየር ሙኒክ አሜሪካዊውን የክንፍ መስመር ተጫዋች ላለፉት 18 ወራት ያህል ሲከታተሉት ከቆዩ በኃላ በድንገት እቅዳቸውን መቀየራቸው ነው።

ባቭሪያኖቹ በ2019 አመት ላይ እድሜያቸው የገፉ የክለቡ ተጭዋቾችን በማሰናበት በአዲስ ሊተኩ ያቀዱ ሲሆን በፑሊሲች ዝውውር ምትክ የባየር ሊቨርኩሰኑን Kai Havertz ለማዛወር ከወዲሁ ቅድመ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

________________________________________


አርሰናሎች Henrikh Mkhitaryan የእግር ጣት ጉዳት በማስተናገዱ እስከ ፌበርዋሪ ድረስ ከሜዳ እንደሚርቅ ገለፁ።

የ29 አመቱ አርሜኒያዊው ኢንተርናሽናል ጉዳቱን ያስተናገደው ቡድኑ ከቶተንሃም ጋር በCarabao Cup በቶተንሃም ሲሸነፍ ነው።

አርሰናሎች ዛሬ እንዳረጋገጡት ከሆነ ተጭዋቹ ለሳምንት ያህል ምርመራ ካደረገ በኃላ የእግር ጣት ስብራት እንደገጠመው እና ጉዳቱ ቢያንስ ለስድስት ሳምንታት ከሜዳ እንሰሚያርቀው አረጋግጠዋል።

ይሄ ማለት ተጭዋቹ የገና ሰሞን የfestive fixtures ጨዋታዎች የሚያመልጡት ከሆነ የጃንዋሪ ሙሉ ፕሮግራሞችም ያመልጡታል።

________________________________________


ማንቸስተር ዩናይትዶች ጆዜ ሞሪንዎን ባሰናበቱ አምስት ደቂቃዎች ውስጥ የፓርቹጋላዊውን አለቃ ቢሮ ቁሳቁሶች በፍጥነት እንዳፀዷቸው ተገለፀ።

ፖርቹጋላዊው ኢንተርናሽናል በሊቨርፑል የ3ለ1 ሽንፈት ከደረሰባቸው ከ48 ሰአታት በኃላ ባለፈው ማክሰኞ ከስራ እንደተሰናበቱ ይታወሳል።

የዩናይትዱ አለቃ ኢድ ውድዋርድ ቢሮአቸው ከጆዜ ሞሪንዎ ጋር የ44 ደቂቃ ውይይት ካደረጉ በኃላ ንግግራቸውን በስንብት ቋጭተዋል።

የክለቡ የፅዳት ቡድን አባላት ቢሮአቸው ገብተው እንዲያፀዱት የተነገራቸው ወዲያውኑ ነበር። ግድግዳ ላይ ተለጥፈው የነበሩ የሞሪንዎ ፎቶዎች እና በቆይታቸው ያገኙአቸው ዋንጫና ሜዳልያዎችም ታሽገው እንዲወጡ ተደርገዋል።

አንድ ምንጭ ለThe Sun ጋዜጣ እንዳለው ከሆነ : "ጆዜን ወደ ታሪክ ለመቀየር 15 ደቂቃ ብቻ ነው የፈጀው። የእርሱ የነበሩ ወረቀቶችን ሁሉ ሳይቀር በነጭ ፌስታል ውስጥ ተቋጥረው እንዲወገዱ ተደርገዋል።"

Saturday, December 1, 2018

ዩናይትዶች ለሴኔጋላዊው መሃል ተከላካይ የ91 ሚ.ፓ ሂሳብ አቀረቡ


ማንቸስተር ዩናይትዶች ለናፖሊው መሃል ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊ የአለም ሪከርድ የዝውውር ሂሳብ አቀረቡ



ናፖሊዎች ለመሃል ተከላካያቸው ካሊዱ ኩሊባሊ ከማቸስተር ዩናይትድ ቀርቦላቸው የነበረን የአለም ተከላካይ ተጭዋቾችን ሪከርድ የዝውውር ሂሳብ  £91 ሚሊዮን ፓውንድ ውድቅ አደረጉ።
(ምንጭ፦ Corriere dello Sport)

Tuesday, November 27, 2018

ማክሰኞ ምሽት የወጡ አዳዲስ የዝውውር ወሬዎች



ሜሱት ኦዚል በአርሰናል የመቆየቱ ነገር አጠራጣሪ እየሆነ መጥቷል። ተጭዋቹ ቡድኑ ከሜዳ ውጪ በሚያደርገው ጨዋታዎች ላይ ቤንች ላይ መቀመጡ አላስደሰተውም።

ኡናይ ኤምሬ በበኩላቸው ቡድኑ ከኢንተርናሽናል እረፍት በፊት ከክሪስታል ፓላስ ጋር ባደረገው ጨዋታ ላይ ነጥብ ሲጥል ለቡድኑ ባደረገው አስተዋፅዎ ደስተኛ አይደሉም። ከዛም በበርንማውዙ ጨዋታ ላይ ተጠባባቂ አድርገውታል። ተጭዋቹ ኢምሬትስን የሚለቅ ከሆነ ማን.ዩናይትዶች አማካዩን የማዛወር የተሻ እድል አላቸው።  (ምንጭ፦ johncrossmirror)

.

ማንቸስተር ሲቲዎች የፖርቹጋሉን የ21 አመት ብሄራዊ ቡድን ተጭዋች ስቴፈን ኢውስታኪዮ ለማዛወር እየተከታተሉት ነው። ለቼቫስ የሚጫወተው ባለተሰጥዎ በባርሴሎና፣ ሪያል ቤቲስ እና ስፖርቲንግም ጭምር ይፈለጋል። ኮንትራቱ ላይ የ£13.3m ውል ማፍረሻ አለው።     (ምንጭ፦ Daily Mail)

.

ጋላታሳራዮች የሊቨርፑሎቹን አጥቂ ዶሚኒክ ሶላንኬ እና ዲቮክ ኦርጂን የማዛወር እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
(ምንጭ፦ Daily Mirror)

.

ኦስማን ዴምቤሌይ ለባርሴሎና ክለብ አመራሮች የጥር የዝውውር መስኮት ከመከፈቱ በፊት ከክለቡ እንዲለቁት መወትወቱን ቀጥሎበታል። ስሙ ከአርሰናል ዝውውር ጋር መያያዙን ተከትሎ በጥር ክለቡን መልቀቅ ይፈልጋል።   (ምንጭ፦ Daily Mail)

.

ኤሲ ሚላኖች የቼልሲውን እና የእንግሊዙን ኢንተርናሽናል መሃል ተከላካይ ጋሪ ካሂል እንዲያስፈርሙት ቀርቦላቸው ሳይቀበሉት ቀርተዋል።
(ምንጭ፦ Calciomercato)

.

ማንቸስተር ዩናይትዶች የቦሩሲያ ዶርትመንዱን አማካይ አክስል ዊትሰል መከታተላቸውን አሁንም ቀጥለውበታል። ምንም እንኳን ክለቡ በክረምቱ ብራዚላዊውን አማካይ ፍሬድ ቢያዛውርም ሞሪንዎ አሁንም የአማካይ ክፍሉ ችግር እንዳልተቀረፈ ተረድተውታል።   (ምንጭ፦ Daily Star)

.

የቀድሞው የአርሰናል አለቃ አርሰን ዌንገር ወደ አሰልጣኝነት ስራቸው መመለስ የሚፈልጉ ሲሆን ኒኮ ኮቫችን ለማሰናበት የተዘጋጁት ባየር ሙኒኮች ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ቀጣዩ የቡድናቸው አለቃ አድርገው ሊሾሙአቸው እያጤኑበት ነው ተብሏል።
(ምንጭ፦ Telegraph)

.

የቀድሞው እንግሊዛዊ ኢንተርናሽናል አሽሊ ኮል በአሜሪካው የ MLS ሊግ ክለብ LA Galaxy ተለቋል።   (ምንጭ፦ LAGalaxy)

.

ጎንዛሎ ሂጉዌይን ቼልሲን የመቀላቀል ፍላጎት አለው። አርጀንቲናዊው አጥቂ በናፖሊ ከማውሪዚዮ ሳሪ ጋር አንድ ላይ የሰራ ሲሆን በድጋሚ የለንደኑን  ክለብ ተቀላቅሎ ከአሰልጣኙ ጋር በድጋሚ መስራት ይፈልጋል።  (ምንጭ፦ Corriere dello Sport)

.

ኔይማር እና ክለቡ PSGዎች ብራዚላዊው ኮከብ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ለዝውውሩ የ€200 ሚሊዮን ዩሮ ሂሳብ የሚቀርብላቸው ከሆነ ወደ ላ ሊጋው እንዲዛወር ፍቃዳቸውን እንደሚሰጡት ከወዲሁ ቅድመ ስምምነት ቃል ገብተውለታል። (ምንጭ፦ Betevé)

.

ሪያል ማድሪዶች የጁቬንቱሱን ፓብሎ ዳይባላ ለማዛወር የነበራቸውን ምኞች እንደማይሳካ ተስፋ አስቆርጧቸዋል። ከእርሱ ይልቅ በክረምቱ ብራዚላዊውን ኮከብ ኔይማር ወደ በርናባው ለማዛወር ሙከራ ለማድረግ ወስነዋል።
(ምንጭ፦ Calciomercato)

.

የቼልሲው የፊት መስመር ተሰላፊ ኤዲን ሃዛርድ ወደ ፈረንሳዩ ክለብ PSG ይዛወራል መባሉን አስተባበለ። ሆኖም የ27 አመቱ ቤልጂየማዊ ኮከብ በክረምቱ ክለቡን ሊለቅ እንደሚችል ፍንጭ ሰትቷል።
(ምንጭ፦ Canal+)

.

ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃሞች የሳምፕዶሪያውን የ22 አመት ተከላካይ ጃኪም አንደርሰን ሁኔታ በቅርበት በመከታተል ላይ ናቸው።  (ምንጭ፦ Daily Mirror)

.

Official: ማይክ ዲን የፊታችን እሁድ የሚደረገውን ተጠባቂ የለንደ ደርቢ አርሰናል እና ቶተንሃም ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በመሃል ዳኝነት እንደሚመሩት FAው አሳውቋል።

.

አርሰንልን ሲጫውቱ ክለቡ የውጤት ድርቅ ይመታዋል የሚባልላቸው እና ከቀድሞው የአርሰናል አለቃ አርሰን ዌንገር ጋር በተደጋጋሚ ውዝግብ ውስጥ ሲገቡ የታዩት ዳኛ ማይክ ዲን በአንድ ወቅት ከቬንገር ጋር ስለፈጠሩት ዱላ ቀረሽ ግብግብ ተጠይቀው፦

"ከጨዋታው በኃላ ወደኔ ሲመጣ ለዱላ ተጋብዞ በንዴት መንፈስ ነበር። ጣቶቹን ወደኔ እየጠቆመ ደጋግሞ 'አንተ ታማኝ ዳኛ አይደለህም' ሲል ይናገረኝ ነበር። 'ስለዚህ አጭበርባሪ ነህ እያልከኝ ነው?' ስል መለስኩለት። 'አሁንም እደግመዋለው አንተን ላምንህ አልችልም በፍፁም' ሲል በድጋሚ መለሰልኝ"

"ከዛም 'እንደዚህ ጨዋታዎች ላይ ስትበድለን ዛሬ የመጀመሪያህ አይደለም፤ ሁልግዜም ትበድለናለህ፤ አንተኮ ፕሮፌሽናል ዳኛ መሆን ይጠበቅብሃል። አንተ ክብረ ቢስ የሆንክ ዳኛ ነህ' ሲል ወረደብኝ። በመሃል የዌስብሮም የሜዳ ላይ ኦፊሰሮች በነሃላችን ገብተው ካለሁበት የስቴዲየሙ ክፍል ይዘውት ወጡ" -  ሲል ምን ያህል ከፈረንሳዊው አለቃ ጋር ያን ወቅት ዱላ ቀረሽ ለሆነ ፀብ ተቃርበው እንደነበር ተናግሯል።
(ምንጭ፦ TheSun)

.

በርካታ የአውሮፓ ክለቦች ሊቨርፑል፣ አርሰናል እና ማንቸስተር ሲቲን ጨምሮ የሊዮኑን አማካይ ታንጋይ ንዶምቤሌይን ሁኔታ በቅርበት ሆነው በመከታተል ላይ ናቸው። ተጭዋቹ የ £55 million ዋጋ ያወጣል ተብሏል።  (ምንጭ፦ Anfieldhq)

.

ሊቨርፑሎች ክሪስቲያን ፑሊሲችን ከቦሩሲያ ዶርትመንድ በ£70 million ፓውንድ ሂሳብ ሊያዛውሩት ይችላሉ። ሆኖም። አሜሪካዊውን አማካይ ማስፈረም የሚችሉት በ2019 የዝውውር መስኮት ላይ ብቻ ከሆነ ነው።   (ምንጭ፦ LiverpoolEco)

.

ማንቸስተር ሲቲዎች በበኩላቸው አሌክሳንደር ዚቺንኮን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለመሸጥ የነበራቸውን እቅድ ሙሉ ለሙሉ ሰርዘውታል። ይሄ የሆነው ቤንጃሚን ሜንዲ ጉዳት ስላጋጠመው ነው።
(ምንጭ፦ TelegraphDucker)

.

ሪያል ማድሪዶች በጥር የዝውውር መስኮት ላይ የማን.ሲቲውን ተፈላጊ ባለተሰጥዎ አማካይ ብራሂም ዲያዝን ለማዛወር ሙከራ ያደርጋሉ። ለዝውውሩ ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥማቸው ይረዱታል። በጥር የማይሳካላቸው ከሆነ ግን በክረምቱ ኮንትራቱ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ያዛውሩታል። ተጭዋቹ በክረምቱ ወደ በርናባው ለማምራት ቅድመ ስምምነት ላይ ደርሷል ተብሏል።    (ምንጭ፦ ellarguero)

.

ሜሱት ኦዚል ሳይጠበቅ አርሰናልን ሊለቅ ይችላል የሚሉ ወሬዎች መሰማት ጀምረዋል። ኤምሬትስን ከለቀቀ ማን.ዩናይትድ አማካዩን የማዛወር የተሻለ እድል አላቸው ተብሏል።     (ምንጭ፦ Express)

.

ሞዬስ : "በኔ ዘመን ቶኒ ክሩስ ወደ ማን.ዩናይትድ ለመምጣት ሙሉ ለሙሉ ተስማምቶ ነበር። ከነ ባለቤቱ አግኝቼው በግል ተነጋግረን ነበር። ባየር ሙኒክ እያለ ወደ ዩናይትድ ለመምጣት በሁሉም ነገር ላይ ከስምምነት ደርሰን ነበር።"   (ምንጭ፦ Bild)

.

ያፕ ሄንኪንሰን በባየር ሙኒክ እየተከሰተ ስላለው የቡድኑ ቀውስ ዝምታቸውን ሰብልረዋል:

"በቡድኑ ውስጥ መልአክ የሆኑ እና ሰይጣን የሆኑ ሁለት አይነት ሰዎች አሉ። በጉዳት ሳቢያ የማይጫወቱ ደግሞ የቡድኑ ቁልፍ ተችዋቾችም አሉ። በክለቡ አናት ላይ የተከመረ ትልቅ የችግር ተራራ ይገኛል።" - ሲል አስገራሚ ምላሽ ሙኒክ ላይ ሰጥተዋል።    (ምንጭ፦ Westdeutsche Zeitung)

Monday, November 26, 2018

ሰኞ ምሽት የወጡ ተጨማሪ አዳዲስ የዝውውር ዜናዎች



ማንቸስተር ዩናይትዶች የናፖሊውን መሃል ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ ለማዛወር የተሻለ እድል አላቸው።   (ምንጭ፦ M.E.N)

.

ኦስማኔ ዴምቤሌይ በጥር የዝውውር መኮት ላይ ክለቡ ባርሴሎና እንዲለቀው ጥያቄ አቅርቧል። የእርሱ ክለቡን መልቀቅ የቀድሞው ብራዚላዊ ኮከብ ኔይማር ወደ ክለቡ እንዲመለስ በር የሚከፍት ነው ተሏል። ዴምቤሌይ በአርሰናል እንደሚፈለግ ይታወሳል።   (ምንጭ፦ Goal)

.

PSGዎች የማንቸስተር ዩናይትዱን ስፔናዊ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደ ሂያን ለማዛወር በሚያደርጉት ጥረት ላይ ከጁቬንቱሶች ከፍተኛ ፉክክር ይጠብቃቸዋል።  (ምንጭ፦ Sun Sport)

.

የማንቸስተር ዩናይትዶች አለቃ ጆዜ ሞሪንዎ ለዩሃን ማታ የሦስት አመት ኮንትራት ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። የ30 አመቱ ስፔናዊ በሲዝኑ መጠናቀቂያ ላይ ከኮንትራቱ ነፃ ይሆናል።
(ምንጭ፦ Mail)

.

ጆሴ ሞሪንዎ የዌስትሃሙ አጥቂ አርናቶቪችን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በማስፈረም ክለቡን ወደ ቶፕ 4 ውስጥ አስገብቶ ሲዝኑን እንዲያጠናቅቁ እንዲረዳቸው ይፈልጋሉ። ለተጭዋቹ ዝውውር የ50 ሚ.ፓ ሂሳብ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።
(ምንጭ፦ Sunday Mirror)

.

ቼልሲዎች ኤዲን ሃዛርድን በሪያል ማድሪድ እንደሚነጠቁ ማመን ጀምረዋል። የስፔኑ ሃያል ክለብ ቤጂየማዊውን ለማዛወር ከወዲሁ እንቅስቃሴ መጀመራቸው የተነገረ ሲሆን ክለቡ በክረምቱ ሊያዛውር ከሚፈልጋቸው ጋላክቲኮዎች ቀዳሚው ሆኑአል።   (ምንጭ፦ OK Diario)

.

የባየር ሙኒኩ አለቃ ኒኮ ኮቫች ገና በመጀመሪያው ዙር የቡንደስሊጋ የውድድር አጋማሽ ላይ ከክለቡ ለመሰናበት ተቃርበዋል። አሰልጣኙ ቡድኑን በሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ማሸነፍ ከተሳናቸው በኃላ የክለቡ ባለስልጣናት ትእግስታቸው አልቋል።
(ምንጭ፦ Sun Sport)

.

አርሰናሎች የማንቸስተር ዩናይትዱን ፔሬራ ለማዛወር በሚፈረገው ፉክክር ላይ ተቀላቀሉ። ፔሬራ በፕሪሚየር ሊጉ መቆየት የሚፈልግ ሲሆን በሲዝኑ መጠናቀቂያ ላይ አዲስ ኮንትራት እስካልፈረመ ድረስ ከኮንትራት ነፃ በመሆኑ ክለቡን በነፃ መልቀቅ ይችላል። ሆኖም መድፈኞቹ ተጭዋቹን ከማዛወር ከቼልሲ ፉክክር ይጠብቃቸዋል።  (ምንጭ፦ Mirror)

.

ሴስክ ፋቤጋዝ ከቤሺክታሾች የእናዛውርህ ጥያቄ ቀርቦለታል። ያም ሆኖ ኤሲ ሚላኖች የቼልሲውን አማካይ ለማዛወር የተሻለ እድል ይዘዋል ተብሏል።
(ምንጭ፦ Sunday Express)

.

ፒር ኤምሬክ ኦበምያንግ በሁሉም ውድድሮች በዚህ ሲዝን ላይ 10 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል። ይሄ ሪከርድ የአርሰናሉ ጋቦናዊ አጥቂ አምና እስከ አፕሪል ወር ድረስ ያላሳካው ነው። (ምንጭ፦ swaka)

.

አሌክሳንደር ላካዜቲ በትላንቱ የመድፈኞች ድል ባደረጉበት ጨዋታ ላይ ያልተሰለፈው መጠነኛ የህመም ስጋት ስላለበት ነው ተብሏል። ሆኖም የአጥቂው ጉዳት ቀላል በመሆኑ በዩሮፓ ሊጉ ጨዋታ ላይ ይመለሳል ተብሏል።  (ምንጭ፦ Mirror)

.

ሮብ ስለ ኡናይ ኤምሬ እና አርሰን ዌንገር ልዩነት: “
"ትልቁ ልዩነት አሁን ማጥቃት ብቻ ሳይሆን እንዴት መከላከል እንሳለብን ማወቃችን ነው። እንዴት የተቃራኒ ክፍል ቦታ ጥቃት እንፈፅማለን ከዛም ወዲያውኑ ቡድኑ ሲጠቃ ወዲያው ተደራጅተን በሚገባ እንከላከላለን ከዛም በፍትነት በመልሶ ማትቃት የምንሄድበት መንገድ ሁሉ ተቀይሯል። ያ ነው ትልቁ ልዩነት።"

"ቡድኑ በቶፕ አራት ውስጥ ገብቶ ቢያጠናቅቅ እና አንድ ዋንጫ ቢያነሳ ለኔ አመቱ የስኬት ይሆናል ባይ ነኝ።" ሲል አስተያየቱን አጠቃሏል።
Skysports)

.

'በቶፕ 4 ውስጥ ገብተን የቻምፒየንስ ሊግ ቦታን ማስጠበቅ ካለብን ከዚህም በላይ መሻሻል ይኖርብናል' - ያሉት ደግሞ የአርሰናሉ አለቃ ኡናይ ኤምሬ ናቸው።  (ምንጭ፦ ArsenalNews)

.

ፍራንክ ሪበሪ በሴፕተምበር ወር ላይ ቡድኑ ከባየርን ሌቨርኩሰን ጋር ከመጫወቱ ቀደም ብሎ የቤተሰብ ጉዳይ እንዳለበት በማስፈቀድ ከአሊያንዝ አሬና ስቴዲየም ለቆ ሲወጣ ፎቶግራፍ ያነሳው የነበረን ጋዜጠኛ እንደመታው ተነግራል። ሪቤሪ በወቅቱ የፎቶግራፈሩን ትከሻ ጨምድዶ በመያዝም ያነሳውን ፎቶ ወዲያውኑ እንዲያጠፋውም በጩሃትና በዱላ አስገድዶታል።   (ምንጭ፦ Ozzywessi)

.

ፔፕ ጋርዲዮላ የፕሪሚየር ሊጉ ዋንጫ ፉክክር ላይ ሲጠየቅ: "የሊጉ ፉክክር ከናዳል፣ ፌደረር እና ጆኮቪች የቴኒስ ፉክክር ጋር ተመሳሳይ ነው። አንዱ ከአንደኛው የተሻለ ሆኖ እንዲመጣ ግፊት ያሳድርበታል። ምክንያቱም ይተዋወቃሉ። ይሄንን ፉክክር በስፖርቱ እንፈልገዋለን፤ ልክ እንደ አትሌቲክሱ ሁሉ። የሲቲ ተጭዋቾች ይሄንን ያውቁታል ምን ያህል ፉክክር እንዳለብን እኔ አልነግራቸውም። ሊቨርፑል ምን ያህል ጠንካራ ቡድን እንደሆነ ራሳቸው ያውቁታል።" - ሲል ስፔናዊው አሰልጣኝ ሊቨርፑል የሊጉ እውነተኛ ተፎካካሪያቸው ክለብ እንደሆነ ጠቁሟል።

.

ማንቸስተር ሲቲዎች የPSGውን አማካይ አድሪያን ራቢዮት ለማዛወር በሚደረገው ፉክክር ላይ ባርሴሎናን ተቀላቅለዋል። የ23 አመቱ ተጭዋች በፓሪሱ ክለብ ኮንትራቱን እንደማያድስ መናገሩ የሚታወስ ሲሆን በጁቬንቱስና በቶተንሃምም በትብቅ ይፈለጋል። ኮንትራቱ በጁን 30; 2019 ላይ እንደሚጠናቀቅ ይታወቃል።   (ምንጭ፦ Téléfoot)

.

"እርግጥ ነው በጥር የዝውውር መስኮት ክለቡን አይለቅም።" - ሲሉ የርገን ክሎፕ ፋቢንዎ በሊቨርፑል እንደሚቆይ ተናግረዋል። በቅርብ በወጡ ሪፖርቶች መሰረት ብራዚላዊው ኮከብ በሊቨርፑል መረጋጋት ስለተሳነው ክለቡን ይለቃል ተብሎ ሲወራ እንደነበር ይታወሳል።  (ምንጭ፦ LiverpoolEco)

.

የማንቸተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ክለቡ ስድስት ተጭዋቾችን በጥር የዝውውር መስኮት እንዲሸጥ ድምፅ ሰጥተዋል። በዚህ መሰረት ክለቡን እንዲለቁ ስሞሊንግ (48.8%), አሌክሲስ (37.6%), ቫሌንሺያ (35.3%), ሮሆ (17.4%) እና ዳርሜይን (7.5%) ናቸው።   (ምንጭ፦ M.E.N)

.

Liverpool and Chelsea receive Asensio boost

የሪያል ማድሪዱ ፕሬዝዳንት ፍሎረንቲኖ ፔቴዝ የሊቨርፑል እና የቼልሲ የዝውውር ኢላማ የሆነውን ማርኮ አሴንሲዮ በሌላ ተጭዋች ለመተካት አስበዋል ሲል Don Balon ዘገበ።

የፊት መስመር ተጭዋቹ የክርስቲያኖ ሮናልዶን ክፍተት ይሸፍናል ተብሎ ተስፋ ቢጣልበትም ለቡድኑ ውጤታማነት ምንም አስተዋፅዎ ማድረግ ተስኖት ታይቷል።

ማድሪዶች ስማቸው በተደጋጋሚ ግዜ ከኤዲን ሃዛርድ ዝውውር ጋር ተያይዞ የተነሳ ሲሆን የአሴንሲዎ አቋም ካልተሻሻለ ተጭዋቹን በመልቀቅ በቤልጂየማዊው ኮከብ ይተኩታል።

.

West Ham to resist Man Utd interest in Arnautovic

ዎስትሃም ዩናይትዶች ማርኮ አርናቶቪችን በጥር የዝውውር መስኮት ላይ በማንቸተር ዩናይትድ ሊነጠቁ ይችላሉ የሚሉ በርካታ ዘገቦች ቢሰሙም ተጭዋቹን ለዋቆየት የቻሉትን ሁሉ ሊያደርጉ ተዘጋጅተዋል ሲል London Evening Standard ዘግቧል።

አጥቂው በዚህ የውድድር አመት ላይ ጥሩ አቋም ላይ የሚገኝ ሲሆን ምንም እንኳን መዶሻዎቹ ከስቶክ ሲቲ ሲያዛውሩት ከከፈሉት የ £23 million ወይም (€26m/$29.5m) ሂሳብ በእጥፍ የሚያተርፊበት ሂሳብ ከዩናይትድ ይቀርብላቸዋል ቢባልም ላለመቀበል ተዘጋጅተዋል።

.

Isco looking for Madrid escape

አማካዩ ያለውን እምቅ ችሎታ አውጥቶ እንዲጠቀም ወደሚያደርገው ክለብ መዛወር ይፈልጋል። የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ኢስኮ ክለቡን ለመልቀቅ አስቧል ሲል Don Balon ዘግባል።

የቡድኑ አሰልጣኝ ሳንቲያጎ ስላሬ በክለቡ ትልቅ ለውጥ ለማድረግ ያቀዱ ሲሆን ኢስኮ ክለቡ ሊሰዋቸው ካሰባቸው ተጭዋቾች መካከል ይገኝበታል። ተጭዋቹ ቡድኑ ካደረጋቸው ያለፉት 5 ጨዋታዎች ውጪ ሆኑአል።

.

Suarez would prefer Arsenal move

የቀድሞው የማንቸስተር ሲቲ ተጭዋች ዴኒስ ሱዋሬዝ ወደ እንግሊዝ መመለስ ይፈልጋል።

እንደ AS ዘገባ ከሆነ ተጭዋቹ ወደ ደቡቡ እንግሊዝ ክለብ አርሰናል ለመዛወር ይፈልጋል።

ስፔናዊው ማን.ሲቲን በመልቀቅ ወደ ካምፕ ኑ ክለብ ከተዛወረ ወዲህ የሚፈልገውን ያህል የመሰለፍ እድል እያገኘ አይደለም።

ቼልሲ እና ቫሌንሺያ ተጭዋቹን የማዛወር ፍላጎት ቢኖራቸውም መድፈኞቹ ግን ከወዲሁ ፉክክሩን እንዳሸነፉት ይታመናል።

Saturday, November 24, 2018

የማን.ዩናይትዱ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደሂያ ወኪል ጆርጅ ሜንዴዝ ጣሊያን ቱሪን ይገኛል



ጁቬንቱሶች ሱፐር ኤጀንቱን ጆርጅ ሜንዴዝ በመቅጠር የማንቸስተር ዩናይትዱን ግብ ጠባቂ ዴቪድ ደ ሂያን ወደ ቱሪን የማዛወር ተልዕኮ ሰጥተውታል - በዚህ ሳቢያ ጆዜ ሞሪንዎ በጉዳዩ ላይ ክፉኛ ብስጭት ውስጥ ናቸው

እውቁ ፖርቹጋላዊ አደራዳሪ የዴቪድ ደ ሂያ ወኪል ሲሆን ግብ ጠባቂው በኦልትራፎርድ የመጨረሻ አመት ውሉ ላይ ሊገባ ተቃርቧል።

ዩናይትዶች ተጭዋቹን ለተጨማሪ 12 ወራት ውሉን የማራዘም መብቱ በጃቸው ነው። ስለዚህ አዲስ የኮንትራት እድሳቱ ባይፈረምና ቢቀር ተጭዋቹን በ2020 የውድድር አመት ላይ በነፃ የዝውውር ሂሳብ ያለምንም ችግር ወደፈለገበት ክለብ ስፔናዊው ማምራት ይችላል።

እንደ SunSport ዘገባ ከሆነ ዩናይትዶች ኮንትራቱ ሲጠናቀቅ ደ ሂያን የማጣት ትልቅ ስጋት ውስጥ ገብተዋል።

ሞሪንዎ ባለፈው ወር ላይ እንዳሉት ከሆነ የቀድሞው የአትሌቲኮ ማድሪድ ኮከብ ደ ሂያ በክለቡ እንደሚቆይ 'እርግጠኛ ስላለመሆናቸው' ተናግረው ነበር።

እናም ጁቬንቱሶች ስፔናዊውን ወደ ጣሊያን ለማስኮብለል በሚያደርጉት ጥረት ላይ ወኪሉ ጆርጅ ሜንዴዝ ላይ ልዩ ትኩረት አድርገው መስራት ጀምረዋል።

የጣሊያኑ ተነባቢ ጋዜጣ Tuttosport እንዳለው ከሆነ ሜንዴዝ ሁለት ደንበኞቹን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ላይ ወደ ቱሪን እንዲያመጣ ተጠይቋል። እነርሱም ዴቪድ ደ ሂያ እና ጀምስ ሮድሪጌዝ ናቸው።

ሮድሪጌዝ በአሁን ሰአት በባየር ሙኒክ በውሰት ተሰጥቶ በመጫወት ላይ ሲሆን ከሲዝኑ መጠናቀቅ በኃላ በሙኒክ ይቆይ አይቆይ የታወቀ ነገር የለም።

የክለቡ የSporting director የሆኑት Fabio Paratici እንዳሉት ከሆነ ክለቡ የዎልቭሱን ሩበን ኔቬስ በጥር የማዛወር እቅድ እንዳለው ተናግረው ነበር። ይሄም ተጭዋች ሌላኛው የሜንዴዝ ደንበኛ ነው።

ማንቸስተር ዩናይትዶች ከሰር አሌክስ ፈርጉሰን ክለቡን መልቀቅ በኃላ ውጤታማነታቸው በፍጥነት እየቀነሱ መምጣታቸው የሚታይ ሲሆን ዴቪድ ደ ሂያ ግን የቡድኑ ወሳኙ ሰው መሆኑን ቀጥሏል።

ተጭዋቹ በ2011 ወደ ክለቡ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ከተዛወረ በኃላ ከሰባት አመታቱ ውስጥ ለአራት ጊዜያቶች ያህል የክለቡ የአመቱ ኮከብ ተጭዋች በሚል ተመርጧል።


Eric Steele ስፖናዊውን ኢንተርናሽናል በእንግሊዝ ለመጀመሪያዎቹ ሁለት አመታት ያህል አሰልጥኖት ነበር። አሁን ክለቡን ስለመልቀቅ ማሰቡ ለሱ የሚያስገርም ዜና እንዳልሆነ ተናግሯል።

ግለሰቡ በግብ ጠባቂዎች ልዩ የUnion podcast, ላይ እንደተናገረው ከሆነ : "አሁን ደ ሂያን እምትጠይቁት ከሆነ በማንቸስተር ዩናይትድ ላይ ሙሉ ትኩረቱ እንደሆነ ይነግራችኊል።"

"እጅግ የተሳኩ አመታት አሉት። ከተጭዋቾቹም ሆነ ከደጋፊዎቹ ጋር ልዩ ቅርርብ አለው። ሆኖም እርሱ አሁን አሸናፊ መሆን ይፈልጋል። አሁን ክለቡን ስለመልቀቅ ሊያስብ ይችላል። የሚፈልጋቸውን ድሎች አሁን በዩናይትድ አገኝ ይሆን ብሎ ራሱን መጠየቁ አይቀርም"

"ሌሎች ተፎካካሪ ክለቦች በደንብ ሲጠናከሩ ተመልክቷል። ፉክክሩ አይሏል።

"እርሱም አሁን እድሜው 28 ነው። የብቃቱ ጫፍ ላይ ነው። ስለ ድል ማሰቡ ትክክለኛው ሰአቱ ነው።

"እኔ በግሌ በክለቡ እንዲቆይ እፈልጋለሁ። ማንቸተር ዩናይትድን ቢያጠናክር ለሊጉም ቢቆይ ብዬ እመኛለሁ"

ዴቪድ ደ ሂያ በማንቸስተር ዩናይትድ ኮንትራታቸው ሊጠናቀድ ከተቃረቡ 10 ተጭዋቾች መሃከል አንዱ ነው። አንቶኒ ማርሻል እና ዩሃን ማታም ይገኙበታል።

Featured Post/ቀጣይ ልጥፍ

የዝውውር ዜናዎች

  ማንቸስተር ዩናይትዶች ከቴላስ ጋር በግል ከስምምነት ደርሰዋል። ፖርቶዎች ለዝውውሩ €20m ድረስ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ። ሁለቱም ክለቦች በሂሳቡ ላይ ድርድር ላይ ይገኛሉ። አሌክስ ቴላስ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ማንቸስተር...